ልደቱ አያሌው ከቴዎድሮስ ጸጋዬ ጋር ያስተባበረው “አየር አንቀጥቅጥ” ትዕይንት ቅዳሜ ቀን ተካሂዷል። ልደቱ በስተመጨረሻ እንዳለው ከታሰበው በላይ የተሳካው የአየር ትዕይንት 15 ሰዎች ተናግረዋል፤ ሕዝብ በሳተላይት እና በተገኘው መንገድ ሁሉ ሰምቷል ብሏል። አገዛዙ ፈርቶ ኢንተርኔት አፍኗል፤ ዳታ ታቅቧል፤ ዩትዩብ እንዳይሠራ ተደርጓል ብለው ልደቱም፣ ቴዎድሮስም እየደጋገሙ ሲናገሩ ተሰምተዋል። ይህ የአየር ላይ ትዕይንት “ስልቴዎች” ማለትም ስብሃት፣ ልደቱ፣ ቴዎድሮስ በልዩ ሁኔታ የቀመሩትና ትህነግን በመታደግ ለሻዕቢያ የተሠራ ልዩ የስልቴዎች ስልት ነው። ንግግር ያደረጉት ሰዎች ጥቂቶቹን ስንቃኝ፤ … የድግሱ መሪ ቴዎድሮስ መደረጉ በራሱ ብዙ የሚለው ነገር አለ። ቴዎድሮስ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ወገኖቼን (የትግራይ ተወላጆችን በተለይም ወያኔዎችን) የፈጀች ኢትዮጵያ ጥንቅር … [Read more...] about “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ)
Opinions
የኔ ሃሳብ
በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ
መለስ ዜናዊ ከስሙ ጀምሮ ሁሉ ነገሩ የውሸት ወይም ፌክ ነው። ላደረሰብን ግፍ እንክሰሰው እንኳን ብንል በየትኛው ስሙ ነው ፍርድ ቤት የምናቆመው የነበረው? ደግነቱ ከዚህ ሁሉ በፊት ወደ ዕረፍቱ ሄዶ እኛንም አሳረፈን። መለስ የዕውቀት ችግር አልነበረውም፤ ዕድሜ ለኢትዮጵያ ከሥር መሠረቱ በነጻ አስተምራዋለች። ንጉሡም ሰው ነው፤ ነገ ሀገር ይጠቅማል ብለው ሸልመውታል ይባላል። ግን ያልታከመና ሥር የሰደደ የበታችነት ስሜት የነበረው፣ አስተሳሰቡ ደሃ የሆነ ሰው ነበር። በዚህ ደሃ አስተሳሰቡ ነበር ኢትዮጵያን ለመምራት ሥልጣን ኮርቻ ላይ የተፈናጠጠው። ሥልጣን፣ ሃብት፣ ድሎት፣ ወዘተ ቢመጣም አስተሳሰብ ደሃ ከሆነ ችግሩ ውስብስብና መፍትሔ ዓልባ ነው የሚሆነው። መለስ ኢትዮጵያን በጣም ነበር የሚጠላት፤ ለማፍረስ ይፈልግ ነበር ለማለት ብዙም አያስደፍርም። ነገርግን ልክ እንደ … [Read more...] about በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ
ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት”
የዛሬ አምስት ዓመት ግድም ነው። የሚያምሩ ሁለት ሸበቶ እናቶችን ጨምሮ ተገልጋዮች ይበላሉ። ይጠጣሉ። ያነሳቸውን ይጠይቃሉ። የወቅቱ የኢሳት ባልደረቦችም በአንድ ኮርነር ክብ ሰርተው የሚበላወንም የሚጠጣውንም በዓይነት ሤራ እያዋለዱ ይጠዘጥዛሉ። ቨርጂኒያ ዳማ ሆቴል!! በድንገት ሁለቱ ሸበቶ ሴቶች ይነሱና እንደ ብራቅ ይጮሃሉ። ክብ ሰርተው የሚመገቡትን የኢሳት የማታ ማታ ኮማንዶዎች እያመለከቱ እሳት ጎርሰው “አፈር ብሉ፣ እምዬ ማሪያም አፈር ታብላችሁ፤ ሕዝብ እያጫረሳችሁ እናንተ እዚህ ሥጋ ትቆርጣላችሁ። ደም ብሉ …. ” እናቶቹ ስሜታቸውን መቆጣጠር አቅቷቸው “ያዙኝ ልቀቁኝ” አሉ። ወርውረው ለመማታት ገላጋዮችን ታገሉ። ተለምነው። ተገዝተው …. የገባቸው እናቶች። እንደ እኔ ያልደነዘዙ። “ሦስትን ወደ አራት” አስገራሚ ትርክት፣ አስገራሚ ሤራ ነው። ሤራው በርካቶችን የሰለበ … [Read more...] about ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት”
የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ?
ቴድሮስ አድሃኖም አዲስ አበባ አልመጣም! መሠረተቢሱ መሠረት ሚዲያ! ራሱን “ዓለምአቀፋዊ ጋዜጠኛ” ብሎ በመሰየም ለፈረንጅ ሚዲያ መሥራት እና አገርን መሸጥ፣ ባንዳ መሆንን ጌጡ ያደረገው ኤሊያስ መሠረት ህወሃት/ትህነግ ከመንበሯ ከተነቀለች ጊዜ ጀምሮ በዋንኛነት የያዘው አጀንዳ መርዘኛ ፕሮፓጋንዳውን በ“መረጃ” ስም መትፋት ነው። ከጥቂት ሳምንታት በፊት የፋኖ ትግል መሪ የሆነውን እስክንድር ነጋን ፊት ለፊት በማድረግ “ከመንግሥት ጋር በውጪ ድርድር እንዲደረግ የፋኖ ክንፍ ጠየቀ” ብሎ የሐሰት ወሬ በትኖ ነበር። ይህ ሆን ብሎ የፋኖ ኃይሎችን ለመበታተን እና አንድነት በመካከላቸው እንዳፈጠር ያስወራው ተራ አሉባልታ እንደሆነ ራሱ እስክንድር ወጥቶ ተናግሯል። መሠረተ ቢሱ ኤሊያስ ይህንን መረጃ ካወጣ በኋላ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ “ይህ ሰው ያኔ ለወያኔ እንደሠራ አሁንም ለብልፅግና … [Read more...] about የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ?
ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ
የአማራ ፋኖዎች አንድ እየሆኑ ነው። ሆኖም አሁንም በእስክንድር ነጋ ከሚመራው የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ጋር በተገናኘ የተወሰኑ የፋኖ ወገኖችንም ማሰባሰብም ያስፈልጋል። እነ ኮሎኔል ፋንታሁን፣ እነ ሻለቃ መከታው፣ እነ ሻለቃ ከፍያለው ደሴ፣ እነ ሻለቃ ደረጄ በላይ የመሳሰሉትን። እነዚህ ወገኖች የህዝብ ፋኖዎች እንጂ የግለሰብ ክቡር ዘበኞች ባይሆኑ ጥሩ ነው። ለራሳቸው ሲሉ። ምን አልባት ከእስክንድር ነጋና ለእስክንድር ነጋ ቅርብ የሆኑ፣ በአገር ቤትም በውጭ አገር የሚገኙ፣ የተዛባ መረጃ ስለደረስቸው ይሆናል አሁን የያዙትን አቋም እየያዙ ያሉት። በዚህ ረገድ እነዚህ ወገኖች እውነታውን እንዲያውቁ ማድረግ አስፈላጊ ነው። አሁንም "እስክንድር፣ እስክንድር" የምትሉ ወገኖች በጭፍንና በስሜት ሳይሆን ነገሮች በማስረጃ ማገናዘብ መጀመር አለባችሁ። እስክንድር ነጋ "አሜሪካ መኖር ሲችል … [Read more...] about ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ
ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ?
መግቢያ ሰሞኑን የፋሲል ቤተመንግሥት እድሳት ጉዳይ መነጋገሪያ ሆኗል፤ ምክንያቱ ደግሞ የግንቡ የውጭ ገፅታ ቀለም ከተለመደው ተቀይሮ መታየቱ ነው። ውዝግቡን ተከትሎም በእድሳቱ ስራ ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ ያላቸውም ሆኑ ሌሎች የቅርስ ጥበቃ ባለሙያዎች ምላሾችን ሰጥተዋል። ሆኖም የተሰጡት ምላሾች ውዝግቡን የማቆም አቅም ያላቸው አይመስልም። በፕሮጀክቶች ቅደም ተከተል ላይ ያለንን ጥያቄ ለጊዜው ያዝ እናድርገውና የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የዓለም ቅርስ የሆነው የፋሲል ቤተመንግሥት መታደሱን የሚቃወም የለም። በተለይም ግቢው ውስጥ የተሰራው ላንድስኬፕና ለቱርስቶች የተዘጋጀው የማረፊያ ቦታ በጥሩ ጎኑ የምንመለከተው ነው፤ እንዲሁም የግንቡ መዋቅራዊ ዝንፈቶችን ለማስተካከል የተወሰደው እርምጃም መልካም የሚባል ነው። ሆኖም የብዙዎቻችን ጥያቄና ውዝግብ መንስኤ የሆነው በግንቡ ውጫዊ ገፅታ … [Read more...] about ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ?
ደም ጠጥቶ “አልጸጸትም” – የጃዋር አዲስ መጽሐፍ
ራሱን ከሚገባው በላይ መካብ የማይበቃው ጃዋር ሲራጅ መሐመድ የ21ኛው ክፍለ ዘመን አህመድ ግራኝ ነኝ፤ ተጽዕኖ ፈጣሪ ነኝ፤ “የአማራ ብሔርተኝነት ማነሳሳታችን ትልቁ ስኬታችን ነው”፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለሥልጣን ያበቃሁት እኔ ነኝ፤ የምርጫውን ቀመር (ካልኩሌሽን ሠርቼዋለሁ)፣ ቁርአን ይዤ ዐቢይን ጅማ ላይ እንዳይመረጥ አደርገዋለሁ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ሁለት መንግሥት ነው ያለው - የዐቢይ እና የቄሮ መንግሥት፣ እኔ ከታሰርሁ ኦሮሚያ ድብልቅልቁ ነው የሚወጣው፣ የፖለቲካ ሳይንቲስት ነኝ፣ ብዙ ዕውቀት አለኝ፤ ብዙ ችሎታ አለኝ፤ ወዘተ በማለት ያለማቋረጥ ከመትፋት አልፎ “ተከበብኩኝ፤ ልገደል ነው” የሚል የሃሰት መረጃ በማውጣት፤ ከህወሓት ጋር በመመሳጠር ለመተግበር የሞከረውን ዕቅድ እንደፈለገ የሚነዳውንና ማሰብ የተሳነውን የቄሮ ኃይል በመጠቀም ለማስፈጸም ባደረገው ሙከራ እጅግ በርካቶች በግፍ … [Read more...] about ደም ጠጥቶ “አልጸጸትም” – የጃዋር አዲስ መጽሐፍ
ግንቦት 20 ቀን 1983 ዓ.ም. እና ኢትዮጵያ
ወደ ግንቦት 20ቀን, 1983 ዓ.ም. ከመግባታችን በፊት ትንሽ ወደ ኋላ መለስ በማለት የደርግ ስርዓትን በትንሹ እንቃኘው:: ደርግ የካቲት ወር 1966 ዓ.ም. የዘውድ አገዛዙን ስርዓት በመቃወም በአርሶ አደሩ ፣ በተማሪው ፣ በአስተማሪው ፣ በመንግስት ሰራተኛው ፣ በወዛደሩ ፣ በነጋዴው እና በመለዮ ለባሹ ወዘተ ፣ ወዘተ የተቀጣጠለው ህዝባዊ አመጽ ጊዜ ሳይወስድበት በ6 ወራት ውስጥ የተነሳው ህዝባዊ አመጽ ግቡን መታ:: ህዝባዊ አመጹን የሚመራው የተደረጀ ፓርቲ ባለመኖሩ በር የተከፈተለት መለዮ ለባሽ አመቺ ሁኔታ በማግኘቱ በፍጥነት ተደራጅቶ ከተራ ወታደር ጀምሮ የተለያዩ ማእረግ ያላቸው አባላቱን አስመርጦ ወደ 120 የሚጠጉ ተወካዮቹን አዲስ አበባ በሚገኘው አራተኛ ክፍለጦር አሰባሰበ:: ከጦር ሃይሎች ፣ ከክቡር ዘበኛ እና ከፖሊስ የተውጣጡት እንኚሁ መለዮ ለባሾች በሰኔ … [Read more...] about ግንቦት 20 ቀን 1983 ዓ.ም. እና ኢትዮጵያ
ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ?
የአባይ ግድብን በተመለከተ ዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ የሚያደርግ” ስምምነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲፈርሙ ተጽዕኖ እየተደረጉና ወደ ፊርማውም እየሄዱ ነው የሚል እንደምታ ያለው ዘገባ ባወጣ ጊዜ አንድ የጎልጉል ተከታታይ የዛሬ ሦስት ዓመት ተኩል አካባቢ የአጸፋ ምላሽ ሰጥተው ነበር። በወቅቱ የውሃ ሃብት ባለሙያ መሆናቸውን ጠቅሰው February 6, 2020 “ለዋዜማ ሬዲዮ – የህዳሴውን ግድብ ዜናችሁን ላስተካክልላችሁ” በሚል ርዕስ ምላሻቸውን የጻፉት ግለሰብ ያኔ የጻፉት መጣጥፍ በድጋሚ እንዲወጣላቸውና በወቅቱ ዋዜማ ሬዲዮ አለኝ ያለውን ሰነድ ይፋ እንዲደርግ ጥያቄ አቅርበዋል። ትላንት መከናወኑ ከተነገረለት 4ኛው የውሃ ሙሌት ጋር በተያያዘ ጥያቄውን ማቅረቡ አሳማኝ ሆኖ ስላገኘነው ለሚዲው የጸሐፊውን መልዕክት እያደረስን መጣጥፉን ከዚህ በታች በድጋሚ … [Read more...] about ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ?
ጀብደኛው
አንድ ሽማግሌ የነገሩኝ ታሪክ ትዝ አለኝ። ሰውዬው ጀግና ነኝ፣ አንበሳ በጡጫ ነብርን በእርግጫ እገላለሁ እያለ ይጎርራል። በኋላ ራሱ ደጋግሞ ያወራውን ጉራ እውነት ነው ብሎ ራሱ አመነው። አምኖም አልቀረ በጉራው የተሳቡ፣ በወሬው የተሰባሰቡ፣ አድናቂዎቹን አስከትሎ በረሃ ወረደ። እሱ ጀብድ ሊሠራ ሌላው ጀብድ ሊያወራ፣ ምን ለምን አብረው አዘገሙ። አድናቂዎቹን ከፍ ያለ ኮረብታ ላይ አስቀመጠና "ዛሬ ሶምሶንን በዓይናችሁ ታያላችሁ" አላቸው። እነርሱም አድንቀውና አዳምቀው እንዴት እንደሚያወሩት እያሰቡ ወደ አንበሳ መንጋ የሚወርደውን ጀብደኛ በማዶ ይመለከቱ ያዙ። ወረደ ጀብደኛው። አንበሶች ሰብሰብ ብለው ተኝተዋል። በሩቁ ድንጋይ ወረወረባቸው። ሁሉም አንበሶች ቀና ቀና አሉ። አንዱ በድንጋይ የተመታ ደቦል ዘሎ ወጣበትና በቅጽበት ሌሎች ገነጣጠሉት። ታሪኩም ከጄት ፈጥኖ ከውኃ ቀጥኖ … [Read more...] about ጀብደኛው