ትሕነግ (የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር - ህወሃት) ከ2010 ዓም ለውጥ በኋላ ሦስት መጠነ ሰፊ የተባሉ ወረራዎችን እንደፈጸም ይታወሳል። በእነዚህ ተዋጊዎችን እንደ ማዕበል (human wave) የማሰለፍ ስልት ከራሳቸው አንደበትና የጽሑፍ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት አንድ ሚሊዮን የሚደርሱ የትግራይ ተወላጆች ህይወት አልፏል። የፕሪቶሪያውን የሰላም አማራጭ ስምምነት ተከትሎ በትግራይ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች እና የሽግግር ወቅት ጊዜያዊ አስተዳደሩ በጦርነቱ ወቅት ተሳታፊ ለመሆን ዕድል የተመቻቸለት ሻዕቢያ በትግራይ እህቶች፣ እናቶችና ተወላጆች ላይ የፈጸመው ግፍም የሚዘነጋ አይደለም። ትሕነግ ለውጡን ተከትሎ ወደ ትግራይ ካፈገፈገ በኋላ “የፌዴራሊስት ኃይሎች” ብሎ የፈረሰውን ኢህአዴግ የሚተካ ሌላ አደረጃጀት ፈጥሮ ወደ አራት ኪሎ ለመመለስ የሚያግደው ምንም ኃይል እንደሌለ “ጦርነት … [Read more...] about የጽምዶ ልክፍት
Left Column
አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፣ የአገሪቱ ዲፕሎማቶች በሌሎች አገራት ምርጫዎችና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ አስተያየት ከመስጠት እንዲቆጠቡ የሚደነግገውን መመሪያ ይፋ ካደረገ ቆይቷል። እ.ኤ.አ. በሐምሌ 2025 በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ ተፈርሞ ለሁሉም የአሜሪካ ኤምባሲዎች የተላከው ይህ ይፋዊ መመሪያ፤ አሜሪካ ለረጅም ዓመታት በሌሎች አገራት ምርጫዎች ላይ ስታደርግ የነበረውን የቁጥጥር፣ የክትትልና የትችት ሚና በከፍተኛ ሁኔታ የገደበ ነው። የመመሪያው ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦ የአገራትን ሉዓላዊነት ማክበር፦ መመሪያው የአሜሪካን "ቅድሚያ ለአሜሪካ" (America First) የተሰኘውን መርህ የሚከተል ሲሆን፣ የሌሎችን አገራት ብሔራዊ ሉዓላዊነት ማክበር እንደሚገባና አሜሪካ የራሷን የፖለቲካ አስተሳሰብ በሌሎች ላይ መጫን እንደሌለባት … [Read more...] about አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ
ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ
የፌዴራል ፖሊስ በሪፖርተር ላይ ያወጣው መግለጫ የሪፖርተርንና የባለቤቱን ማንነት እንዲሁም ስሑት ሥራውን ያጋለጠ ነው። እንደ ፌዴራል ፖሊስ መግለጫ ሪፖርተር “ስውር ተልዕኮ የተንፀባረቀበት ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ፈፅሟል”። የመግለጫው ሙሉ ቃል ከዚህ በታች ይገኛል። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሪፖርተር ጋዜጣ “ከፍተኛ ባለስልጣናትና ታዋቂ አርቲስቶች ከ98 ቢሊየን ብር በላይ መዝረፋቸው በኦዲት ምርመራ መረጋገጡ ተነገረ" በሚል የዘገበው መረጃ የተዛባ መሆኑን አስታወቀ ሪፖርተር ጋዜጣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የዘጠኝ ወር የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ለተከበረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና የፍትህ ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ሪፖርቱን ለማስረዳት በማስታወሻነት የተጠቀመበትን ጥቅል መረጃ መነሻ በማድረግ፣ ጠቅላላ ይዘቱን በአግባቡ … [Read more...] about ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ
አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?!
* ለመሆኑ የቴዲ ኢትዮጵያ የት ትሆን ያለችው? ታዋቂው አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) አዲሱን አልበሙን በስምንተኛው ወር፣ በስምንተኛው ቀን፣ በስምንተኛዋ ሰዓት ለመልቀቅ መወሰኑ በቁጥር ስሌት (Gematria) ዙሪያ መነጋጋሪያ አጀንዳ ፈጥሯል። ይህ "888" የተሰኘው ቁጥር በአጋጣሚ የተመረጠ እንዳልሆነና አርቲስቱ ሆን ብሎ መልዕክት ለማስተላለፍ የተጠቀመበት ነው የሚሉ ወገኖችም አሉ። በክርስትና እምነት 777 የመለኮት ቁጥር ሲሆን፣ 666 ደግሞ የባቢሎን፣ የአውሬው ወይም የክርስቶስ ተቃዋሚ ቁጥር ተደርጎ እንደሚወሰድ ሁሉ፣ 888 ምንን ሊወክል ይችላል የሚለው ጥያቄ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል። ከመንፈሳዊ ትርጓሜ አንፃር፣ 888 በግሪክ ቋንቋ የኢየሱስ (Ιησούς) ስም መጠሪያ ሆኖ የሚያገለግልና ከፍጽምና በላይ የሆነን መለኮታዊ ኃይል ወይም አዲስ ጅማሮን … [Read more...] about አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?!
ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ”
መነሻውን አማራ ክልል በማድረግ ወደ አዲስ አበባ ገብቶ ለሽብር ዓላማ ሊውል የነበረ ሕገ ወጥ ጠመንጃና ጥይቶች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ። መነሻውን ከአማራ ክልል ያደረገ ኮድ 3 አ.አ ታርጋ ቁጥር 05299 የሆነ ተሽከርካሪ ሕግ ወጥ 08 ክላሽ፣ 151 የክላሽ ጥይት፣ 17 የብሬን ጥይት እና 07 የክላሽ ካዝና ጭኖ በድብቅ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ለማሳለፍ ሲሞክር ለገጣፎ ኬላ ላይ ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደረገው ጠንካራ ፍተሻ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል። በተመሳሳይ መነሻውን አማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ ያደረገ ኮድ 3 ኢት የታርጋ ቁጥሩ 55426 የሆነ ተሽከርካሪ በእንቁላል ካርቶን ውስጥ 988 የክላሽ ጥይት ደብቆ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ለማሳለፍ ሲሞክር በሱልልታ ኬላ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደረገው ጠንካራ ፍተሻ በቁጥጥር ሥር መዋሉ … [Read more...] about ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ”
የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች
የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢ ስለሆኑት የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶችና የንግድ ተቋማት ሲነሳ ግንኙነታቸው “በሬ ካራጁ” እንደሚሉት ዓይነት መሆኑን መጠቆም ጉዳዩን ምን አልባትም ማሳነስ ካልሆነ በቀር አይበዛም። ምክንያቱም አውሬው ኦሮሚያ ላይ በተቀመጡ የትህነግ ቅምጦች አማካይነት መረጃ እየተቅበለ በተሰጠው የቤት ሥራ መሠረት ኃላፊዎችን እያንገዋለለ ያስጠበጥብ ስለነበር ነው። በዘመነ ት ህነግ ሪፖርተር ኦሮሚያ ላይ የሠራው ሤራና አሻጥር በዚህ አጭር ጽሑፍ የሚገለጽ አይደለም። ትህነግ ኦሮሚያን የተቆጣጠረው በሪፖርተር አማካኝነት ነበር ቢባል ምንም ማጋነን አይሆንም። በኦሮሚያ ላይ የሚከናወኑ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ፣ የኢኮኖሚ ጉዳዮች መረጃ ይጠባ የነበረው ሪፖርተር ነበር። ለምሳሌ፤ ኢህአዴግ ሥልጣን ላይ በነበረ ጊዜ፤ በተዋረድ የተቀመጡ የትህነግ ካድሬዎችና ሰላዮች ጥይት በማቀበል … [Read more...] about የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች
የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ
በ1930ዎቹ የጀርመን ወግ አጥባቂ ልሒቃን በሀገራቸው እያቆጠቆጠ ያለው ኮሙኒዝም አስፈራቸውና አንድ “መላ” ዘየዱ። በሕዝብ ዘንድ ዝና እያገኘ የመጣውን አዶልፍ ሒትለርን ወደ ሥልጣን ማምጣትና ኮሙኒዝምን ድባቅ መምታት። ውሳኔ ተላለፈ፤ ሒትለርም የፓርቲው ካዝና፣ ቁልፍ፣ ወንበር፣ … ሁሉም ተሰጠው። አጅሬውም ወዲያውኑ የራሱን መስተጋብር በመፍጠር ያበላውን ፓርቲ መልሶ መውጋት ጀመረ። የናትዚው “አውሬ” ሒትለር የዴሞክራሲ መዋቅሮችን አፈራረሰ፣ የተቃዋሚ እንቅስቃሴዎችን አገደ፣ የቀድሞ አጋሮቹን በሙሉ አጸዳና ሥልጣኑን በኪሱ አስገባ። ነፍሰበላ አውሬ እየቀለቡ መሆናቸውን ያልተገነዘቡት ወግ አጥባቂዎቹ ባሳደጉት “ውሻ” ተበሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ሒትለር እየተቀለቡ ያሉና አንድ ቀን ሊበሉን ያሰፈሰፉ፤ የበሉበትን ወጭት ሰባሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ያበላቸውን የሚበሉ ወይም ሊበሉ እያደቡ ያሉ … [Read more...] about የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ
ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር?
* የተዘነጋው የኢህአፓ ነጭ ሽብርና የወቅቱ ኢህአፓ አካሄድ ነጭ ሽብርም ሆነ ቀይ ሽብር በቀለም መጠሪያቸው ካልተለያዩ በቀር ሁለቱም ሽብር ናቸው። መስከረም 21 ቀን 1969 ዓ.ም. አዲስ አበባ ሞርጌጅ ህንጻ ውስጥ ትሠራ የነበረችውን ባለቤታቸውን መኪናቸው ውስጥ ሆነው በመጠባበቅ ላይ እያሉ አድብተው ይጠብቁ በነበሩ የኢሕአፓ ነፍሰ ገዳዮች በቅርብ ርቀት በተተኮሰ ጥይት ሕይወታቸው ያለውፈው በወቅቱ በሕዝብ ድርጅት ጉዳይ ጊዜያዊ ጽ/ቤት የጊዜያዊ ጉዳዮች ሰብሳቢ የነበሩት ዶ/ር ፍቅሬ መርዕድ ነጭ ሽብር ከበላቸው ዜጎች አንዱና ነጭ ሽብር ራሱን ያስተዋወቀበት ኦፕሬሽኑ ነው። ሚስታቸውን ጋንዲ ሆስፒታል ጠይቀው ሲወጡ ቀይ መስቀል አካባቢ አድፍጠው ሲጠብቋቸው በነበሩ የኢህአፓ ነፍሰ ገዳዮች የተገደሉት ሌላው ነጭ ሽብር የበላቸው ዜጋ የወቅቱ የኢሰማኮ ሊቀመንበር የነበሩት ተመስገን … [Read more...] about ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር?
የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ
* "እኛ የገባነው ልናፈርሰው ነው" ሕዝቅኤል ገቢሣ በሰላማዊ ትግል መንግሥት ለመጣል ማቀዱን አስታውቆ ሃያ አንድ ቦርድ አባላትን ሰይሞ የሰነበተው የ-አብሮነት ማኅበር ሰባት ሥራ አስፈጻሚዎችን መምረጡ ታወቀ። ማኅበሩ “ለቦርድ አባላት” በሚል ባሰራጨው የ“እንኳን ደስ አላችሁ” መልዕክት አቶ ልደቱ፣ ከአማራ የማኅበሩ ፕሬዚዳንትና ሊቀመንበር ሆነዋል። መቅደስ አዳነ ከወላይታ (ምክትል)፣ አሸናፊ አብርሃም ከደቡብ (ጸሐፊ)፣ ሙሉጌታ ዘለቀ ከአማራ (ገንዘብ ያዥ)፣ የሕዝብ ግንኙነት ኦፊሰር ሕዝቅኤል ገቢሣ /በተለይ እንግሊዘኛና ትግርኛ ጠንቀቀው ስለሚያውቁ/ ከኦሮሞ፣ የድርጅት አስተባባሪ እስማኤል ጎርሴ ከሶማሌ፣ የውጭ ግንኙነት ኦፊሰር መስፍን አየነው ከትግራይ መመረጣቸው ይፋ አድርጓል። ቀደም ሲል ምርጫው ከመደረጉ በፊት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አባላቶች ሕቡዕ እንደሚሆኑ … [Read more...] about የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ
አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው
አምስተርዳም ይካሄዳል ተብሎ በውጭ አገር በሚኖሩ በተለያዩ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች የተሰራጨው የሽግግር መንግሥት ምስረታ ጉባኤ ከአሜሪካ ወደ አምስተርዳም ያመራው አሜሪካ ጥያቄውን ባለመቀበሏ መሆኑ ተሰማ። ስብሰባው ከጀርባው ሆነው የሚመሩትና ሻዕቢያና ሌሎች ፍላጎት ያላቸው የሚታወቁ አካላት እንደሆኑም እየተነገረ ነው። የቀድሞ የትህነግ አመራርና አሁን ላይ “ቪዥን ኢትዮጵያ” ከሚባለው አደረጃጀት ጋር እየሠሩ ያሉት አቶ ግደይ ዘርዓጽዮን በግል የኢሜል አድራሻቸው “ለስብሰባው ተዘጋጁበት” ሲሉ ያሰራጩት ሰነድ ጉባዔው ለምን ወደ አምስተርዳም እንደተዛወረ፣ ወይም አምስተርዳም ለምን እንደተመረጠች አያስረዳም። ይህንኑ አስመልክተን ተጋባዥ ከሆኑት መካከል የአዲስ ሪፖርተር የዋሽንግቶን ተባባሪ ያነጋገራቸው “ቅድሚያ ዕቅዱ ስብሰባውን በአሜሪካ ለማድረግ ነበር፤ ምላሹ ጥሩ ባለመሆኑ ወደ … [Read more...] about አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው








