ራሱን የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) በማለት የሚጠራው ሕገወጥ የወንበዴዎች ቡድን ተክሎብን እና ጥሎብን የኼደው መርዝ እስካኹን አልፋታ ብሎን የመከራ ዘመናችንን አርዝሞታል። ሀገርን በዘር ከፋፍሎ፤ ሕዝብን እንደ ከብት በክልል ወስኖ፤ ኢትዮጵያዊነትን በሰፈርና በወንዝ ወስኖ፤ ለዘመናት አብሮ የኖረን ሕዝብ በጠላትነት እንዲተያይ አድርጓል። እንዳሰበው ባይሳካለትም ሀገራችን ከመፍረስ ድና አኹን ያለችበት ቁመና ላይ ትገኛለች። ትህነግ ግን ነጻ አወጣዋለኹ ብሎ ሲነግድበት የነበረውን ሕዝብ የምድር ሲዖል ውስጥ ጨምሮ እያሰቃየው ይገኛል። ወደ ጉዳያችን ስንመለስ፤ ትህነግ መርዙን ተፍቶብን ወደ ትግራይ ኼዶ ቢመሽግም አሁንም ግን ግድያ፣ ደም ማፍሰስ፣ ማፈናቀል፣ አልቆመም። በሀገሪቱ ላይ የሚፈጽመው ዕልቂት የገፊና ጎታች ሤራ እንደሆነ በተደጋጋሚ ያነሳነው ጉዳይ ነው። ጎልጉል በዚህ … [Read more...] about ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው?
Pull and Push Conspiracy
ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ”
መነሻውን አማራ ክልል በማድረግ ወደ አዲስ አበባ ገብቶ ለሽብር ዓላማ ሊውል የነበረ ሕገ ወጥ ጠመንጃና ጥይቶች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ። መነሻውን ከአማራ ክልል ያደረገ ኮድ 3 አ.አ ታርጋ ቁጥር 05299 የሆነ ተሽከርካሪ ሕግ ወጥ 08 ክላሽ፣ 151 የክላሽ ጥይት፣ 17 የብሬን ጥይት እና 07 የክላሽ ካዝና ጭኖ በድብቅ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ለማሳለፍ ሲሞክር ለገጣፎ ኬላ ላይ ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደረገው ጠንካራ ፍተሻ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል። በተመሳሳይ መነሻውን አማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ ያደረገ ኮድ 3 ኢት የታርጋ ቁጥሩ 55426 የሆነ ተሽከርካሪ በእንቁላል ካርቶን ውስጥ 988 የክላሽ ጥይት ደብቆ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ለማሳለፍ ሲሞክር በሱልልታ ኬላ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደረገው ጠንካራ ፍተሻ በቁጥጥር ሥር መዋሉ … [Read more...] about ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ”
በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት
ካለፉት አራት ወይም አምስት ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ የሚታየው የፖለቲካ መካረርና ጡዘት የሁለትዮሽ የተናበበ የገፊና ጎታች ሤራ (Pull and Push Conspiracy) ነው ለማለት የሚያስችሉ በርካታ ጠቋሚዎች አሉ። የዚህ ሤራ ዓላማ ሕዝብን መስዋዕት በማድረግ መስዋዕትነቱ በሚፈጥረው ቁጭትና ሐዘን ሕዝብን ስሜት ውስጥ በማስገባት ሥርዓት አፍርሶ ሥልጣን ባቋራጭ ለመጨበጥ ያለመ ነው። ለነገሩ ይህ ዓይነት የፖለቲካ አካሄድ አመጽ በተቀላቀለበት መልኩ ሁልጊዜ ባይታይም ሠለጠነ በሚባለው ዓለም የተለመደ አካሄድ ነው። ፓርቲዎች ጎራ ለይተው ይናቆራሉ፣ ይሰዳደባሉ፤ ሚዲያው ጉዳዩን የተካረረ ፖለቲካ ያደርገዋል፤ ደጋፊዎች በስሜት በመነዳት ብዙ ርቀው ይሄዳሉ፤ አታጋይ የተባሉት ፖለቲከኞች ግን አብረው ሲበሉ፣ ሲጠጡ፣ ሲሳሳቁ ይገኛሉ። “የሠለጠነ ፖለቲካ” በማለት ይህንን ድራማ ሚዲያው ሌላ ቅኝት … [Read more...] about በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት



