• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ

May 6, 2026 11:55 pm by Editor Leave a Comment

 የፌዴራል ፖሊስ በሪፖርተር ላይ ያወጣው መግለጫ የሪፖርተርንና የባለቤቱን ማንነት እንዲሁም ስሑት ሥራውን ያጋለጠ ነው። እንደ ፌዴራል ፖሊስ መግለጫ ሪፖርተር “ስውር ተልዕኮ የተንፀባረቀበት ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ፈፅሟል”። የመግለጫው ሙሉ ቃል ከዚህ በታች ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሪፖርተር ጋዜጣ “ከፍተኛ ባለስልጣናትና ታዋቂ አርቲስቶች ከ98 ቢሊየን ብር በላይ መዝረፋቸው በኦዲት ምርመራ መረጋገጡ ተነገረ” በሚል የዘገበው መረጃ የተዛባ መሆኑን አስታወቀ

ሪፖርተር ጋዜጣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የዘጠኝ ወር የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ለተከበረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና የፍትህ ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ሪፖርቱን ለማስረዳት በማስታወሻነት የተጠቀመበትን ጥቅል መረጃ መነሻ በማድረግ፣ ጠቅላላ ይዘቱን በአግባቡ ሳይረዳ እና በተቋሙ ስትራቴጂክ አመራሮች የቀረበውን  ዝርዝር ማብራሪያ መጠቀም እየቻለ እውነታውን ወደ ጎን በመተው ሕዝብን በሚያሳስት መልኩ የተዛባ መረጃ በጋዜጣው የፊት ገፅ ላይ ይዞ ወጥቷል።  

ሪፖርተር ጋዜጣ ከአንድ ቁንፅል ሀሳብ በመነሳት በማይገባ የሒሳብ ስሌት ውስጥ በመግባት 133 ሚሊየን 903 ሺህ 384 ዶላር ወደ ብር በመቀየር እና ከ78 ቢሊየን ብር ጋር በመደመር ከፍተኛ ባለስልጣናትና ታዋቂ አርቲስቶች ከ98 ቢሊየን ብር በላይ ዘርፈዋል በማለት ያሰራጨው ዘገባ ፍፁም የተሳሳተ ነው። 

እውነታው ግን 78 ቢሊየን ብር በየወንጀሉ ዓይነት ሲተነተን፦ 7 ቢሊየን ብር በሙስና ወንጀሎች (ከመዳበሪያ ግዥ እና ከባንክ ማጭበርበር ጋር የተያያዘውን ጨምሮ)፣ 6.4 ቢሊየን ብር በጉምሩክና ታክስ ወንጀሎች (ታክስ ስወራንና የኮንትሮባንድ ወንጀሎችን ጨምሮ)፣ 13.7 ቢሊየን ብር በተደራጁና ልዩ ልዩ ወንጀሎች (ሕገ-ወጥ የሰዎችና የገንዘብ ዝውውር እንዲሁም የማዕድን ዝውውርን ጨምሮ)፣ 44.9 ቢሊየን ብር በፋይናንስ እና ንግድ ነክ ወንጀሎች (ኢትዮጵያውያን እና የውጭ ሀገር ዜጎች የተሳተፉበት ሕገ-ወጥ ሐዋላ፣ የሳይበር ወንጀል፣ የንግድ ነክ ወንጀል በተለይም ከፊንቴክ ድርጅት እና ከአርቲስቶች ጋር በተያያዘ በ1,400 ሰዎች ላይ የደረሰውን 1.7 ቢሊየን ብር ጉዳትን ጨምሮ) እንዲሁም 6 ቢሊየን ብር የሚገመት በሽብርና በሌሎች የተለያዩ ወንጀሎች ላይ ጉዳት ከመድረሱ በፊት ማዳን የተቻለ እና አልፎም በደረሰ ጉዳት ላይም ምርመራ ማጣራቱን በዝርዝር ሪፖርቱ ተመላክቷል።

በተመሳሳይ ለተከበረው ቋሚ ኮሚቴ በቀረበው ሪፖርት ላይ 133 ሚሊየን 903 ሺህ 384 ዶላር ላይ ምርመራ ተጣርቶ ጉዳቱን ማዳን መቻሉ በዝርዝር ተገልጾ እያለ፤ ሪፖርተር ጋዜጣ ግን እንደተዘረፈ አድርጎ ለሕዝብ ያሰራጨው ዘገባ ከእውነታው የራቀና የተዛባ ነው።

ከላይ ከተዘረዘሩት ወንጀሎች ጋር በተያያዘ በ9 ወር ውስጥ የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜጎችን ጨምሮ 1,518 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ ተጣርቶባቸውና ክስ ተመስረቶባቸው ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ ተደርጓል።

እነዚህ ከላይ በዝርዝር የተጠቀሱት ወንጀሎችን በተመለከተ ፖሊስ በየጊዜው የደረሰበትን የምርመራ ውጤት ለሕዝብ ሲያሳውቅ እንደነበር ይታወቃል።

እውነታው ይሄ ሆኖ ሳለ የሪፖርተር ጋዜጣ መረጃውን በትክክል ለህዝብ ማድረስ ሲገባው አዲስ ነገር እንደተፈጠረ እና ኀብረተሰቡ እንደ ተዘረፈ አድርጎ ከጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባር ያፈነገጠና የጋዜጣው ስውር ተልዕኮ የተንፀባረቀበት ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ፈፅሟል።

በመሆኑም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሐሰተኛና የተዛባ መረጃ በማሰራጨት ኃላፊነት የጎደለው ተግባር የፈጸመውን ሪፖርተር ጋዜጣን በሕግ አግባብ የሚጠይቅ መሆኑን አስታውቋል።

‎የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፥ ‎አዲስ አበባ፥ ሚያዚያ 27 ቀን 2018 ዓ.ም

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Slider Tagged With: Amare Aregawi, ethiopian terrorists, federal police, operation dismantle tplf, Reporter, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule