በ1930ዎቹ የጀርመን ወግ አጥባቂ ልሒቃን በሀገራቸው እያቆጠቆጠ ያለው ኮሙኒዝም አስፈራቸውና አንድ “መላ” ዘየዱ። በሕዝብ ዘንድ ዝና እያገኘ የመጣውን አዶልፍ ሒትለርን ወደ ሥልጣን ማምጣትና ኮሙኒዝምን ድባቅ መምታት። ውሳኔ ተላለፈ፤ ሒትለርም የፓርቲው ካዝና፣ ቁልፍ፣ ወንበር፣ … ሁሉም ተሰጠው። አጅሬውም ወዲያውኑ የራሱን መስተጋብር በመፍጠር ያበላውን ፓርቲ መልሶ መውጋት ጀመረ። የናትዚው “አውሬ” ሒትለር የዴሞክራሲ መዋቅሮችን አፈራረሰ፣ የተቃዋሚ እንቅስቃሴዎችን አገደ፣ የቀድሞ አጋሮቹን በሙሉ አጸዳና ሥልጣኑን በኪሱ አስገባ። ነፍሰበላ አውሬ እየቀለቡ መሆናቸውን ያልተገነዘቡት ወግ አጥባቂዎቹ ባሳደጉት “ውሻ” ተበሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ሒትለር እየተቀለቡ ያሉና አንድ ቀን ሊበሉን ያሰፈሰፉ፤ የበሉበትን ወጭት ሰባሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ያበላቸውን የሚበሉ ወይም ሊበሉ እያደቡ ያሉ … [Read more...] about የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ
Amare Aregawi
ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ
የትህነግ ልዩ ዓላማ እየተተገበረ ያለበትን የአማራ ክልል ቀውስ ለማስታገስ የወጣው የአስቸኳይ አዋጅ ከመጽደቁ በፊት ሪፖርተር ጋዜጣ የድምጽ ስሌት አቅርቦ የአማራ ብልጽግና ከዋናው ብልጽግና የተለየ አቋም እንዲይዝ የቢሆን ስሌትና ምኞት ያለበት ዜና አሰራጨ። አብንና ኢዜማንም ደምሯል። ምንም እንኳን በሪፖርትር ስሌትና "የቢሆንልኝ" ምልከታ የድምጽ መመጣጠን ሊፈጠር የሚችልበት አጋጣሚ ሊታሰብ እንደማይችል የገለጹ እንደሚሉት፣ የዜናው ምኞትና አቅጣጫ ትህነግ የሚከተለውን "በብሄር አስብ" የሚለውን ርዕዮት የሚያንጸባርቅና አማራ ክልል በዚህ ቀጥሎ በሁከት ሲናጥ ትህነግ የከሰራቸውን ኪሳራዎች መልሶ እንዲያገኝ ለሚያደርገው ዝግጅት መንገድ ለመጥረግ እንደሆነ አመልክተዋል። "... በሚኒስትሮች ምክር ቤት የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክር ቤቱ በሁለት ሦስተኛ ድምፅ ማፅደቅ … [Read more...] about ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ


