የቀረቡ ጥያቄዎች በጥቅሉ፤ ከኦነግ ሸኔ፣ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ፣ከሰሜኑ የሰላም ስምምነት፣ከዜጎች መፈናቀልና ግድያ፣ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ ስለተከለከሉ ዜጎች፣አርሶ አደሩ ምርቱን ለመሸጥ ከመቸገሩ ጋር በተያያዘ፣ወደ አዲስ አበባ ምርት እንዳይገባ ከመከልከሉ ጋር፣ከክልሎች የርስ በርስ መናበብ አለመቻል፣የሱዳን ወታደሮች ወረው የያዙትን የኢትዮጵያ መሬትና ያወደሟቸውን ንብረቶች የተመለከቱ ጥያቄዎች ቀርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች‼️ ሰላምና መረጋጋት* የአገራችን የሰላምና መረጋጋት አሁን ያለው ከነበርንበት የተሻለ ነው፤ወደተሟላ ሰላም ለመሄድ በጣም በርካታ ስራ ይጠበቅብናል፤ … [Read more...] about አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም
Slider
“ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን
የፍትህ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ በዛሬው የምክር ቤት ልዩ ስብሰባ ወቅት ፤ "የሰላም ስምምነቱ ቀሪ ጉዳዮች ቢኖሩም ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል" ሲሉ መናገራቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል። ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት በአብላጫ ድምፅ ተሰርዟል። ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ / ህወሓት / ከሽብርተኛ ድርጅትነት በተሰረዘበት የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ልዩ ስብሰባ ላይ 280 የፓርላማ አባላት ተገኝተው ነበር። 61 የፓርላማ አባላት ተቃውመው ድምፅ ሰጥተዋል ከተገኙት የፓርላማ አባላት መካከል 61 የፓርላማ አባላት ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት መሰረዙን ተቃውመው ድምፅ ሰጥተዋል። 5 የፓርላማ አባላት ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል። በዚህም በአብላጫ_ድምፅ ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት ይነሳ የሚለው … [Read more...] about “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን
በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ
ከለውጥ ወዲህ መላው የኢትዮጵያ ክፍል ሲታመስ ሰላሙ ተጠብቆ የነበረው በትግራይ ነበር። በአገሪቷ ውስጥ እየተከሰተ ያለው የሰላም መታጣት ያሳሰባቸው እናቶች ወደ ተለያዩ ክልሎች ሄደው ስለ ሰላም ሲማጸኑ ቆይተው ትግራይ ሲደርሱ የተነገራቸው እነርሱንም ያስደመመ ነበር። በወቅቱ ከታቦት እኩል ለአምልኮ የደረሰው ደብረጽዮን የመለሰላቸው በትግራይ ሰላም ነው፤ ሰው ወጥቶ ይገባል፤ ሰላም የታጣው በሌላ ክልል ነው፤ እዚያ ሄዳችሁ ብታለቅሱ ይሻላል ነበር ያላቸው። ሌላው የአገሪቱ ክልል ቀውስ ውስጥ መግባት ዋናው መሪ እና ግጭት ቀማሚ ህወሓት መሆኑን የካደ ግብዝነት የተሞላበት ምላሽ ነበር። እጅግ ከፍተኛ የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ፣ የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ያለችው ትግራይ እስካሁን ድምጽ ሳይሰማባት ቆይቶ ዛሬ በተቃውሞ ስትናወጥ ውላለች። በጦርነቱ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው በመለስ ዜናዊ አነጋገር … [Read more...] about በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ
የኢትዮጵያ ወርቅ የት ገባ?
ኢትዮጵያ ባለፉት ሶስት ወራት የወርቅ ምርት “በከፍተኛ መጠን” መቀነሱን የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ይናገር ደሴ ተናገሩ። የባንኩ ገዢ በሀገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ምክንያት ጥብቅ የፊስካል እና የገንዘብ ፖሊስ መከተል አለመቻሉን ገልጸዋል። ዶ/ር ይናገር ይህን ያሉት የብሔራዊ ባንክን የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ እና የሩብ ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት፤ ለፓርላማ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ ሐሙስ ህዳር 29 ባቀረቡበት ወቅት ነው። የባንኩ ገዢ በዚሁ ሪፖርታቸው፤ በሩብ ዓመቱ የነበረውን የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሁኔታ ዳስሰዋል። የሩብ ዓመቱ የወጪ ንግድ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር “መጠነኛ ጭማሪ” ማሳየቱን ያነሱት ዶ/ር ይናገር፤ ገቢው “በተወሰኑ ዘርፎች ላይ” የተገኘ መሆኑን ጠቁመዋል። ሀገሪቱ ላገኘችው ገቢ “ከፍተኛውን ድርሻ” የያዙት አበባ እና ቡና መሆናቸውን … [Read more...] about የኢትዮጵያ ወርቅ የት ገባ?
ሌባ እንዲይዝ ተሹሞ የነበረው ሌባ ሆኖ ተያዘ
የፖለቲካው መዋቅር ውስጥ ያሉትን ሌቦች የመያዙ ተግባር ይጠናከር የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ በቀለን ጨምሮ በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፍትህ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ተናገሩ። ይህ የተገለፀው በቅርቡ የተቋቋመው የፀረ ሙስና ብሔራዊ ኮሚቴ ስራውን በይፋ መጀመሩን አስመልክቶ የኮሚቴው አባላት ዛሬ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው። በአዲስ አበባም የአርሶ አደር ልጆች ወይም የልማት ተነሽ ሳይሆኑ የሆኑ በማስመሰል በሐሰት ሙስና የሰሩ ግለሰቦችም ተለይተዋል ብለዋል የብሔራዊ ኮሚቴው አባል ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ። 175 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታና የኮንዶሚኒየም ቤት ምዝበራ የፈፀሙ እንዲሁም በፍትህ ዘርፉ ስልጣናቸውን በመጠቀም ከግለሰቦችና ከንግድ ተቋማት ጋር ለግል ጥቅማቸው ሲሰሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎችም … [Read more...] about ሌባ እንዲይዝ ተሹሞ የነበረው ሌባ ሆኖ ተያዘ
“ከሩቁ የሚፈራ የመከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል”
ሳይዋጋ የሚያሸንፍ ጠንካራ የመከላከያ ሰራዊት እየገነባን ነው የመከላከያ ሠራዊት ቀንን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ "የጥንካሪያችን ምንጭ ሕዝባችን ነው" በሚል መልዕክት የፓናል ውይይት ተካሄደ። በመርሃ ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር አብርሐም በላይ (ዶክተር)፣ አሁን በኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ግንባታ ከፍተኛ አቅም ተፈጥሯል፤ ከሩቁ የሚፈራ መከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ጠላቶች ሳንቆም ሊጥሉን ሞክረዋል፤ አሁን ቆመን ማንም ሊነቀንቀን የማይችልበት ደረጃ ደርሰናል ያሉት ሚኒስትሩ፣ በአሁኑ ጊዜ ሳይዋጋ የሚያሸንፍ ሠራዊት መገንባት መቻሉን አንስተዋል። ኢትዮጵያ የግዛት አንድነቷ በማንም እንደማይሸረፍ በመስዋዕትነት የሚያረጋግጥ ጀግና ወታደር ያላት ሀገር እንደሆነች የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ይህን በተግባር እያረጋገጠ … [Read more...] about “ከሩቁ የሚፈራ የመከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል”
ከ፴ ዓመት በኋላ በሰፈሩት ቁና መሰፈር እንደ ትህነግ
አደራውን ለባለ አደራው ሰጥተው የልማት ሥራዎችን እየተዘዋወሩ የሚመለክቱትና የአረንጓዴ ዘመቻ መመሪያ እየሰጡ ያሉ ዐቢይ አሕመድ ከአዲሱ ዓመት ጀምሮ የወትሮ ጭንቀትና ያለመመቸት ስሜት ፊታቸው ላይ አይታይም። በመንግሥት የዘመኑ ዕቅድ ላይም በተያዘው ዓመት አስተማማኝ ሰላም እንደሚሰፍን ተመልክቷል። ዐቢይ አህመድ ለበዓላት ባስተላለፉት መልዕክቶቻቸውና በፕሮጀክት ምረቃ ላይ “አትጠራጠሩ የሰሜኑ ጦርነት ያበቃል” ብለዋል። “አሁን” ሲሉ መረጃ የሰጡ ወገኖች “አሁን የሰኞው ንግግር ልክ እንደ 1991ዓም (እኤአ) ድርድር ዋጋ የለውም። ምክንያቱም የትህነግ አመራሮች ጊዜ የሚፈጁበት አንዳችም የድርድር ቀብድ የላቸውም”። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ቴድሮስ አድሃኖም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ደውሎ መማጸኑ ተሰምቷል። ምላሽም አግኝቷል። ከመቀሌ ውጪ ቀሪዋ ትልቅ ከተማ አዲግራትና አድዋ … [Read more...] about ከ፴ ዓመት በኋላ በሰፈሩት ቁና መሰፈር እንደ ትህነግ
“ትህነግን ለማጥፋት የሚደረግ ማንኛውም ነገር ቅዱስ ነው”
የትህነግ 10 በደሎች - በተለይ በአማራ ሕዝብ! "ትህነግ"... (ትግራይ/ተጋሩ አላልሁም) የተሸነፈው በ1967 ነው። ማንም ቡድን ወይም ርዕዮተ አለም ሕዝብን ጠላት አድርጎ ማሸነፍ አይችልም። ግለሰቦች፣ የፊውዳሉ ስርዓት ጠላት ሊሆን ይችላል። ሁሉም አማራ ግን ጠላት ሊሆን አይችልም። ትህነግ እንጂ የትግራይ ሕዝብ ጠላት እንዳልሆነው ሁሉ። የትህነግ መሠረታዊ ትርክት (ድርሰት) በገሃድ የተተወነው ባለፈው ዓመት ነው። ትህነግ በተለይ በአማራ ሕዝብ 10 ዐበይት በደሎች ፈፅሟል። በእኔ ሚዛንና ምልከታ። 1) መልክዓምድራዊ ለውጥ (Demographic Change): ድህረ 1983 ማንነትን ባላገናዘበ መልኩ ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ዋግና ራያ ላይ መሬቱን በመውረር ሰዎችን አፈናቅሎል፣ ጅምላ ግድያ ፈፅሟል። ሴቶችን በመድፈርና አስገድዶ በማግባት የዲሞግራፊ … [Read more...] about “ትህነግን ለማጥፋት የሚደረግ ማንኛውም ነገር ቅዱስ ነው”
“አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”
በአሜሪካ ኦሪጎን ጠቅላይ ግዛት እየተካሄደ ባለው የሰሞኑ የአትሌቲክስ ኢትዮጵያ እንደገና ስሟ ከፍ ብሏል። በፖለቲካው የሚታየው መከፋፈልና ጥላቻ በስፖርቱ አከርካሪውን ተመትቷል። የዚህ ድል ምንጭ ምንድነው? ብለን ወደ ኋላ እንድናይ ያስገድደናል። ተወዳዳሪ የሌለው ወደፊትም የማይኖረው የጀግኖቹን ጀግና አበበ ቢቂላ ማስታወስ የግድ ይላል። አበበ ሮም ላይ በባዶ እግሩ ሲያሸንፍ የዓድዋ ድል ነው በድጋሚ የተበሰረው። ጣሊያኖቹም ይህንን አልካዱም። የክብር ዘበኛው ወታደር አበበ ሲያሸንፍ “ሮምን የወረረ ኢትዮጵያዊ” ብለው ዘግበውለታል። “ጣሊያን ኢትዮጵያን ለመውረር ግዙፍ ጦር አዝምቶ ነበር፤ ሮምን ለመውረር ግን አንድ ኢትዮጵያዊ ወታደር ብቻ በቂ ሆኗል” በማለትም አትተዋል። እነ ማሞ ወልዴና እነባሻዬ ፈለቀ “ኢትዮጵያ” የሚል ቱታ ለብሰው ሲያይ ለአገሩ ተሰልፎ ስሟን ማስጠራት … [Read more...] about “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”
ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው
በተለይ ምዕራብ ወለጋን ምሽጉ አድርጎ ከትህነግ ጋር በመሆን ንጹሐንን እየጨፈጨፈ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚሞክረው ሸኔ ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ መሆኑ ተነገረ። ሸኔን የማጽዳት ዘመቻው ወደ ፖለቲካውና መንግሥታዊ መዋቅሩም ውስጥ በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ተጠየቀ። ጎልጉል ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸው ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በአሁኑ ጊዜ በተጠናከረ ሁኔታ በሸኔ ላይ እየተካሄደ ባለው ዘመቻ ኦነግ ሸኔ ጠንካራ የሚላቸውን ይዞታዎቹን ሳይወድ በግዱ እንዲለቅ እየተደረገ ነው። በተለይ በቅርቡ በምዕራብ ወለጋ በንጹሐን ወገኖቻችን ላይ አሰቃቂና ለኅሊና የሚሰቀጥጥ ግድያ በፈጸመው ሸኔ ላይ አሁን ዝርዝሩን መናገር የማያስፈልግ ዘመቻ እየተካሄደበት ይገኛል። በቀጣይ ባሉት ቀናት መንግሥት በይፋ ዝርዝሩን የሚያሳውቅ ቢሆንም ዘመቻው በዋንኛነት ትኩረት ያደረገው የሸኔን ጠንካራ ምሽጎችን … [Read more...] about ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው