“ባለፉት 50 ዓመታት የተከሰቱት ጦርነቶች የተጀመሩት ሚዲያው ባስተጋባው ውሸት መሆኑን ደርሼበታለሁ” ጁሊያን አሳንዥ፤ የዊኪሊክስ መሥራች። የአገራችን ሚዲያ አውታሮች በተለይም የግሉ ሚዲያ የሚባሉትና በ1997 ምርጫ ወቅት የነበሩት በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ እንዲቀጭጭ፣ የሃሳብ ልዩነት እንዳያድግ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና አመራሮች ጉያ ሥር ገብተው የፈጸሙት ወንጀል የሚያስጠይቅ ነው። ለቀጣዩ ትውልድ መማሪያ ይሆን ዘንድ በወጉ ተጠንቶና ተሰንዶ ሊቀመጥ ይገባል። ምክንያቱም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በተደጋጋሚ ሲከሰት ያየነው ፖለቲካው ወይም ፓርቲዎች ሚዲያውን አጀንዳ እያስያዙ ሲመሩት ይቆዩና በኋላ ፖለቲከኞቹ እርስበርስ ሽኩቻ ውስጥ ሲወድቁ የሚፈልጉትን ለማጥቃት ወይም በሐሰት ለመወንጀልና ፕሮፓጋንዳ ለመንዛት ሲሉ ለሚዲያ ባለቤቶቹ ባሪያና ተገዢ በመሆን እነርሱ ሚዲያውን መምራት ሲገባቸው … [Read more...] about ቀጣዩ የዳያስፖራ ፖለቲካና የሚዲያው አሰላለፍ
Slider
የትግራይ ኢንዱስትሪ ቢሮ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት ማረጋገጫ ሰጠ
* በ“ጋዜጠኛነት” ስም የሚፈጸመው የሚዲያ ሸፍጥ በትግራይ ክልል "ከ200 በላይ ኢንዱስትሪዎች ሥራ ጀምረዋል" በሚል ፓርላማ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበው ሪፖርት "ከእውነት የራቀ ነው" ሲሉ የከሰሱት የትግራይ ክልል ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ 212 ኢንዱስትሪዎች ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ሥራ እንዲጀመሩ ክስ ባቀረቡበት ዜና ጎን ለጎን አስታወቁ። ዜናው የክስ ሳይሆን አሃዱና ቲክቫህ በቅብብሎሽ አንዱ ሌላውን ዋቢ አድርገው ባሰራጩት ዜና መግቢያና ርዕስ ቀዳሚ ያደረጉት "ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በፓርላማ ያቀረቡት ሪፖርት ከዕውነት የራቀ ነው" በሚል ነው። ዜናው በመሪ ርዕሱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ የቀረበውን ክስ አላብራራም፣ እርሳቸው ካሉት ጋርም አላነጻጸረም። የትግራይ ኢንዱስትሪ ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ መሐሪ ገብረሚካኤል "በአሁኑ ወቅት በክልሉ ሥራ የጀመሩት ለትላልቅ … [Read more...] about የትግራይ ኢንዱስትሪ ቢሮ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት ማረጋገጫ ሰጠ
ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ
የትህነግ ልዩ ዓላማ እየተተገበረ ያለበትን የአማራ ክልል ቀውስ ለማስታገስ የወጣው የአስቸኳይ አዋጅ ከመጽደቁ በፊት ሪፖርተር ጋዜጣ የድምጽ ስሌት አቅርቦ የአማራ ብልጽግና ከዋናው ብልጽግና የተለየ አቋም እንዲይዝ የቢሆን ስሌትና ምኞት ያለበት ዜና አሰራጨ። አብንና ኢዜማንም ደምሯል። ምንም እንኳን በሪፖርትር ስሌትና "የቢሆንልኝ" ምልከታ የድምጽ መመጣጠን ሊፈጠር የሚችልበት አጋጣሚ ሊታሰብ እንደማይችል የገለጹ እንደሚሉት፣ የዜናው ምኞትና አቅጣጫ ትህነግ የሚከተለውን "በብሄር አስብ" የሚለውን ርዕዮት የሚያንጸባርቅና አማራ ክልል በዚህ ቀጥሎ በሁከት ሲናጥ ትህነግ የከሰራቸውን ኪሳራዎች መልሶ እንዲያገኝ ለሚያደርገው ዝግጅት መንገድ ለመጥረግ እንደሆነ አመልክተዋል። "... በሚኒስትሮች ምክር ቤት የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክር ቤቱ በሁለት ሦስተኛ ድምፅ ማፅደቅ … [Read more...] about ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ
በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ
ከአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ያከናወናቸውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ተግባራት ገምግሟል፡፡ የዕዙ የመጀመሪያ ምዕራፍ ዕቅድ በባሕር ዳር፣ ደብረ ማርቆስ፣ በደብረ ብርሃን፣ በላሊበላ፣ በጎንደርና በሸዋ ሮቢት አካባቢ የተሰባሰበውን በዘረፋ እና በጥፋት የተሰማራ ቡድን በመምታትና ከተሞቹን ወደ ሰላማዊ ሁኔታ መመለስ ነበር። እነዚህ አካባቢዎች የተመረጡት ብዙ ሕዝብ የሚኖርባቸው፣ ከፍተኛ የንግድና የቱሪስት እንቅስቃሴ ያለባቸው፣ የፖለቲካና የኢንዱስትሪ ማዕከላት በመሆናቸው ነው። በዚህ መሠረት በስድስቱ ከተሞች ዙሪያ የመጣው የጥፋት ቡድን መሣሪያውን እንዲያስረክብና እጁን እንዲሰጥ የተሰጠውን ዕድል ባለመጠቀሙ እርምጃ ተወስዶበታል፣ የሕግ የበላይነትም እንዲከበር ተደርጓል። የክልሉ ሕዝብ በዚህ ዘራፊ ቡድኑ … [Read more...] about በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ
ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ
በመንግሥትና በኦነግ ሸኔ ወይም ኦነግ መካከል ሲካሄድ የከረመው የመጀመሪያ ምዕራፍ የተባለ ንግግር መጠናቀቁን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የደኅንነት አማካሪ ሬድዋን ሑሴን ቅድሚያ ወስደው ይፋ አድርገዋል። የጎልጉል ታማኝ የመረጃ አቀባዮች እንደሰሙት መንግሥት “አልቀበልም” ያለውና ያላስማማው ጉዳይ ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ ያቀረበው ጥያቄ ዋናው ነው። ከመንግሥት ተደራዳሪዎች በኩል ቃል በቃል ምን ምላሽ እንደተሰጠ ባይገልጹም ዜናውን ያቀበሉን እንዳሉት ከሆነ መንግሥትም ሆነ አቀራራቢዎቹ አካላት በዚህ ጉዳይ ላይ የያዙት አቋም ተመሳሳይ ሆኗል። ጥያቄው ሚዛን የሚደፋና አሁን ላይ ሊነሳ የማይችል እንደሆነ ቀደም ሲል የኦነግ ከፍተኛ አመራር የነበሩ ማስታወቃቸው የሚታወስ ነው። የኦፌኮው ሊቀመንበር መረራ ጉዲና ገና ከጅምሩ ኦነግን በሚቃወሙት አፍላ ጊዜያቸው “ኦሮሞ … [Read more...] about ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ
በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው
ጦርነት ባሕላችን ነው፣ ተራራ ያንቀጠቀጠ ትውልድ፣ ወዘተ በሚሉ ባዶ ዲስኩሮችና ከንቱ ልፈፋዎች ትውልድን በስሁት ትርክት ሲነዳ የኖረው ትህነግ የሚፈራው ጥያቄ እየቀረበለት ነው። "ልጆቻችን የት ናቸው?" "ልጆቻችንን መልሰን ማግኘት እንፈልጋለን" ወዘተ የሚሉ የወላጆች ጥያቄ በትግራይ እየተሰማ ነው። አቶ ገብረመስቀል አበበ የተባሉት ሌላኛው ነዋሪም የአንድ ወንድ ልጅ አባት ሲሆኑ “ከአንድ ቤት አንድ ሰው ወደ ጦርነት መግባት አለበት፣ ካልሆነ እርዳታ አይሰጠውሙ” በተባለ ጊዜ አንዱ ልጃቸው በግዳጅ ወደ ውጊያ ማምራቱን በሀዘን ድባብ ውስጥ ሆነው ነግረውናል። አሁን በተደረሰው ስምምነት መሰረት “ልጄ ከዛሬ ነገ ይመጣል እያልኩ በሀዘንና በተስፋ እገኛለሁ” የሚሉት አቶ ገብረመስቀል ልብ በሚሰብር ሁኔታ እያለቀሱ ልጄ ካለ መንግስት ምላሽ ይስጠኝ ሲሉ … [Read more...] about በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው
በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ
ከለውጥ ወዲህ መላው የኢትዮጵያ ክፍል ሲታመስ ሰላሙ ተጠብቆ የነበረው በትግራይ ነበር። በአገሪቷ ውስጥ እየተከሰተ ያለው የሰላም መታጣት ያሳሰባቸው እናቶች ወደ ተለያዩ ክልሎች ሄደው ስለ ሰላም ሲማጸኑ ቆይተው ትግራይ ሲደርሱ የተነገራቸው እነርሱንም ያስደመመ ነበር። በወቅቱ ከታቦት እኩል ለአምልኮ የደረሰው ደብረጽዮን የመለሰላቸው በትግራይ ሰላም ነው፤ ሰው ወጥቶ ይገባል፤ ሰላም የታጣው በሌላ ክልል ነው፤ እዚያ ሄዳችሁ ብታለቅሱ ይሻላል ነበር ያላቸው። ሌላው የአገሪቱ ክልል ቀውስ ውስጥ መግባት ዋናው መሪ እና ግጭት ቀማሚ ህወሓት መሆኑን የካደ ግብዝነት የተሞላበት ምላሽ ነበር። እጅግ ከፍተኛ የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ፣ የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ያለችው ትግራይ እስካሁን ድምጽ ሳይሰማባት ቆይቶ ዛሬ በተቃውሞ ስትናወጥ ውላለች። በጦርነቱ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው በመለስ ዜናዊ አነጋገር … [Read more...] about በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ
የኢትዮጵያ ወርቅ የት ገባ?
ኢትዮጵያ ባለፉት ሶስት ወራት የወርቅ ምርት “በከፍተኛ መጠን” መቀነሱን የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ይናገር ደሴ ተናገሩ። የባንኩ ገዢ በሀገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ምክንያት ጥብቅ የፊስካል እና የገንዘብ ፖሊስ መከተል አለመቻሉን ገልጸዋል። ዶ/ር ይናገር ይህን ያሉት የብሔራዊ ባንክን የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ እና የሩብ ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት፤ ለፓርላማ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ ሐሙስ ህዳር 29 ባቀረቡበት ወቅት ነው። የባንኩ ገዢ በዚሁ ሪፖርታቸው፤ በሩብ ዓመቱ የነበረውን የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሁኔታ ዳስሰዋል። የሩብ ዓመቱ የወጪ ንግድ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር “መጠነኛ ጭማሪ” ማሳየቱን ያነሱት ዶ/ር ይናገር፤ ገቢው “በተወሰኑ ዘርፎች ላይ” የተገኘ መሆኑን ጠቁመዋል። ሀገሪቱ ላገኘችው ገቢ “ከፍተኛውን ድርሻ” የያዙት አበባ እና ቡና መሆናቸውን … [Read more...] about የኢትዮጵያ ወርቅ የት ገባ?
ሌባ እንዲይዝ ተሹሞ የነበረው ሌባ ሆኖ ተያዘ
የፖለቲካው መዋቅር ውስጥ ያሉትን ሌቦች የመያዙ ተግባር ይጠናከር የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ በቀለን ጨምሮ በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፍትህ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ተናገሩ። ይህ የተገለፀው በቅርቡ የተቋቋመው የፀረ ሙስና ብሔራዊ ኮሚቴ ስራውን በይፋ መጀመሩን አስመልክቶ የኮሚቴው አባላት ዛሬ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው። በአዲስ አበባም የአርሶ አደር ልጆች ወይም የልማት ተነሽ ሳይሆኑ የሆኑ በማስመሰል በሐሰት ሙስና የሰሩ ግለሰቦችም ተለይተዋል ብለዋል የብሔራዊ ኮሚቴው አባል ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ። 175 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታና የኮንዶሚኒየም ቤት ምዝበራ የፈፀሙ እንዲሁም በፍትህ ዘርፉ ስልጣናቸውን በመጠቀም ከግለሰቦችና ከንግድ ተቋማት ጋር ለግል ጥቅማቸው ሲሰሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎችም … [Read more...] about ሌባ እንዲይዝ ተሹሞ የነበረው ሌባ ሆኖ ተያዘ
“ከሩቁ የሚፈራ የመከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል”
ሳይዋጋ የሚያሸንፍ ጠንካራ የመከላከያ ሰራዊት እየገነባን ነው የመከላከያ ሠራዊት ቀንን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ "የጥንካሪያችን ምንጭ ሕዝባችን ነው" በሚል መልዕክት የፓናል ውይይት ተካሄደ። በመርሃ ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር አብርሐም በላይ (ዶክተር)፣ አሁን በኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ግንባታ ከፍተኛ አቅም ተፈጥሯል፤ ከሩቁ የሚፈራ መከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ጠላቶች ሳንቆም ሊጥሉን ሞክረዋል፤ አሁን ቆመን ማንም ሊነቀንቀን የማይችልበት ደረጃ ደርሰናል ያሉት ሚኒስትሩ፣ በአሁኑ ጊዜ ሳይዋጋ የሚያሸንፍ ሠራዊት መገንባት መቻሉን አንስተዋል። ኢትዮጵያ የግዛት አንድነቷ በማንም እንደማይሸረፍ በመስዋዕትነት የሚያረጋግጥ ጀግና ወታደር ያላት ሀገር እንደሆነች የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ይህን በተግባር እያረጋገጠ … [Read more...] about “ከሩቁ የሚፈራ የመከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል”