• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ

April 29, 2026 02:27 pm by Editor Leave a Comment

* ዳያስፖራው ራሱን ከትግሉ እያገለለ ነው 

ከሚያዚያ 6 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ በተደረገ ተከታታይ ስምሪት የፋኖ ኃይል እጅግ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ተገለጸ። በተለይ በራያ ቆቦ ወረዳ የተደረገው ሥምሪት ባካባቢው በሚገኘው የፋኖ ኃይል የደረሰው ጉዳት መጠነ ሰፊ እንደሆነ ተመልክቷል። በፋኖ ተስፋ የቆረጠው ዳያስፖራ ከሚኖርበት ሀገር የገጠመው ችግር ተጨምሮ ለፋኖ የሚሰጠውን ድጋፍ እየቀነሰ ነው።

እስከ ዛሬ ድረስ በራያ ቆቦ ወረዳ በአማያ፣ በባይባዋ፣ በፀበለት እና አካባቢው በተደረገው ተከታታይ ስምሪት የመከላከያ ሠራዊት በፋኖ ላይ ባደረሰው ከፍተኛ ምት ንብረቱን፣ ትጥቁን እና ተተኳሹን በመተው ከአካባቢው ሲለቅቅ የሰሜን ምስራቅ ዕዝ 802ኛ ኮር አካል የሆነው 48ኛ ክፍለ ጦር በተጠቀሱት ቦታዎች እና ልዩ ሥፍራው “አካምባ” በሚባል ቦታ ፈጥኖ በመድረስ የፋኖው ኃይል ጥሎት እና አንጠባጥቦት የሸሸውን ንብረት በቁጥጥር ሥር አውሏዋል።  

በዚህም መሠረት፦

የ82 ሚ/ሜ ሞርተር ጥይት – 515

የ82 ሚ/ሜ ሞርተር ፊውዝ – 520

የ82 ሚ/ሜ ሞርተር ካምሱር – 43

የ12.7 ሚ/ሜ ዶሽቃ ጥይት – 818

የመትረዬስ/ብሬን ጥይት – 47080

ቆመህ ጠብቀኝ መሣሪያ – 48

የተተካይ ክላሽ ብሬን – 1

የኤኬኤም ክላሽ ማፅጃ – 137 የተገኘ መሆኑን መረጃው ይጠቁማል።

ከውስጥም ከውጪም ከፍተኛ የመበታተን አደጋ የተጋረጠበት የፋኖ ኃይል እየደረሰበት ያለውን ጫና መቋቋም እያቃተው እንደሆነ ይሰማል። በፊት ላይ በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላርና ዩሮ በቀላሉ ለመሰብሰብ ይችል የነበረው የውጪው ደጋፊ በተለያዩ ምክንያቶች እጁን ወደ ኪስ ማስገባት እየቸገረው መጥቷል። ከፋኖ እየከዳ ለመንግሥት እጁን የሚሰጠው ሠራዊትና አመራር ጉዳይም ሌላው ተስፋ አስቆራጭ ሆኗል።

በተለይ በቅርቡ በማኅበራዊ ሚዲያ ሲሰራጭ የታየና ለፋኖ የገቢ ማሰባሰቢያ ተብሎ የተጠራ ስብሰባ “በቂ ሰው ስላልተገኘ” በሚል መበተኑ ተበትኗል። በሥፍራው የነበሩና በሁኔታው እጅግ የተናደዱ ሰዎች በስብሰባ ጠሪዎች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር እንደሞከሩና ይህንን የተመለከቱትም ወዲያውኑ ጸጥታ አስከባሪ በመጥራት ሁኔታውን ለመቆጣጠር ችለዋል።

ሰለሞን ቦጋለ የተባለ ግለሰብ የፋኖ ደጋፊ መሆኑ ተጠቅሶ ወደ ኢትዮጵያ ከተጠረዘና በተለይ በዚሁ ዜና ላይ ፋኖ ሦስተኛ ደረጃ አሸባሪ ተብሎ ከተጠቀሰ በኋላ የፋኖ ደጋፊ ደብቁኝ እያለ መምጣቱ በገሃድ የሚታይ ሐቅ ሆኗል። የትራምፕ አስተዳደር የአሜሪካ ዜግነት ያላቸውን ጭምር ዜግነታቸውን እየገፈፈ ወደ መጡበት ሀገር መመለስ መጀመሩ በማንኛውም ቡድን የዳያስፖራ ደጋፊ ዘንድ ከፍተኛ ሽብር ፈጥሯል።

በተለይ ዱሮ ሶማሌያዊ ነኝ፣ የመናዊ ነኝ፣ ሱዳናዊ ነኝ እያሉ አሜሪካ ጥገኝነት የጠየቁና ዜግነት ያገኙ በርካታዎች ሊመለሱ የሚችሉበትን ሀገር ሲያስቡት የፈጠረባቸው ጭንቀት እጅግ ከፍተኛ እንደሆነ ይፋ ያልሆኑ በየአካባቢው በሚደረጉ ኢመደበኛ ስብሰባዎች ላይ የሚሰማ ትርክት ሆኗል። የገቢ ማሰባሰቢያ ስብሰባዎች መሰረዛቸውና በአካል የሚደረጉ ሰላማዊ ሰልፎች ወደ ድረገጽ ትዕይንት መቀየራቸው ከዚሁ ጋር የተያያዘ እንደሆነ በስፋት ይሰማል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ      

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Slider Tagged With: ethiopian terrorists, Fano, North Wollo Fano, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule