ፋኖና ኦነግ ሸኔ በማጣቀስ በውጭ አገራት የሚቀርቡ የጥገኝነት መጠየቂያ ማመልከቻዎች ተቀባይነት እንደማያገኙ ይህንኑ ጉዳይ በማስፈጸም የሚሠሩ አንድ ባለሙያ ለጎልጉል ጥቆማ ሰጡ። ድርጅቶቹ “ነውጥ ቡድኖች" ወይም “violent group s” በሚል የተፈረጁበት አግባብ መኖሩንም አክለው ገልጸዋል። ከአገራቸው በተለያዩ ምክንያቶች ተሰድደው ጥገኝነት የሚጠይቁ ወገኖች ከለላ ለማግኘት በሚያስገቡት የስደተኝነት ማመልከቻ በአሁኑ ሰዓት እንደየብሔራቸው ወይም ብሔራቸውን በመቀየር በብዛት በማስረጃነት የሚጠቀሙት የፋኖና የኦነግ ሸኔን ትግል እንደሆነ ይታወቃል። “ለምሳሌ በካናዳ ድርጅቶቹ “violent groups” ተብለዋል" የሚሉት የሕግ ባለሙያ ይህን የተረዱት በሥራቸው አማካይነት የደንበኞቻቸውን ጉዳይ ሲከታተሉ ነው። ባለሙያው ከተሞቹን ለይተው በስም ባይጠሩም መረጃውን የሰሙት … [Read more...] about ፋኖና ኦነግ ሸኔ “ነውጠኛ ቡድኖች” በመባላቸው ለጥገኝነት ማመልከቻ ተቀባይ እንደማይሆኑ ተሰማ
Fano
“ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን”
”ነገሮች ተበላሽተዋል” በሚል የፋኖ አሰባሳቢ ኮሚቴ ናቸው የሚባሉት ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ ከመስከረም ጋር በስልክ ያደረጉትን ንግግር ይፋ በሆነ ማግስት በሰሜን ወሎ ዞን አካባቢ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበልና ይፋዊ ይቅርታ በማቅረብ ወደ መደበኛ ህይወታቸው መመለሳቸውን የአማራ ክልል አስታወቀ። ክልሉን ጠቅሶ የአማራ ማስ ሚዲያ ይፋ እንዳደረገው በሰሜን ወሎ ዞን አካባቢ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበልና ይፋዊ ይቅርታ በማቅረብ ወደ መደበኛ ህይወታቸው ተመልሰዋል ብሏል። “ተታለን ነው” በሚል ሽማግሌ የላኩትን የሰሜን ወሎ ፋኖዎች ጥያቄ ለመቀበል የአገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች ከዚህ በኋላ ምንም አይነት መንገድ እንዳይዘጋ፣ምንም አይነት የታጠቀ አካል ከተማ ውስጥ እንዳናገኝ … [Read more...] about “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን”