አባዬ - አለው የገበሬው ልጅአቤት - አለ አባቱ።ይሄ የምሰማው ድምጽ ምንድን ነው?የጃርቶች ድምጽ ነው ልጄ።ባለፈው ስታርስ ጮኹ። ስትዘራ ጮኹ። ስታጭድ ጮኹ- አለው ልጁ።ልክ ነህ - መለሰለት አባቱ።ለምን?- አለ ልጅ።የጃርት ጠባዩ ነው። ጃርት ይጮኻል እንጂ አይሠራም። ጃርት አያርስም፤ ስታርስ ይጮሃል። ጃርት አይዘራም፤ ስትዘራ ይጮሃል። አያጭድም፤ ስታጭድ ይጮሃል - አለው አባቱ።ለምን? - ደግሞ ጠየቀ ልጁ።ጃርት ከጮኸ እየሠራህ ነው ማለት ነው። ፍሬ እያፈራህ ነው ማለት ነው። ጃርት ጠፍ መሬት ላይ አይጮህም። ምርት ያለበት ቦታ ነው የሚጮኸው። ጃርት የራሱ ጉዳይ የለውም፤ የራሱ ሥራ የለውም። የሚችለው በሰው ሥራ ላይ መጮህ፤ እሾህ መርጨት እና ሰብል ማጥፋት ብቻ ነው። ጃርቶች ሲጯጯሁ ከሰማህ ያ ገበሬ እየሠራ ነው ማለት ነው። መሬቱ እያፈራ ነው ማለት ነው። - አለው አባቱ።እና ምን … [Read more...] about ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ?
Right Column
ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ?
የአባይ ግድብን በተመለከተ ዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ የሚያደርግ” ስምምነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲፈርሙ ተጽዕኖ እየተደረጉና ወደ ፊርማውም እየሄዱ ነው የሚል እንደምታ ያለው ዘገባ ባወጣ ጊዜ አንድ የጎልጉል ተከታታይ የዛሬ ሦስት ዓመት ተኩል አካባቢ የአጸፋ ምላሽ ሰጥተው ነበር። በወቅቱ የውሃ ሃብት ባለሙያ መሆናቸውን ጠቅሰው February 6, 2020 “ለዋዜማ ሬዲዮ – የህዳሴውን ግድብ ዜናችሁን ላስተካክልላችሁ” በሚል ርዕስ ምላሻቸውን የጻፉት ግለሰብ ያኔ የጻፉት መጣጥፍ በድጋሚ እንዲወጣላቸውና በወቅቱ ዋዜማ ሬዲዮ አለኝ ያለውን ሰነድ ይፋ እንዲደርግ ጥያቄ አቅርበዋል። ትላንት መከናወኑ ከተነገረለት 4ኛው የውሃ ሙሌት ጋር በተያያዘ ጥያቄውን ማቅረቡ አሳማኝ ሆኖ ስላገኘነው ለሚዲው የጸሐፊውን መልዕክት እያደረስን መጣጥፉን ከዚህ በታች በድጋሚ … [Read more...] about ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ?
ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ
በርካታ ሞባይሎችን፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎችንና ሌሎች ቁሳቁሶችን በሕገ-ወጥ መንገድ በመኪና ሻግ ሲያዘዋውሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለፀ። በርካታ ሞባይሎችን፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎችንና ሌሎች ቁሳቁሶችን በመኪና ሻግ በሕገ-ወጥ መንገድ ጭነው ሲያዘዋውሩ የነበሩ ሁለት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ገለፀ። ሁለቱ ተጠርጣሪዎች ነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ለጊዜው ባለቤቱ ባልታወቀ ተሽከርካሪ 202 ፍየሎችን ከላይ፣ ከሥር ደግሞ በርካታ ሞባይሎችን፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎችን፣ መድሃኒቶችን እና የብር ጌጣጌጦችን በሻግ ጭነው ከያቤሎ በመነሳት አዲስ አበባ ከተማ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ብርጭቆ ፋብሪካ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ እንደደረሱ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር … [Read more...] about ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ
ጀብደኛው
አንድ ሽማግሌ የነገሩኝ ታሪክ ትዝ አለኝ። ሰውዬው ጀግና ነኝ፣ አንበሳ በጡጫ ነብርን በእርግጫ እገላለሁ እያለ ይጎርራል። በኋላ ራሱ ደጋግሞ ያወራውን ጉራ እውነት ነው ብሎ ራሱ አመነው። አምኖም አልቀረ በጉራው የተሳቡ፣ በወሬው የተሰባሰቡ፣ አድናቂዎቹን አስከትሎ በረሃ ወረደ። እሱ ጀብድ ሊሠራ ሌላው ጀብድ ሊያወራ፣ ምን ለምን አብረው አዘገሙ። አድናቂዎቹን ከፍ ያለ ኮረብታ ላይ አስቀመጠና "ዛሬ ሶምሶንን በዓይናችሁ ታያላችሁ" አላቸው። እነርሱም አድንቀውና አዳምቀው እንዴት እንደሚያወሩት እያሰቡ ወደ አንበሳ መንጋ የሚወርደውን ጀብደኛ በማዶ ይመለከቱ ያዙ። ወረደ ጀብደኛው። አንበሶች ሰብሰብ ብለው ተኝተዋል። በሩቁ ድንጋይ ወረወረባቸው። ሁሉም አንበሶች ቀና ቀና አሉ። አንዱ በድንጋይ የተመታ ደቦል ዘሎ ወጣበትና በቅጽበት ሌሎች ገነጣጠሉት። ታሪኩም ከጄት ፈጥኖ ከውኃ ቀጥኖ … [Read more...] about ጀብደኛው
“አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ
አሁን ፊታቸውን ያዞሩበት ጓደኞቹ አራጋቢዎቹ “ዜናን አንተ ጻፋት፤ አንተ አንብባት” እያሉ ሲያሞካሹት ነበሩ። እንዲህ እንዲሉ ያበቃቸው ደግሞ መሳይ የግንቦት ሰባት/ኢሳት ሁለገብ ሠራተኛ በነበረበት ወቅት ኤርትራ ምድር ሄዶ እንደ አንድ የጦር አዛዥ “ዘመነ ካሤ” የሚመራውን “ጦር” ሲጎበኝ ፎቶ ተነስቶ ሲያዩት፤ የሻዕቢውን መሪ በልዩ ጥሪ አስመራ ድረስ ሄዶ ቃለ መጠይቅ ሲያደርግ ሲያዩት፣ የብልፅግናን ድሎች አዲሳባ ድረስ ሄዶ ሲዘግብ በምላሹም ለከፈለው መስዋዕትነት ተብሎ ትንሽዬ ጉልት ሲቸረው ሲያዩት፣ አዲሳባ በሄደበት ወቅት የሹማምንትን ስልክ ቁጥሮች ሰብስቦ ከመጣ በኋላ ከምግብ ቤቱ ሆኖ የሚያወራበትን አንከር ብሎ የሚጠራውን ዩትዩብ ሲከፍት ሲያዩት ነበር። የመሳይ “ድሎች” እንዲህ በቀላሉ ተወርተው የሚያልቁ አይደሉምና እዚሁ ላይ ላብቃ። አንዳንዶች ሲቀልዱ እንደሰማሁት መሳይ በወኔ … [Read more...] about “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ
ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው
ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን አሳልፎ ለመስጠት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። አራተኛው የኢትዮ-ደቡብ አፍሪካ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በስብሰባው ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የደቡብ አፍሪካ የዓለም አቀፍ ግንኙነቶችና ትብብር ሚኒስትር ዶክተር ናሌዲ ፓንዶር እንዲሁም የሁለቱ አገራት ባለስልጣናት ተሳታፊ ሆነዋል። በዚህ ወቅት ሁለቱ አገራት በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን አሳልፎ ለመስጠት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የፍትሕ ሚኒስትር ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ እና የደቡብ አፍሪካ የዓለም አቀፍ ግንኙነቶችና ትብብር ሚኒስትር ዶክተር ናሌዲ ፓንዶር ተፈራርመዋል። ሁለቱ አገራት በስብሰባው ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ሳይንስ፣ ኢኖቬሽን፣ ትምህርት፣ … [Read more...] about ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው
የተሰረቁ የሞባይል ስልኮች (215) በህጋዊ ስም በተከፈቱ የንግድ ሱቆች ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋሉ
በተለያዩ አካባቢዎች የተሰረቁ ከሁለት መቶ በላይ የሞባይል ስልኮችን በህጋዊ ስም በተከፈቱ የንግድ ሱቆች ውስጥ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖለስ አስታውቋል፡፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ በህጋዊ የሞባይል ስልክ እና የቴሌቪዥን ጥገና ሱቅ ሽፋን ከግለሰቦች የተሰረቁ ስልኮችን እየገዙ ሲሸጡ ከነበሩ ግለሰቦች ሱቅ ውስጥ 215 ሞባይል ስልኮች መያዛቸው ታውቋል፡፡ የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ ከህዝብ በደረሰው ጥቆማ እና ባደረገው ክትትል በወረዳ 3 ኤድናሞል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሞባይል ጥገና ስራ በሚሰሩ አራት የንግድ ሱቆች ላይ ትናንት ሃምሌ 19 ቀን 2015 ዓ.ም በህግ አግባብ በተከናወነ ብርበራ ነው ከተለያዩ ቦታዎች ተሰርቀው የተከማቹ ሞባይል ስልኮች ሊያዙ የቻሉት፡፡ ከሞባይል ስልኮቹ በተጨማሪ የወንጀል ፍሬ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ እና በጥገና ቤቶቹ ውስጥ የተገኙ የተለያየ … [Read more...] about የተሰረቁ የሞባይል ስልኮች (215) በህጋዊ ስም በተከፈቱ የንግድ ሱቆች ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋሉ
“ዛሬ መጻሕፍት የሚያነቡ ህፃናት ነገ አይሰርቁም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
“ዛሬ መጻሕፍት የሚያነቡ ህፃናት ነገ አይሰርቁም፤ በሙስና እና በሌብነት ቀንበር ስር አይወድቁም” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ። "መጻሕፍት የህይወት ዘመን ጓደኛ ናቸው" እንዳሉት ከተሽከርካሪ ነፃ (car free) መንገድ ያስፈልጋል፤ ከሀሳብ እና ከመጻሕፍት ነፃ የሆነ ጎዳና ግን ሊኖር አይገባም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት አብርሆት ቤተ-መጻሕፍት ከመደበኛ ስፍራው ባለፈ በአዲስ አበባ የተለያዩ ጎዳናዎች ላይ ለታዳጊ ህፃናት መጻሕፍት ያቀርባል ደግሞም ያነባል፤ ያስነብባልም። ዛሬ መጻሕፍት የሚያነቡ ህፃናት ነገ አይሰርቁም፤ በሙስና እና በሌብነት ቀንበር ስር አይወድቁም ሲሉም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ታነባለች ጎዳናዋም በመጻሕፍት ተሞልቶ ይትረፈረፋል። “እኛ ኢትዮጵያውያን ካለብን ችግር የምንወጣው … [Read more...] about “ዛሬ መጻሕፍት የሚያነቡ ህፃናት ነገ አይሰርቁም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
ነብርን ያላመዱ እናት
ወ/ሮ ጂሎ ጃተኒ ይባላሉ፤ በቦረና ዞን የዲሎ ወረዳ ቃዲም ኦላ ጫጩ ገልገሎ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ወ/ሮ ጂሎ ጃተኒ የዱር እንስሳት የሆነውን ነብርን በማላመድ አብራቸው እየኖረ ይገኛሉ፡፡ ወ/ሮ ጂሎ በዞኑ ድርቅ ተከስቶ በነበረበት ወቅት ለከብቶች ሳር ለመፈለግ ወደ ዱር ባቀኑበት ጊዜ የነብር ግልገል ማግኘታቸውን ይናገራል። ወይዘሮዋ ግልገሏን እነርሱ የሚመገቡትን ምግብ በመመገብ እንዳሰደጉትና አሁን ላይ ተላምዶ ከፍየሎችና ህፃናት ጋር እያደገ ነው ማለታቸውን ኦቢኤን ዘግቧል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ነብርን ያላመዱ እናት
ከ6-10ኪሎ ሜትር መወንጨፍ የሚችል BM-21 የሠራ ወጣት
በወላይታ ዞን በተለያዩ ፈጠራ ሥራዎች የሚታወቅ ወጣት ከ6-10ኪሎ ሜትር መወንጨፍ የሚችል BM-21 የተባለውን አዲስ ሮኬት ሰራ። በወላይታ ዞን በተለያዩ ፈጠራ ስራዎች የሚታወቅ ወጣት ሳሙኤል ዘካሪያ 360° ዞር መምታት የሚችል BM-21 የተባለውን አዲስ ሮኬት ሰርቶ የወላይታ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ዮሐንስ በየነ እና የዞኑ የመንግስት ረዳት ተጠሪ ወ/ሮ እታገኝ ኃ/ማርያም በተገኙበት ለእይታ አቅርቧል። ሮኬቱ ከስድስት እስከ 10 ኪሎ ሜትር መወንጨፍ የሚችል መሆኑን ወጣት ዘካሪያ በመገለጽ በአንዴ አራት ቀላዮችን የሚይዝና መወንጨፍ የሚችል ሮኬት መሰራቱን ገልጸዋል። ያለሰው ንክኪ በራሱ ማዘዣ 360° ዲግሪ በመዞር በአየር ክልል የሚንቀሳቀስና ጥሶ የሚገባ የጠላት ዒላማን መምታት የሚችል ሮኬት መሆኑንም አስታውቆ ቦታው ከተመቻቸ በኋላ በሳምንታት ውስጥ የተሳካ … [Read more...] about ከ6-10ኪሎ ሜትር መወንጨፍ የሚችል BM-21 የሠራ ወጣት