በትግራይ፥ "ተራሮችን ያንቀጠቀጠ ትውልድ" የሚለው በግነት የተሞላ ትርክት ከራሱ ከትርክቱ መነሻ ጋር ሦስት ትውልድ በልቷል። አያት፣ አባትና ልጅን የሕይወት ዘመን የአካል ጉዳተኛ አድርጓቸዋል። በትጥቅ ትግሉ፣ በባድመ ጦርነት እና በአሁኑ ጦርነት አያት፣ አባትና ልጅ አካለ ጎደሎ የሆኑበት የትግራይ ፖለቲካ ሙሉ ትራጀዲ ለኢትዮጵያም የተረፈ መሆኑ ይሰመርበት። ዛሬ በትግራይ ያለ አካለ ጎደሎ 'የጉዳት መቼት' ለማወቅ 'የደርጉ ነው ወይስ የብልጽግናው?' እንዲህ ያደረገህ ብሎ መጠየቅ ግድ የሚልበት ሁኔታ ተፈጥሯል። አያት፣ አባትና ልጅ አካለ ጎደሎ ለመሆን ያበቃቸውን፤ ከአማራ፣ አፋርና ኤርትራ ሕዝብ ጋር ደም አፋሳሽ ቅራኔ ውስጥ የከተታቸውን የእብደት ፖለቲካቸውን መርምሮ ለመከለስ/ለማረም ከመነሳሳት ይልቅ ዛሬም ለአራተኛ ዙር ጦርነት ምልመላ፣ ልምምድና ስልጠና ላይ ናቸው። … [Read more...] about ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት!
Right Column
የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ
ሕጉ ምን ይዟል ? ማንኛውንም ራሱን በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት አፍቃሪነት የመደበ፣ ወይም የጾታ ለውጥ ያስደረገ እንዲሁም በእንግሊዝኛ ምሕጻራቸው ኤል-ጂ-ቢ-ቲ-ኪው (LGBTQ+) ዝርዝር ውስጥ የሚካተት የጾታ ዝንባሌ ያለው ዜጋን ሁሉ ወንጀለኛ ያደርጋል። በጸደቀው አዲሱ ሕግ መሠረት የተመሳሳይ ጾታ ዝንባሌ ያለው ዜጋ የረጅም ጊዜ እስር ይጠብቀዋል። የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎችን በጉያው ያቀፈ፣ በቤተሰብ ደረጃ ያስጠለለ፣ ወዳጃቸው የሆነ ወይም አብሯቸው ያለ ሰው “እከሌ እና እከሌ” ብሎ ለሕግ አካላት ማንነታቸውን የማጋለጥ ግዴታን በሌሎች ላይ ይጥላል። በዚህ ሕግ ልጆችን ለዚሁ ለተመሳሳይ ጸታ ያጨ ወይም ያስተላለፈ የእድሜ_ይፍታህ ፍርድ ይጸናበታል። "በተመሳሳይ ጸታ መብት" ዙርያ የሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ግንኙነቱን የሚያበረታታ ማንኛውንም የሕትመት ውጤት … [Read more...] about የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ
በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም
ከቀናት በኋላ በሚካሄደው ሮም ማራቶን ኢትዮጵያዊው ሯጭ በባዶ እግሩ በመሮጥ ታሪክ ሊደግም ነው። የፊታችን እሁድ የ2023 በሚካሄደው የሮም ማራቶን ኢትዮጵያዊው የባዶ እግር ሯጭ እንዲሁም ለረጅም አመታት በኢትዮጵያ ታላቁ ሩጫ ቁልፍ ሰው (ዳይሬክተር) በመሆን የሰራው የ45 ዓመቱ ኤርሚያስ አየለ ሙሉ ማራቶን በባዶ እግሩ በመሮጥ የታላቁን አትሌት አበበ ቢቂላን ታሪክ ሊደግም ይችላል እየተባለ ነው። ኤርሚያስ ከዚህ ቀደም የታላቁ ሩጫንና የሀዋሳ ግማሽ ማራቶንን በባዶ እግሩ የሮጠ ሲሆን ይህንን የሚያደርገውም ለኢትዮጵያው ታላቅ አትሌት አበበ ቢቂላ ክብር እንዲሁም ለሀገር ገፅታ ግንባታ ሲል መሆኑን ተናግሯል። የሮም ውድድሩ ቀላል እንደማይሆንና ስሜታዊም የሚያደርግ እንደሆነ የገለፀው ኤርሚያስ "ይህን ትልቅ ትርጉም ያለውና ታሪካዊ ውድድር ለማድረግ ዝግጅቴን አጠናቅቄያለሁ" … [Read more...] about በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም
ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ይታሰባል ተብሎ ባልተገመተ ሁኔታ የዓድዋ በዓል በኢትዮጵያዊነት መንፈስ በትግራይ የዓድዋ ከተማ ሶሎዳ ተራራ ሥር መከበሩን ኢፕድ ዘግቧል። በበዓሉ ላይ ህፃናት ስለ ዓድዋ ድል የሚተርክ ህብረ ዝማሬ አቅርበዋል። የከተማው ነዋሪዎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በዓሉን ለመታደም ማልደው በሥፍራው ተገኝተዋል። ከዚህ በተጨማሪም የኢትዮጵያን ሠንደቅ ዓላማ የሚያውለበልቡና በአማርኛ የተጻፉ አስደማሚ መፈክሮች በበዓሉ ሰልፍ ላይ ታይተዋል። ትህነግ በግፍ በሚገዛት ትግራይ ይህ ዓይነት አከባበር መከሰቱ ለክልሉ ሕዝብ የነጻነት ተስፋ የፈነጠቀ ነው ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ
የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ!
ስሙ የክህደት መጠሪያ ሆነ እንጂ የስሙ ትርጉም ግሩም ነው። ይሁዳ የሚለው ቃል በእብራይስጥም “ይሁዳ” ማለት ነው፤ “ያዳ” ነው ሥርወ ቃሉ ይላሉ የሙያው ባለቤቶች። ይህ ደግሞ ትርጉሙ “ማመስገን” ማለት ነው። በግሪክም ትርጓሜው ተመሳሳይ ነው - “የተመሰገነ”፣ “ምስጉን” ማለት ነው። “የአስቆሮቱ” የሚለው ቃል ደግሞ የክፋት መጠሪያ አይደለም። በተለምዶ “የአስቆሮቱ ይሁዳ” በማለት ከሃዲዎችን ስንጠራቸው “አስቆሮቱ” የይሁዳ የክፋት ማዕረግ ይመስለናል። ሊቃውንቱ እንደሚሉን ከሆነ ትርጉሙ “የኬሪዮት ሰው” ወይም “የአራዳ ልጅ” እንደ ማለት ነው ይላሉ። ስለዚህ በከሃዲነቱ ባናውቀው ኖሮ “ተመስገን ያራዳ ልጅ” ብለን እንጠራው ነበር። ስሙ ግን ከግብሩ ፍጹም የራቀ ነው፤ እንዲያውም ተጻራሪ። ይሁዳ ከሃዲ ብቻ አይደለም፤ ማሳካት የሚፈልገው ዓላማ ያለውና የሚያደርገውን … [Read more...] about የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ!
አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ
የኢትዮጵያን ፊደል አማርኛ ቋንቋን የአፍሪካ ኅብረትና የአፍሪካ አሃጉር ፊደል ይደረግ ዘመቻ መጀመሪያ በግሪጎሪያን 1989, በየሐረርወርቅ (የኢትዮጵያወርቅ) ጋሻው መስራችነት ተጀመረ። ይህንን ትልቅ ዓላማዋን በጽናት ይዛ ግቧን ለመምታት እነሆ በይፋ በ1990 (ግጎ) ለአፍሪካ መሪዎች በነብስ ወከፍ በማስተዋወቅ ብሎም ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት አሁን የአፍሪካ ኅብረት ጭምር ካስተዋወቀችበት ጊዜ ጀምሮ አንድቀን ሳታቋርጥ ቀጥላበት እነሆ በጉዳዩ ጸንታ እስከዛሬ በመታገል ላይ ትገኛለች። ከተነሳችበት ጊዜ ጀምሮ ብዙ እንቅፋቶች በትሕነግ መሪ በመለስ ዜናዊና በግብረ አበሮቹ ጅምሯን ለማኮላሸት የተፈጸሙ ችግሮች ቢያጋጥሟትም፣ እነሆ እስከዛሬ ድረስ ወደኋላ ሳትል ሌሎች አፍሪካውያንን ጭምር በማስተባበር እየታገለች ትገኛለች። ለዚህም አንዱ ይሄ የስም ፊርማ ዘመቻን ጀምራ ለዚህ ዓላማ ይጠቅማሉ … [Read more...] about አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ
የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ!
ጃዋር መሐመድ “የኦሮሞ ፕሮቴስት” ብሎ የጀመረ ሰሞን ብዙ የፌስቡክ ተከታታይ አልነበረውም። ወዲያው አገር ቤት ከኦህዴድ ጋር በነበረው ግንኙነት የተቃውሞ ሰልፎችንና የፖሊስ ግፎችን የሚያሳዩ ፎቶዎችን መለጠፍ ሲጀምር የተከታታዩ መብዛት ጀመረ።ዝግጅቱም፣ ትምህርቱም፣ ሥራውም፣ በሚዲያ ዙሪያ ስለነበር ሚዲያን እንዴት እንደሚቆጣጠርና የሕዝቡን ቀልብ እንዴት እንደሚስብ ጠንቅቆ ያውቅ ነበር። በመሆኑም ከማኅበራዊ ሚዲያ እስከ ዋንኛ (mainstream) ያለውን በቀላሉ ተቆጣጠረው። ለመረጃ፣ ለዘገባ፣ ለዜና፣ … እንደ ምንጭ የሚጠቀስ ሆነ። ትልልቅ የሚባሉት የውጪዎቹ የሚዲያ አውታሮች እሱን ሳያናግሩ ዜና መሥራት አልታያቸው አላቸው። በፍጥነት ወጣ፣ ተመነደገ፣ ከፍ አለ! የዚያኑ ልክ እሱም እያበጠ መጣ። ዕብጠቱ ገና አፍላ በነበረበት ጊዜ ባደባባይ የዕብሪት ንግግር ለጠፈ። አሁን በማላስታውሰው … [Read more...] about የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ!
የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው
ክርስቲያኗ ክስ መመሥረቷም ተሰምቷል በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ውስጥ የተፈጠረውን መከፋፍለ ተከትሎ አንደኛውን ወገን ለማውገዝ ተጠርቶ ከነበረው የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ መካከል የባህር ዳሩ መሰረዙ ተገለጸ። “ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ጾመ ነነዌን ምክንያት በማድረግ በመላው ዓለም የሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያን ጥቁር ልብስ ብቻ በመልበስ በጾምና በጸሎት ምሕላ በመያዝ በቤተ ክርስቲያን ዓውደ ምሕረት በመገኘት ወደ እግዚአብሔር ጾም፤ ጸሎትና ምሕላ እንዲቀርብ” ሲል ቅዱስ ሲኖዶስ ባስተላለፈው ጥሪ መሰረት ነው “ጥር 28 በባሕር ዳር ከተማ እሑድ ጥር 28 ፡ 2015 ዓ.ም ባሕር ዳር መስቀል አደባባይ ሊደረግ የነበረው “ኦርቶዶክሳዊ” የተባለው ሰልፍ እና የምህላ ፀሎት መራዘሙ በመግለጫ የተገለጸው። “ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪ አስተላልፏል። ስለሆነም በቀጣይ … [Read more...] about የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው
በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ በማኅበራዊ የትሥሥር ገጻቸው ይህንን ጽፈዋል። ዛሬ በአቡዳቢ በመሠራት ላይ ያለውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጎብኝቻለሁ። 17682 ካሬ ሜትር መሬት ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬት መንግሥት ተሰጥቶናል። ለዚህም በኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ስም አመሰግናቸዋለሁ። ለጊዜው መገልገያ የሚሆነው ቤተ ክርስቲያን እየተጠናቀቀ ነው። የጥምቀት በዓል በቦታው እንዲከበር የሚቻለው ሁሉ እንደሚደረግ ከሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ቃል ተገብቶልናል። ይሄንን መሰል ቦታዎች የታሪክና የዲፕሎማሲያችን ትእምርቶች ናቸው። እነርሱ ለእኛ ይሄንን ሲያደርጉ፣ አኛ ለገዛ ወገኖቻችን ከዚህ በላይ እንድናደርግ ትምሀርት ይሆነናል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ
ሐሰተኛ መታወቂያ በማዘጋጀት የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎትና የሌሎች መንግሥታዊ ተቋማት አባል ነን በማለት ኅብረተሰቡን እያጭበረበሩ በሚገኙ ግለሰቦች ላይ ጥብቅ ክትትል በማድረግ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ ተገለጸ። የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢፕድ በላከው መረጃ እንዳመለከተው፤ ሐሰተኛ መታወቂያ በማዘጋጀት የደኅንነትና የሌሎች መንግሥታዊ ተቋማት አባል ነን የሚሉ ግለሰቦችን በተመለከተ በተለያዩ መንገዶች ክትትል ሲደረግ ቆይቷል። ሰሞኑን በተደረጉ ጥብቅ ክትትሎችም ፈለቀ ዴብሳ ደማ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02፤አስፋው አዳማ ሙታ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01፤ሳምሶን ገነነ መንገሻ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5፤ተስፋ ሀተው ገምቴሳ … [Read more...] about በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ