ራሱን የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) በማለት የሚጠራው ሕገወጥ የወንበዴዎች ቡድን ተክሎብን እና ጥሎብን የኼደው መርዝ እስካኹን አልፋታ ብሎን የመከራ ዘመናችንን አርዝሞታል። ሀገርን በዘር ከፋፍሎ፤ ሕዝብን እንደ ከብት በክልል ወስኖ፤ ኢትዮጵያዊነትን በሰፈርና በወንዝ ወስኖ፤ ለዘመናት አብሮ የኖረን ሕዝብ በጠላትነት እንዲተያይ አድርጓል። እንዳሰበው ባይሳካለትም ሀገራችን ከመፍረስ ድና አኹን ያለችበት ቁመና ላይ ትገኛለች። ትህነግ ግን ነጻ አወጣዋለኹ ብሎ ሲነግድበት የነበረውን ሕዝብ የምድር ሲዖል ውስጥ ጨምሮ እያሰቃየው ይገኛል። ወደ ጉዳያችን ስንመለስ፤ ትህነግ መርዙን ተፍቶብን ወደ ትግራይ ኼዶ ቢመሽግም አሁንም ግን ግድያ፣ ደም ማፍሰስ፣ ማፈናቀል፣ አልቆመም። በሀገሪቱ ላይ የሚፈጽመው ዕልቂት የገፊና ጎታች ሤራ እንደሆነ በተደጋጋሚ ያነሳነው ጉዳይ ነው። ጎልጉል በዚህ … [Read more...] about ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው?
Right Column
ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም!
በኦነግ ሸኔ ዐማጽያን በንጹሐን ዜጎች ላይ በተለይም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ዒላማ ተደርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ተከትሎ፤ የቤተሰብ እና የወዳጆቻቸውን ሕይወት ላጡ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እና የቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው በአርሲ ዞን ለሚገኙ ወገኖቻችን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻሉ። እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ሲሆኑ፤ ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው። መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር ፍትሐዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከአንድ … [Read more...] about ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም!
የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ
የውጭ የደህንነት ተቋማት በአንድ ሀገር ውስጥ ወደፊት ስልጣን ወይም ተፅዕኖ ሊኖራቸው የሚችሉ ወጣቶችን ገና በለጋ እድሜያቸው የመመልመልና የራሳቸውን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ግብ በሚያሳካ መልኩ ኮትኩቶ የማሳደግ ስልትን በስፋት ይተገብራሉ። ይህ ተግባር በዘርፉ "የልሂቃን ቀረጻ" (Elite Capture or Cultivation) ተብሎ የሚጠራ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም የተመረጡ ወጣቶችን የዓለም እይታ (Worldview) ከሀገራዊ ጥቅም ይልቅ የውጭ ሃገር ፍላጎትና ጥቅምን በሚያሳካ መልኩ አድርጎ መቅረጽ ነው። እነዚህ ተቋማት የአንድን ወጣት የወደፊት የመሪነት ዝንባሌ ቀድመው በመረዳት፣ በትምህርት እና በተለያዩ ስልጠናዎች ስም ከሀገሩ በማውጣት የአስተሳሰብ አድማሱን በእነሱ የፍላጎት ልክ ይቀርፁታል። ይህ "Formative age" ወይም የማንነት ቀረጻ ምቹ እድሜ የአንድ ሰው ስብዕና እና … [Read more...] about የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ
ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ
ሀገር ሙሉ ሕዝብ በሴፍቲኔት እየተረዳ አይደለም የዓለም ባንክ የሰጠው ዕርዳታ ለ700 ሺህ ሕዝብ ብቻ የሚውል ነው ሰላሳ ዓመት ሞላኝ የሚለውና ብዙዎችም የሚዲያ ጽናት፣ አውራ፣ ወዘተ እያሉ የሚጠሩት አውሬው ሪፖርተር ሀገር ለማፍረስ ቀስ እያለ በመሸርሸር ሥራ ላይ እንደተሠማራ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በተደጋጋሚ በርካታ መረጃዎች አውጥቶበታል፤ ማውጣቱንም ይቀጥላል። አፍቃሪ ትህነግ የሆነው ሪፖርተርና ባለቤቱ አማረ አረጋዊ ዜና መቀሸብ የተካኑበት ሞያቸው ነው። አካሄዱ ግልጽና ጽንፈኛ የመቃወም ስልት የተከተለ ሳይሆን እንደ ምስጥ ከውስጥ የመቦርቦርና ቀፎ አድርጎ የማስቀረት ነው። በዚህ ስልት የሚዘገቡትን የዜና ዘገባዎችን ማሰራጨት ለሪፖርተር አይጠበቅበትም፤ አፈ-ሰማይ የሆነው የማኅበራዊ ሚዲያ ተቀላቢ፤ ይህ ሁሉንም ማለትም በመንግሥትም፣ በግልም፣ በግብፅም፣ በሻዕቢያም፣ ወዘተ … [Read more...] about ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ
“አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ
በ1980ዎቹ ነበር፤ በዘመኑ ቀልድ የሚያበዛ ታዋቂ ጋዜጠኛ በአንድ የታወቀ ሪዞርት ሽንት ቤት ውስጥ አሳማ ያስቀምጣል። አሳማዋንም የከንፈር ቀለም (ሊፕስቲክ) ቀብቶ እንደ ሰው አስመስሎ። ዓላማው ሌላ ሳይሆን ፕራንክ ነበር። ክስተቱ የሪዞርቱን ባለቤት ፕራንክ አድርጎ ቢያልፍም ከዚያ በኋላ ግን አሳማ የከንፈር ቀለም ቢቀባ እንደ አሳማ መጮኹ (ኦይንክ ማድረጉ)፣ ጭቃ ላይ መንከባለሉ፣ አሰሱንም ገሰሱንም መብላቱ፣ … ባጠቃላይ አሳማነቱ አይቀርም ማለት ነው በሚል አባባል ተተካ። ከዚያም በ90ዎቹ ለቴክሳስ ሀገረግዢነት ይወዳደሩ የነበሩት አን ሪቻርድስ አባባሉን ተጠቀሙበት። ትልቁ ቡሽ በምርጫ ውድድር በነበሩበት ጊዜ የቡሽ አስተዳደር ለውጥ እንደማያመጣ አን ሲናገሩ “ዌል የአሳማዋን ከንፈር ሊፕስቲክ ቀብቶ ሞኒካ ነሽ ሊሏት ይቻላሉ፤ ግን አሳማነቷ ፈጽሞ አይቀየርም” ነበር … [Read more...] about “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ
የተንጋደደው የገዱ መልስ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የቀድሞ ጭፍራቸውን ገዱ አንዳርጋቸው በፓርላማ በስም ጠርተው ለተናገሩት ገዱ መልስ ሰጥተዋል። ይህ ጽሑፍ ዓላማ ያደረገው ለገዱ ምላሽ አስተያየት ለመስጠት አይደለም። ምክንያቱም የመጀመሪያና ትልቁ ስህተት ያለው ገዱ በጻፉት የመጀመሪያው አንቀጽ ላይ ስለሆነ ነው። ያ ሳይስተካከል በገዱ ጽሑፍ ላይ ምንም ማለት አይቻልም። ገዱ የጠቅላዩን ንግግር የሰሙት እንዴት እንደሆነ ሲገልጹ “ሰዎች ቆርጠው በላኩልኝ የቪዲዮ ቅጂ” ነው ብለዋል። ገዱ የግል ታሪካቸው እንደሚያስረዳው “መጀመሪያ ዲግሪ” የያዙት በተለምዶ “የዲግሪ ወፍጮ” ወይም “ድንጋይ ማምረቻ” ከሚባለው ሲቪል ሰርቪስ “ዩኒቨርሲቲ” ነው። ሲቀጥል “ማስተርስ ዲግሪ” ከአዙዛ ነው። መቼም ስለ አዙዛ መናገር እዚህ ላይ አያስፈልግም። ግልጽ መሆን ያለበት ጉዳይ ግን ከሲቪል ሰርቪስም ሆነ ከአዙዛ የተመረቀ ሁሉ … [Read more...] about የተንጋደደው የገዱ መልስ
አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ
* በስጋት ከቀያቸው የተፈናቀሉት የትግራይ ተወላጆች ቤታቸው ሳይፈርስ፣ ንብረታቸው ሳይጎድል ለዓመታት ጠብቋቸዋል በትላንትናው የፓርላማ ውሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢሉባቦር ዞን ሁሩሙ ወረዳ ይኖሩ የነበሩ የትግራይ ተወላጆችን አስመልክቶ የተናገሩ የብዙዎችን ልብ የነካና ኢትዮጵያዊነትን አድምቆ ያሳየ መረጃ ነበር። “ለምሳሌ ጦርነት ሲጀመር” አሉ ዐቢይ “ከኢሉባቡር ሸሽተው ትግራይ የሄዱ አርሶ አደሮች ነበሩ። ከዛ የመጣችሁ ሰዎች አጥኑ ይሄን ጉዳይ ትክክለኛ መረጃ ነው። “ሰዎቹ ሸሽተው ትግራይ ገብተዋል፤ ኢሉባቡር ያሉ አርሶአደሮች ከእነርሱ ማሳ ቡና ለቅመው ሸጠው ገንዘቡን በአካውንታቸው ያስገባሉ፤ ሰዎቹ የሉም። ከእርሻቸው ላይ የተመረተ ምርት ሸጠው ገንዘቡን በራሳቸው አካውንት ያስገባሉ። “ሰዎቹ 'የኛ ሰዎች በሌለንበት ሰርተው አካውንታችን እያስገቡ ነውና በቃ … [Read more...] about አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ
በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ
በአሜሪካ የኦሃዮ ጠቅላይ ግዛት ሴናተር የሆኑት ሪፓብሊካኑ በርኒ ሞሬኖ ጣምራ ዜግነት እንዲቀር ለሕግ መወሰኛው ምክር ቤት Exclusive Citizenship Act of 2025 በሚል ርዕስ ረቂቅ ሕግ አቅርበዋል። አዋጅ ሆኖ ከጸደቀ ዜጎች በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የሚፈልጉትን እንዲመርጡ ይደረጋሉ። አሜሪካ በስደተኞች የተመሠረተች አገር እንደመሆኗ የኢሚግሬሽን ሕጓ ከአውሮጳውያኑ በተለየ ለስደተኞች የሚያደላ ነው። ለምሳሌ አሜሪካ መጥቶ ጥገኝነት የጠየቀ ሰው ጉዳዩ ከጸደቀለት ከአምስት ዓመት በኋላ ዜጋ መሆን ይችላል። በአሜሪካዊ ዜግነቱ ከሌላ ሀገር ሚስት ቢያመጣ አሜሪካዊ ስላገባች በሚል እሷ በሦስት ዓመት ዜጋ መሆን ትችላለች። ጉዳዩ ሳያልቅለት ወይም ሕጋዊ ሳይሆን ቢቀርና በመካከል ግን ልጅ ቢወልድ ልጁ ዜጋ ይሆናል። ዜግነትንም በተመለከተ ጣምራ ዜግነት በሕግ የሚፈቀድ … [Read more...] about በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ
የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች
* ውሳኔው ለአብያተ ክርስቲያናት ኅብረት መንገድ ጠራጊ ነው ተብሏል የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ከዚህ በፊት ለማርያም ተሰጥተዋት የነበሩት “የመድኃኒዓለም ረዳት” (Co-Redemptrix) እና “ሴት አማላጅ” (እናት አማላጅ) (Mediatrix) የሚሉት ስሞች ለማርያም እንዳይውሉ ውሳኔ አስተላለፈች። ውሳኔው በአብያተ ክርስቲያናት መካከል ሊመሠረት ለታቀደው ኅብረት ድጋፍ ሰጪ እንደሆነም ተነግሮለታል። የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያንን የአስተምህሮና ሥነ-ስርዓት የሚመራው “በጳጳሳዊ ምክር ቤት የእምነት አስተምህሮ ጽ/ቤት” (Dicastery for the Doctrine of the Faith (DDF)) በኅዳር ወር መጀመሪያ “የእግዚአብሔር ታማኝ ሕዝብ እናት” (Mater Populi Fidelis) በሚል ርዕስ ስለ ማርያም ሰፊ ማብራሪያ ይፋ አድርጓል። ሰነዱ “የመድኃኒዓለም ረዳት … [Read more...] about የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች
በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ
* “ዳህላክ ነው ቤቴ”፤ “ደሞ በዓባይ (ድርድር) ከሞከሩንማ” ኢትዮጵያ ላይ ተረባርበው የነበሩ፣ ኢትዮጵያ ላይ ፍትሕ በማዛባት ዘምተው የነበሩ፣ ኢትዮጵያን ማሳጣት የዕለት ተዕለት ተግባራቸው የሆነ ወዘተ ሚዲያ አውታሮች “ኢትዮጵያ ኑክሊየር ታጠቀች” በማለት ለታላቁ የዓባይ ግድብ አድናቆታቸውን ቸረዋል። በጨለማ ውስጥ ለሚኖሩ ብርሃን ያዩ ዘንድ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ በራሷ ልጆችና ኪስ ይህን “ክስተት" የተባለ ፕሮጀክት ስታስመርቅ የተሰማው ታሪክ በዜጎች ዘንድ ሁሉ ከዳር እስከዳር ልዩ ስሜትን ዘርቷል። አስራ አምስት ሺህ ዜጎች የጠላት ተልዕኮ በተቀበሉ ቅጥረኞች ወጥመድ ማለቃቸው ግድቡ በኢትዮጵያዊያን፣ ጉልበት፣ ገንዘብና ዕውቀት ብቻ ሳይሆን አጥንትና ደም ጭምር የተገነባ፣ የታተመ የኢትዮጵያዊያን ሁሉ ማኅተባቸው እንደሆነ እዚያው ሥፍራው ላይ ሆነው ሁሉንም ያዩና የታዘቡ … [Read more...] about በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ










