የፌዴራል ፖሊስ በሪፖርተር ላይ ያወጣው መግለጫ የሪፖርተርንና የባለቤቱን ማንነት እንዲሁም ስሑት ሥራውን ያጋለጠ ነው። እንደ ፌዴራል ፖሊስ መግለጫ ሪፖርተር “ስውር ተልዕኮ የተንፀባረቀበት ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ፈፅሟል”። የመግለጫው ሙሉ ቃል ከዚህ በታች ይገኛል። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሪፖርተር ጋዜጣ “ከፍተኛ ባለስልጣናትና ታዋቂ አርቲስቶች ከ98 ቢሊየን ብር በላይ መዝረፋቸው በኦዲት ምርመራ መረጋገጡ ተነገረ" በሚል የዘገበው መረጃ የተዛባ መሆኑን አስታወቀ ሪፖርተር ጋዜጣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የዘጠኝ ወር የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ለተከበረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና የፍትህ ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ሪፖርቱን ለማስረዳት በማስታወሻነት የተጠቀመበትን ጥቅል መረጃ መነሻ በማድረግ፣ ጠቅላላ ይዘቱን በአግባቡ … [Read more...] about ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ
Reporter
ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ
ሀገር ሙሉ ሕዝብ በሴፍቲኔት እየተረዳ አይደለም የዓለም ባንክ የሰጠው ዕርዳታ ለ700 ሺህ ሕዝብ ብቻ የሚውል ነው ሰላሳ ዓመት ሞላኝ የሚለውና ብዙዎችም የሚዲያ ጽናት፣ አውራ፣ ወዘተ እያሉ የሚጠሩት አውሬው ሪፖርተር ሀገር ለማፍረስ ቀስ እያለ በመሸርሸር ሥራ ላይ እንደተሠማራ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በተደጋጋሚ በርካታ መረጃዎች አውጥቶበታል፤ ማውጣቱንም ይቀጥላል። አፍቃሪ ትህነግ የሆነው ሪፖርተርና ባለቤቱ አማረ አረጋዊ ዜና መቀሸብ የተካኑበት ሞያቸው ነው። አካሄዱ ግልጽና ጽንፈኛ የመቃወም ስልት የተከተለ ሳይሆን እንደ ምስጥ ከውስጥ የመቦርቦርና ቀፎ አድርጎ የማስቀረት ነው። በዚህ ስልት የሚዘገቡትን የዜና ዘገባዎችን ማሰራጨት ለሪፖርተር አይጠበቅበትም፤ አፈ-ሰማይ የሆነው የማኅበራዊ ሚዲያ ተቀላቢ፤ ይህ ሁሉንም ማለትም በመንግሥትም፣ በግልም፣ በግብፅም፣ በሻዕቢያም፣ ወዘተ … [Read more...] about ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ
የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች
የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢ ስለሆኑት የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶችና የንግድ ተቋማት ሲነሳ ግንኙነታቸው “በሬ ካራጁ” እንደሚሉት ዓይነት መሆኑን መጠቆም ጉዳዩን ምን አልባትም ማሳነስ ካልሆነ በቀር አይበዛም። ምክንያቱም አውሬው ኦሮሚያ ላይ በተቀመጡ የትህነግ ቅምጦች አማካይነት መረጃ እየተቅበለ በተሰጠው የቤት ሥራ መሠረት ኃላፊዎችን እያንገዋለለ ያስጠበጥብ ስለነበር ነው። በዘመነ ት ህነግ ሪፖርተር ኦሮሚያ ላይ የሠራው ሤራና አሻጥር በዚህ አጭር ጽሑፍ የሚገለጽ አይደለም። ትህነግ ኦሮሚያን የተቆጣጠረው በሪፖርተር አማካኝነት ነበር ቢባል ምንም ማጋነን አይሆንም። በኦሮሚያ ላይ የሚከናወኑ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ፣ የኢኮኖሚ ጉዳዮች መረጃ ይጠባ የነበረው ሪፖርተር ነበር። ለምሳሌ፤ ኢህአዴግ ሥልጣን ላይ በነበረ ጊዜ፤ በተዋረድ የተቀመጡ የትህነግ ካድሬዎችና ሰላዮች ጥይት በማቀበል … [Read more...] about የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች
የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
የሪፖርተርን እና የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የ“በሬ ካራጁ” አዋዋል በአንድ ታሪክ እናብራራው … አንድ አውራ ዶሮ የነበረው አንድ ሰነፍ ገበሬ ነበር፤ ገበሬው ይህንን አውራ ዶሮ ከገዛበት ቀን ጀምሮ ዶሮውን ለመብላት የሚመኝ አንድ ኮሳሳ ቀበሮ በገበሬው ቤት ሁልጊዜ ያንዣብባል፤ በሰፈሩ እየዞረም “ዶሮው ታምሟል፤ ጠዋት ይሞታል” እያለ ቀበሮው ለሰፈረተኛው በሙሉ ያወራል፤ የሚወራበትን ያልሰማው ወይም ጆሮ ዳባ ያለው ሰነፍ ገበሬም ጉዳዩን ከመጠየቅና ከማጣራት ይልቅ “ቀበሮው መዞር ከጀመረ አንድ ቀን ሆነው፤ አንድ ሳምንት ሆነው፤ 15 ቀን ሆነው፤ … መቼም ቢርበው ነው” እያለ ያገኘውን ሥጋ ሲመግበውና የዙረቱን “በዓል” ሲያከብርለት ከሰነበተ በኋላ ቀበሮው በደንብ ሲጠበድል ዶሮውንም ያበላውን ገበሬም ሰለቀጣቸው። በኢትዮጵያ በነጻ ሚዲያ ስም በነጻነት እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ሪፖርተር … [Read more...] about የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ
በ1930ዎቹ የጀርመን ወግ አጥባቂ ልሒቃን በሀገራቸው እያቆጠቆጠ ያለው ኮሙኒዝም አስፈራቸውና አንድ “መላ” ዘየዱ። በሕዝብ ዘንድ ዝና እያገኘ የመጣውን አዶልፍ ሒትለርን ወደ ሥልጣን ማምጣትና ኮሙኒዝምን ድባቅ መምታት። ውሳኔ ተላለፈ፤ ሒትለርም የፓርቲው ካዝና፣ ቁልፍ፣ ወንበር፣ … ሁሉም ተሰጠው። አጅሬውም ወዲያውኑ የራሱን መስተጋብር በመፍጠር ያበላውን ፓርቲ መልሶ መውጋት ጀመረ። የናትዚው “አውሬ” ሒትለር የዴሞክራሲ መዋቅሮችን አፈራረሰ፣ የተቃዋሚ እንቅስቃሴዎችን አገደ፣ የቀድሞ አጋሮቹን በሙሉ አጸዳና ሥልጣኑን በኪሱ አስገባ። ነፍሰበላ አውሬ እየቀለቡ መሆናቸውን ያልተገነዘቡት ወግ አጥባቂዎቹ ባሳደጉት “ውሻ” ተበሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ሒትለር እየተቀለቡ ያሉና አንድ ቀን ሊበሉን ያሰፈሰፉ፤ የበሉበትን ወጭት ሰባሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ያበላቸውን የሚበሉ ወይም ሊበሉ እያደቡ ያሉ … [Read more...] about የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ
አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ
ሪፖርተር በሌላ ሐሰተኛ መረጃ በማሰራጨት በኃላፊነት ተጠየቀ፤ ይህንን የጠየቀው የአዲስ አበባ አስተዳደር ሲሆን ሪፖርተር መረጃውን ካላስተካከለ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል። መግለጫው ከዚህ በታች ይገኛል:- ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ፣ የተዛባና ሚዛናዊነት የጎደለው መረጃን ግልፅ ስለማድረግ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በመጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም "በማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የባለድርሻ አካላትን ግንዛቤና ተሳትፎ ማሳደግን" አላማው ያደረገ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ማዘጋጀቱ ይታወሳል። መድረኩ የታለመለትን አላማ እንዲያሳካም በእለቱ የውይይት መድረኩን እንዲዘግቡ በጽ/ ቤታችን ከተጠሩት ከ15 በላይ የሚሆኑ የመደበኛና የዲጂታል ሚዲያዎች ተገኝተው ዘገባቸውን … [Read more...] about አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ
ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዚህ በጀት ዓመትም ሆነ ከዚያ በፊት አንድም ብር ለመንግሥት በቀጥታ አበድሮ እንደማያውቅ አስታውቋል። ጉዳዩን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተሰጠው መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፡- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለመንግሥት አንድም ብር አበድሮ አያውቅም! የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዚህ በጀት ዓመትም ሆነ ከዚያ በፊት አንድም ብር ለመንግሥት በቀጥታ አበድሮ አያውቅም። መንግሥት ከሀገር ውስጥ የንግድ ባንኮች (በብሔራዊ ባንክ በኩል ለሽያጭ ከሚቀርበው የግምጃ ቤት ሰነድ ግዢ ውጪ) በቀጥታ የመበደር አሠራርም ሆነ ልምድ የለውም። ሀቁ ይህ ሆኖ ሳለ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዚህ በተገባደደው ሳምንት ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የስምንት ወራት የስራ አፈጻጸም ማቅረባችንን ተንተርሶ በሪፓርተር … [Read more...] about ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ
የኅቡዕ ቡድን ሪፖርት በኅቡዕ በሚሠሩ “ኢትዮጵያውያን” – ኢትዮጵያ ላይ የተመዘዘ ሰይፍ!
የስሙ መነሻ ግንድ የሚመዘዘው ከላቲን ነው። “vates” ይባላል። ትርጉሙም “prophet” ነቢይ፣ ወይም Fortune teller ትንቢት አብሳሪ፣ የወደፊቱን ገላጭ እንደ ማለት ነው። ስሙንም ስያሜውንም ጠቅሶ ማብራሪያ ያኖረው ራሱ ቡድኑ ሲሆን ከስሙ ለመረዳት እንደሚቻለው “ሰማያዊ ቅባትን” ራሱ ላይ ደፍቷል። የአደባባይ የድረገጹ ስምና መገኛው vatescorp.com ነው። ምርመራና የሥጋት ቅድመ ትንተና ማድረግ ዋናው የሥራው የጀርባ አጥንት እንደሆነ የሚጠቁመው ይኸው ቡድን ከስያሜውና ለራሱ ከሰጠው የነቢይነት አክሊል ውጪ ሌላ ዝርዝር የማንነት መገለጫ ስለሌለው ጥሞናን ለሚያስቀድሙ ዜጎች ሁሉ “ማነህ ነቢዩ? እነማን ናችሁ ትንቢት አብሳሪዎቹ?” ወዘተ የሚል ጥያቄ እንዲያነሱ አስገድዷቸዋል። ይህ ግራ አጋቢነቱ ቀድሞ መነጋገሪያ የሆነበት ማኅበር፣ ቡድን፣ የመናፍስት … [Read more...] about የኅቡዕ ቡድን ሪፖርት በኅቡዕ በሚሠሩ “ኢትዮጵያውያን” – ኢትዮጵያ ላይ የተመዘዘ ሰይፍ!
ቀሲስ በላይን ፊት አድርጎ የተሞከረው የማጭበርበር ሤራ ከሸፈ
* ሚዲያው አስቀድሞ ዝግጅት አድርጎበታል ቀሲስ በላይን ግንባር አድርጎ አፍሪካ ኅብረትን ለመዝረፍ የተወጠነው ሤራ መክሸፉ አርብ ዕለት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አለሳልሶ ይፋ አድርጎታል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃላ አቀባይ አቶ ነቢዩ ተድላ “ጉዳዩ በሕግ ያለ ነው። ዝርዝር ልንናገር አንችልም። የተሞከረው ጥቃት ግን ከሽፏል። ጉዳዩ ወደ ሌላ ደረጃ ሳያልፍ ወይም ጉዳት ሳያስከትል ለመቆጣጠር ተችሏል” ማለታቸው ጉዳዩ ሤራ መሆኑን ያመላክታል። “ከኅብረቱ ጋር ባደረግነው ቀጥተኛ ውይይት ይህ አይነት እሳቤ በተቋሙ ውስጥ እንደሌለ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች አረጋግጠዋል” ሲሉ በመግለጫቸው ያመለከቱት አቶ ነቢዩ ጉዳዩ ሕግ የያዘው በመሆኑ ዝርዝር ለመስጠት እንደማይችሉ ገልጸዋል። የጎልጉል የአዲስ አበባ ተባባሪ ዜናው ከተሰማበትና ሪፖርተር ጋዜጣ በአማርኛና በእንግሊዘኛ ሁለት የተለያዩ … [Read more...] about ቀሲስ በላይን ፊት አድርጎ የተሞከረው የማጭበርበር ሤራ ከሸፈ
ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ
የትህነግ ልዩ ዓላማ እየተተገበረ ያለበትን የአማራ ክልል ቀውስ ለማስታገስ የወጣው የአስቸኳይ አዋጅ ከመጽደቁ በፊት ሪፖርተር ጋዜጣ የድምጽ ስሌት አቅርቦ የአማራ ብልጽግና ከዋናው ብልጽግና የተለየ አቋም እንዲይዝ የቢሆን ስሌትና ምኞት ያለበት ዜና አሰራጨ። አብንና ኢዜማንም ደምሯል። ምንም እንኳን በሪፖርትር ስሌትና "የቢሆንልኝ" ምልከታ የድምጽ መመጣጠን ሊፈጠር የሚችልበት አጋጣሚ ሊታሰብ እንደማይችል የገለጹ እንደሚሉት፣ የዜናው ምኞትና አቅጣጫ ትህነግ የሚከተለውን "በብሄር አስብ" የሚለውን ርዕዮት የሚያንጸባርቅና አማራ ክልል በዚህ ቀጥሎ በሁከት ሲናጥ ትህነግ የከሰራቸውን ኪሳራዎች መልሶ እንዲያገኝ ለሚያደርገው ዝግጅት መንገድ ለመጥረግ እንደሆነ አመልክተዋል። "... በሚኒስትሮች ምክር ቤት የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክር ቤቱ በሁለት ሦስተኛ ድምፅ ማፅደቅ … [Read more...] about ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ








