• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

Religion

ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ

May 9, 2022 01:46 pm by Editor Leave a Comment

ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ

በሴቶች ጭፈራ ደምቆ በወንዶች የሚታጀበው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራን ለማስተዋወቅ የሁለት ቀን ፌስቲቫል በደሴ ከተማ ተካሂዷል። እራሷን ተሰርታ ወለባ ስጋለች፣ እንሶስላ ሙቃ ሎሚ ጨብጣለች፣ ያች ያገሬ ልጅ እሷዉ ትሆናለች። ሲሉ ጨዋታውን ደመቅ ያደርጉታል የወሎ ወይዛዝርት። ታዲያ በዚህ ጭፈራ ጊዜ ወንዶቹ ሴቶቹን ተቀላቅለው ጭፈራውን ደመቅ ያደርጉታል። አኾላሌ በሃይማኖታዊና ሃይማኖታዊ ባልሆኑ ክብረ በዓላት የሚከናወን ብዙ ጊዜ ጥር ወር ላይ በአርሶ አደሩ የዕረፍት ወቅት፣ በመተጫጫና ጋብቻ እንዲሁም የመዋቢያ ጊዜ የሚከናወን ባህላዊ ጨዋታ ነው። በአብዛኛው በወሎ በተለይም በተውለደሬ የሚከወነው ተዉኔት አዘል ባህላዊ የወጣቶች ጭፈራ ሃይማኖት ሳይለይ በክርስትናም በእስልምና ተከታዮችም ይካሄዳል። አሆላሌ ባህላዊ ጨዋታ የራሱ የኾነ የመከወኛ አጋጣሚዎች እና ወቅቶችም … [Read more...] about ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ

Filed Under: Religion, Right Column, Social Tagged With: Aholale, Carnival, Cultural Event, Wollo

“ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ተቀራርበን እንሠራለን” የከተማ አስተዳደሩና ቤተክርስቲያኗ

February 15, 2022 09:47 am by Editor Leave a Comment

“ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ተቀራርበን እንሠራለን” የከተማ አስተዳደሩና ቤተክርስቲያኗ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዛሬው ዕለት ውይይት አድርገዋል። ከውይይታቸው በኋላም የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል። የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል። ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ እና ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጋራ የተሰጠ መግለጫ በዛሬው እለት የካቲት 8 ቀን 2014 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በመስቀል አደባባይና በጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት ቦታዎች በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ የጋራ ውይይት አድርገናል፡፡ ውይይቱ በፍጹም ቅን ልቡና፣ መደማመጥና መግባባት በተሞላበት ስሜት ተካሂዷል፡፡ በመሆኑም በውይይቱ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመስቀል አደባባይና … [Read more...] about “ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ተቀራርበን እንሠራለን” የከተማ አስተዳደሩና ቤተክርስቲያኗ

Filed Under: Middle Column, News, Religion Tagged With: Abune Mathias, Adanech Abebie, addis ababa is a city state, EOTC

የዛሬ ዓመት በማይካድራ በተፈጸመው የዘር ጭፍጨፋ

November 9, 2021 10:38 am by Editor 1 Comment

የዛሬ ዓመት በማይካድራ በተፈጸመው የዘር ጭፍጨፋ

• አንድ ሺ 564 ሰዎች በጭካኔ ተገድለዋል። • 81 ሰዎች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል። • ድርጊቱን የፈጸመው አሸባሪው ሕወሓት ያደራጀው ሳምሪ የሚባል ገዳይ ቡድን ነው። የዛሬ ዓመት በማይካድራ በተፈጸመው የዘር ጭፍጨፋ አንድ ሺ 564 ሰዎች በጭካኔ መገደላቸውን፤ 81 ሰዎች ከፍተኛ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑን ድርጊቱን የፈጸመው አሸባሪው ሕወሓት ያደራጀው ሳምሪ የሚባል ገዳይ ቡድን መሆኑን በጎንደር ዩኒቨርሲቲ መምህርና ወልቃይት፣ ጠገዴና ጠለምት የጥናት ቡድን መሪ ገለጹ። የጥናት ቡድኑ መሪ አቶ ጌታ አስራደ አለማየሁ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የዛሬ አመት በማይካድራ ጭፍጨፋውን ያካሄዱት ሳምሪ የተባለ አሸባሪው ሕወሓት ያደራጃቸው ገዳይ ቡድን ነው። ይህ ቡድን አንድ ሺ 564 ሰዎችን መጥረቢያ፣ ቆንጨራና፣ ቢለዋ፣ ማጭድና መሰል … [Read more...] about የዛሬ ዓመት በማይካድራ በተፈጸመው የዘር ጭፍጨፋ

Filed Under: Middle Column, News, Religion Tagged With: mia cadra, miacadra massacre, operation dismantle tplf, tplf terrorist

ስለ አገር ሰላምና አንድነት የ5 ቀናት ፀሎትና ምህላ ታወጀ

September 5, 2021 06:50 pm by Editor Leave a Comment

ስለ አገር ሰላምና አንድነት የ5 ቀናት ፀሎትና ምህላ ታወጀ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በጳጉሜ ወር ለሀገር ሰላም እና አንድነት በመላው ዓለም በምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፀሎት እና ምህላ ወስኗል። ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ፣ ጌዴኦ አማሮና ቡርጂ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፥ ቋሚ ሲኖዶሱ 5ቱን የጳጉሜ ቀናት በፀሎትና ምህላ እንዲታሰብ መወሰኑን ገልፀዋል። ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ፥ 2013 ዓ.ም ብዙ ችግሮችን ያሳየ መሆኑን ያነሱ ሲሆን "በፈተናው ውስጥም ቢሆን ግን ብዙ በረከቶችን ያሳየን ነገሮች አሉ" ብለዋል። እንደሀገር፤ እንደዓለምም የተከሰቱ ችግሮች ወደቀጣይ ዓመት አብረው እንዳይተላለፉ እግዚአብሔርን በፀሎት መጠየቅ ስላለብን ይህ ውሳኔ ተላልፏል ሲሉ አስረድተዋል። አክለውም፥ "ቤተክርስቲያን በሀገራችን ውስጥ ያለው ጦርነቱ፣ ረሃቡ፣ ስደቱ፣ … [Read more...] about ስለ አገር ሰላምና አንድነት የ5 ቀናት ፀሎትና ምህላ ታወጀ

Filed Under: Middle Column, News, Religion Tagged With: operation dismantle tplf

ትህነግ ቤተ እምነቶችን እንደ ጦር ካምፕ እየተጠቀመባቸው ነው

September 3, 2021 02:05 pm by Editor Leave a Comment

ትህነግ ቤተ እምነቶችን እንደ ጦር ካምፕ እየተጠቀመባቸው ነው

የህወሓት የሽብር ቡድን በወረራቸው አካባቢዎች አብያተ ክርስቲያንን እና መስጅዶችን ከማውደም ባሻገር እንደ ጦር ካምፕ እየተጠቀመባቸው መሆኑን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ። የአማራ ክልል የሃይማኖት ተቋማት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የውይይት መድረክ በባህርዳር እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ ንግግር ያደረጉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ የህወሓት የሽብር ቡድን በኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት ላይ የጋረጠውን የኅልውና አደጋ ለመቀልበስ ኅብረተሰቡ በኅልውና ዘመቻው እንዲሳተፍ የሃይማኖት አባቶች የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። የህወሓት የሽብር ቡድን ለመደምሰስ በሚደረገው ጥረት የሃይማኖት አባቶች የሚጠበቅባቸውን እየተወጡ መሆኑን የክልሉ መንግሥት በአድናቆት ይመለከተዋል ሲሉም ተናግረዋል። ነገር ግን ጥቂትም ቢሆኑ ሽማግሌ በመምሰል ለህወሓት … [Read more...] about ትህነግ ቤተ እምነቶችን እንደ ጦር ካምፕ እየተጠቀመባቸው ነው

Filed Under: News, Religion, Right Column, Social Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

የማይካድራ ዕልቂት

November 12, 2020 04:03 am by Editor 1 Comment

የማይካድራ ዕልቂት

በምዕራባዊ ትግራይ ሁመራ አቅራቢያ «ማይካድራ» በተባለው አካባቢ የትግራይ ልዩ ኃይል ባልታጠቁ የአማራ ተወላጆች ላይ በሌሊት አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን ከሞት ያመለጠ የዐይን እማኝ ገለፀ። ጥቃቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው ሲል ደግሞ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ዐስታውቋል። በምዕራባዊ ትግራይ ሁመራ አቅራቢያ «ማይካድራ» በተባለው አካባቢ የትግራይ ልዩ ኃይል ባልታጠቁ የአማራ ተወላጆች ላይ በሌሊት አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን ከሞት ያመለጠ የዐይን እማኝ ገለፀ። ጥቃቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው ሲል ደግሞ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ዐስታውቋል። ድርጊቱ የተጀመረውን ሕግ የማስከበር ሂደት ህወሓት ወደ የእርስ በእርስ ጦርነት እንዲቀየር የዘየደው መላ ነውም ብሎታል። አንዳንድ የአማራ ክልል ነዋሪዎች የህወሓት የተስፋ መቊረጥ ስሜት ነው፤ ኅብረተሰቡ ህወሓት በዘየደው የብቀላ ሂደት … [Read more...] about የማይካድራ ዕልቂት

Filed Under: News, Religion, Right Column Tagged With: operation dismantle tplf

የጆካ ዳኞች ባህላዊ የዳኝነት ሥነ-ሥርዓት

October 20, 2020 12:12 pm by Editor 1 Comment

የጆካ ዳኞች ባህላዊ የዳኝነት ሥነ-ሥርዓት

ቒጫ የጉራግኛ ቃል ሲሆን ጥሬ ትርጉሙም ደንብ፣ ስርዓት፣ ህግ ማለት ነው፡፡ የጉራጌ ህዝብ ባህላዊ ስርዓት ህግ ራሱን በራሱ መገልገል የጀመረው በስሙ እየተጠራ ባለበት ሀገር ከሰፈረበት ዘመን ጀምሮ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ይሁን እንጂ ህብረተሰቡ በየክፍሉ የሸንጎ ማእከላት በክፍለ ህዘብ ምድብ ባለበት ሁሉ የስሙ አሰያየሙ ይለያያል፡፡ መደበኛ ህግ ክፍሎች አሉት፡፡ የፍትሃብሄር፣ ወንጀለኛና የቤተሰብ (የጋብቻ) ስነስርዓት (ህግጋት) በውስጡ ይዟል፡፡ ይኽውም፡- የአንቂት ቒጫ - ይህ ደንብ በአጠቃላይ የጋብቻና የፍቺ ስነስርዓት የተደነገገበት ሲሆን የአተጫጨት፣ የቸግ ወይም የኒካ የሰርግ እና ፍቺ አፈጻጸም የሚዳኝበት ስርዓት (ደንብ) ነው፡፡የቅየ ቒጫ - ይህ ደንብ በሁለት ወሰንተኞች መካከል የድንበር መገፋፋት እንዳይኖር በሁለት ወገኞች ስምምነት በሚመረጡ ሽማግሌዎች አማካይነት … [Read more...] about የጆካ ዳኞች ባህላዊ የዳኝነት ሥነ-ሥርዓት

Filed Under: Left Column, Religion, Social Tagged With: Ethiopia, guragie, jokka, qichaa

የኢሬቻ በዓልን ለመረበሽ የተዘጋጁ 503 ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

October 2, 2020 12:01 pm by Editor Leave a Comment

የኢሬቻ በዓልን ለመረበሽ የተዘጋጁ 503 ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

መስከረም 23 እና 24 የሚከበረውን የኢሬቻ በአል ለመበጥበጥ የተዘጋጁ 503 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ መሳሪያም ተገኝቶባቸዋል። የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ኮማንደር አራርሳ መርዳሳ ትላንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለፁት፤ የኢሬቻ በዓል ላይ የሚሳተፉ የበዓሉ ታዳሚዎች በሰላም ወጥተው እንዲገቡ ኮሚሽኑ በጥብቅ እየሰራ ነው። የግል ፍላጎታቸውን ለማሳካት በተለያየ አቅጣጫ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ሀይሎች እንዳሉና ኮሚሽኑም እንደደረሰባቸው የገለፁት ኮማንደሩ፤ እስካሁን ድረስ 503 ሰዎች፣14 ክላሽ ፣ 26 ቦምብ እና 103 ሽጉጦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል፡፡ ከኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው የኢሬቻ በዓል በኮረና ምክንያት እንደ ከዚህ ቀደሙ በርከት ባለ ሰው የማይከበር ሲሆን በገዳ … [Read more...] about የኢሬቻ በዓልን ለመረበሽ የተዘጋጁ 503 ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

Filed Under: Left Column, News, Religion Tagged With: Ethiopia, irechaa, terrorism, tplf

ኦሮሞዎች በየዓመቱ ለሚያከብሩት ኢሬቻ በዓል ቦታ ተሰጠ

September 18, 2020 07:09 pm by Editor 9 Comments

ኦሮሞዎች በየዓመቱ ለሚያከብሩት ኢሬቻ በዓል ቦታ ተሰጠ

የኦሮሞ ተወላጆች በየዓመቱ ለሚያከብሩት የኢሬቻ በዓል መከበሪያ ቦታ በአዲስ አበባ መስጠቱን አስተዳደሩ አስታወቀ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኢሬቻ በዓል (ሆረ ፊንፊኔ) ማክበሪያ ቦታ የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ለአባገዳዎች በዛሬው ዕለት አስረክቧል። ከዚህ በተጨማሪ ዛሬ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓሉ የሚከበርበትን ቦታ ከአባገዳዎች ጋር በመሆን በመጎብኘት ዝግጁነቱን አረጋግጠዋል። በኮቪድ-19 ምክንያት የዘንድሮ በዓል በአባገዳዎች በሚወሰን ትንሽ የሰው ቁጥር ብቻ እንደሚከበር ከስምምነት ላይ መደረሱን ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳውቀዋል። የኢሬቻ በዓል ከገዳ ሥርዓት ጋር የተጣመረ ነው፤ ይህም ሃይማኖታዊ ክብረበዓል የገዳን ሥርዓት ሃይማኖታዊ ያደርገዋል፤ ስለዚህ የገዳ ሥርዓት እንደ ትምህርት በመንግሥት ትምህርት ቤቶች መሰጠት አይገባውም … [Read more...] about ኦሮሞዎች በየዓመቱ ለሚያከብሩት ኢሬቻ በዓል ቦታ ተሰጠ

Filed Under: Left Column, News, Religion

ጠቅላይ ቤተ ክህነት፤ በኦሮሚያ የተፈጸመው ኦርቶዶክሳውያንን የማጽዳት እንቅስቃሴ ነው

September 1, 2020 11:55 am by Editor Leave a Comment

ጠቅላይ ቤተ ክህነት፤ በኦሮሚያ የተፈጸመው ኦርቶዶክሳውያንን የማጽዳት እንቅስቃሴ ነው

የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ጥያቄዎቿን እንዲቀበላት ጠየቀች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሱ ያሉ ተደጋጋሚ ጥቃቶች እንደሚነገረው “በሽግግር ወቅት የሚያጋጥሙ” ተብለው ብቻ የሚታለፉ ሳይሆኑ፣ የተሳሳቱ ርዕዮተ ዓለማዊ ትርክቶችንና ጂኦ ፖለቲካዊ ዳራዎችን መነሻ በማድረግ በተቀነባበረና በተደራጀ ሥልት የሚፈጸሙ ኦርቶዶክሳውያንን የማፅዳት እንቅስቃሴዎች መሆናቸውን ቤተ ክህነት ገለጸች። የኦሮምኛ ቋንቋ ድምፃዊው ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ምክንያት በማድረግ በኦሮሚያ በተለያዩ አካባቢዎች በስድስት ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙ 25 ወረዳዎች በሚኖሩ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የገለጸችው ቤተ ክህነት፣ በጥቅምት ወርና በጥር ወር ከጥምቀት በዓል አከባበር ጋር በተያያዘ እንዲሁም በሃጫሉ ሞት ምክንያት በአቢያተ ክርስቲያናትና … [Read more...] about ጠቅላይ ቤተ ክህነት፤ በኦሮሚያ የተፈጸመው ኦርቶዶክሳውያንን የማጽዳት እንቅስቃሴ ነው

Filed Under: Left Column, Religion Tagged With: jawar massacre, oromia, orthodox church

  • Page 1
  • Page 2
  • Next Page »

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule