* "እኛ የገባነው ልናፈርሰው ነው" ሕዝቅኤል ገቢሣ በሰላማዊ ትግል መንግሥት ለመጣል ማቀዱን አስታውቆ ሃያ አንድ ቦርድ አባላትን ሰይሞ የሰነበተው የ-አብሮነት ማኅበር ሰባት ሥራ አስፈጻሚዎችን መምረጡ ታወቀ። ማኅበሩ “ለቦርድ አባላት” በሚል ባሰራጨው የ“እንኳን ደስ አላችሁ” መልዕክት አቶ ልደቱ፣ ከአማራ የማኅበሩ ፕሬዚዳንትና ሊቀመንበር ሆነዋል። መቅደስ አዳነ ከወላይታ (ምክትል)፣ አሸናፊ አብርሃም ከደቡብ (ጸሐፊ)፣ ሙሉጌታ ዘለቀ ከአማራ (ገንዘብ ያዥ)፣ የሕዝብ ግንኙነት ኦፊሰር ሕዝቅኤል ገቢሣ /በተለይ እንግሊዘኛና ትግርኛ ጠንቀቀው ስለሚያውቁ/ ከኦሮሞ፣ የድርጅት አስተባባሪ እስማኤል ጎርሴ ከሶማሌ፣ የውጭ ግንኙነት ኦፊሰር መስፍን አየነው ከትግራይ መመረጣቸው ይፋ አድርጓል። ቀደም ሲል ምርጫው ከመደረጉ በፊት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አባላቶች ሕቡዕ እንደሚሆኑ … [Read more...] about የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ
operation dismantle tplf
አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው
አምስተርዳም ይካሄዳል ተብሎ በውጭ አገር በሚኖሩ በተለያዩ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች የተሰራጨው የሽግግር መንግሥት ምስረታ ጉባኤ ከአሜሪካ ወደ አምስተርዳም ያመራው አሜሪካ ጥያቄውን ባለመቀበሏ መሆኑ ተሰማ። ስብሰባው ከጀርባው ሆነው የሚመሩትና ሻዕቢያና ሌሎች ፍላጎት ያላቸው የሚታወቁ አካላት እንደሆኑም እየተነገረ ነው። የቀድሞ የትህነግ አመራርና አሁን ላይ “ቪዥን ኢትዮጵያ” ከሚባለው አደረጃጀት ጋር እየሠሩ ያሉት አቶ ግደይ ዘርዓጽዮን በግል የኢሜል አድራሻቸው “ለስብሰባው ተዘጋጁበት” ሲሉ ያሰራጩት ሰነድ ጉባዔው ለምን ወደ አምስተርዳም እንደተዛወረ፣ ወይም አምስተርዳም ለምን እንደተመረጠች አያስረዳም። ይህንኑ አስመልክተን ተጋባዥ ከሆኑት መካከል የአዲስ ሪፖርተር የዋሽንግቶን ተባባሪ ያነጋገራቸው “ቅድሚያ ዕቅዱ ስብሰባውን በአሜሪካ ለማድረግ ነበር፤ ምላሹ ጥሩ ባለመሆኑ ወደ … [Read more...] about አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው
“በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ
ሃራ ወይም ነጻ ተብሎ በሚጠራው መሬት ላይ ሠፍሮ የሚገኘው "የትግራይ የሰላም ኃይሎች" (TPF) ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ኃይል በያዝነው ዓመት መጨረሻ ሙሉ ትግራይን እንደሚቆጣጠር አስታወቀ። "ጸጥተኛ" ብለው ለሚጠሩት አቢዮት ሠራዊቱ እየተዘጋጀ እንደሆነም ተነግሯል። ይህ የተገለጸው በፈረንሳይኛ ቋንቋ በድረገጽ የሚታተመውና አፍሪክ XXI (Afrique XXI) የተባለው ጋዜጣ ከጥቂት ቀናት በፊት በትግራይ ላይ በሠራው ዘገባ ነው። ዘገባው በሃራ ምድር የሰፈሩትን የትግራይ የሰላም ኃይል/ቲፒኤፍ ተብለው ከሚጠሩት ታጣቂዎች ጋር ቃለ ምልልስ ካደረገ በኋላ ነው። የሰላም ኃይሉ አባላት በአብዛኛው ከዚህ በፊት በትህነግ ሥር ከነበረው የትግራይ መከላከያ ኃይል ወይም ቲዲኤፍ (TDF) ከሚባለው ከድተው የወጡ ናቸው። በተለይ ካለፈው መጋቢት ወር ጀምሮ በብዛት ከቲዲኤፍ እየኮበለሉ ወደ አፋር … [Read more...] about “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ
Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women
Warning: this article contains extremely graphic and distressing testimony and images For two years, Tseneat carried her rape inside her. The agony never faded. It attacked her from the inside out. The remnants of the attack stayed in Tseneat’s womb – not as a memory or metaphor, but a set of physical objects: Eight rusted screws. A steel pair of nail clippers. A note, written in ballpoint pen and wrapped in plastic. “Sons of Eritrea, we are brave,” the note reads. “We have … [Read more...] about Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women
የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ
በቅርቡ “ሰማይ አንቀጥቅጥ” በሚል ስያሜ ተካሂዶ በቅብብሎሽ “የሻዕቢያ ተቀጣሪዎች” እና አፍቃሪ የትህነግ ሚዲያዎች ያራገቡት የበይነ መረብ ትዕይንት በዋናት የሻዕቢያና የበረከት ስምዖን ሤራ እንደሆነ ተሳታፊዎች አመልከቱ። ርዕዮት ዩቱብ ልዩ ገጸ ባህርይ ተዘጋጅቶለት ድራማውን ከልደቱ ጋር እንዲተውን የተደረገው ሆን ተብሎ እንደሆነም ተጠቁሟል። በአደባባይ ትህነግና ሻዕቢያን ለጆሮ በሚከብድ ቃላት የሚሳደበው የርዕዮት ዩቱብ ባለቤት ቴዎድሮስ ጸጋዬ ይህንን ገጸ ባህርይ እንዲጫወት የተደረገው ሆን ተብሎ ነው። የዜናው ባለቤቶች እንደሚሉት ቴዎድሮስ ከማንነቱ የተነሳ ለድራማው ተመራጭ አድርጎታል። ይህ ተፈጥሮው ታማኝ ስለሚያስመስለው ድራማውን በደንብ እየተጫወተ መሆኑም ተመልክቷል። የቴዎድሮስ ገጸ ባህሪ ልክ ልደቱ በ1997 ሕዝብ ጉድ እስኪል ኢህአዴግን እየተሳደበ በመጨረሻ ይፋ ከሆነው … [Read more...] about የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ
“ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ)
ልደቱ አያሌው ከቴዎድሮስ ጸጋዬ ጋር ያስተባበረው “አየር አንቀጥቅጥ” ትዕይንት ቅዳሜ ቀን ተካሂዷል። ልደቱ በስተመጨረሻ እንዳለው ከታሰበው በላይ የተሳካው የአየር ትዕይንት 15 ሰዎች ተናግረዋል፤ ሕዝብ በሳተላይት እና በተገኘው መንገድ ሁሉ ሰምቷል ብሏል። አገዛዙ ፈርቶ ኢንተርኔት አፍኗል፤ ዳታ ታቅቧል፤ ዩትዩብ እንዳይሠራ ተደርጓል ብለው ልደቱም፣ ቴዎድሮስም እየደጋገሙ ሲናገሩ ተሰምተዋል። ይህ የአየር ላይ ትዕይንት “ስልቴዎች” ማለትም ስብሃት፣ ልደቱ፣ ቴዎድሮስ በልዩ ሁኔታ የቀመሩትና ትህነግን በመታደግ ለሻዕቢያ የተሠራ ልዩ የስልቴዎች ስልት ነው። ንግግር ያደረጉት ሰዎች ጥቂቶቹን ስንቃኝ፤ … የድግሱ መሪ ቴዎድሮስ መደረጉ በራሱ ብዙ የሚለው ነገር አለ። ቴዎድሮስ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ወገኖቼን (የትግራይ ተወላጆችን በተለይም ወያኔዎችን) የፈጀች ኢትዮጵያ ጥንቅር … [Read more...] about “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ)
ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …?
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ “አሉኝ” የሚላቸውን መረጃዎች የሚያሰራጭበት ሚዲያ በመኖርና በመጥፋት መካከል እንደሆነ ጠቅሶ የተለያዩ አማራጮችን ሲያቀርብ የነበረው ኤሊያስ መሠረት በተቃውሞ ሽፋን ለብልጽግና እየሠራ እንደሆነ መቅመጫቸውን ኬኒያ ያደረጉ ክፍሎች ገልጸዋል። በአገር ቤት ያሉና ይህንኑ ዜና የሚደግፉ ተጨማሪ ማስረጃዎችን በመገጣጠም ዜናውን አጉልተዋል። ኤሊያስ መሠረት በተቃውሞ ሽፋን ለብልጽግና እንደሚሠራ መረጃ የሰጡት ክፍሎች ኤሊያስ መሠረት ናይሮቢ በከተመበት ወቅት በቅርበት የሚያውቁት ናቸው። ትህነግ በሥልጣን በነበረበት ዘመን በሥልት ዜናዎችን ሲያቀዛቅዝና ሲያድበሰብስ ጠንቀቀው የሚያውቁት ወዳጆቹ እንደሚሉት፣ ኤሊያስ መሠረት ወደ ብልጽግና የመሸጋገር ዝንባሌ የታየበት “ትህነግ ዳግም ይመለሳል” የሚለው ምኞቱ ሙሉ በሙሉ መክሰሙን ከተረዳ በኋላ ነው። ለትህነግ … [Read more...] about ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …?
በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ
መለስ ዜናዊ ከስሙ ጀምሮ ሁሉ ነገሩ የውሸት ወይም ፌክ ነው። ላደረሰብን ግፍ እንክሰሰው እንኳን ብንል በየትኛው ስሙ ነው ፍርድ ቤት የምናቆመው የነበረው? ደግነቱ ከዚህ ሁሉ በፊት ወደ ዕረፍቱ ሄዶ እኛንም አሳረፈን። መለስ የዕውቀት ችግር አልነበረውም፤ ዕድሜ ለኢትዮጵያ ከሥር መሠረቱ በነጻ አስተምራዋለች። ንጉሡም ሰው ነው፤ ነገ ሀገር ይጠቅማል ብለው ሸልመውታል ይባላል። ግን ያልታከመና ሥር የሰደደ የበታችነት ስሜት የነበረው፣ አስተሳሰቡ ደሃ የሆነ ሰው ነበር። በዚህ ደሃ አስተሳሰቡ ነበር ኢትዮጵያን ለመምራት ሥልጣን ኮርቻ ላይ የተፈናጠጠው። ሥልጣን፣ ሃብት፣ ድሎት፣ ወዘተ ቢመጣም አስተሳሰብ ደሃ ከሆነ ችግሩ ውስብስብና መፍትሔ ዓልባ ነው የሚሆነው። መለስ ኢትዮጵያን በጣም ነበር የሚጠላት፤ ለማፍረስ ይፈልግ ነበር ለማለት ብዙም አያስደፍርም። ነገርግን ልክ እንደ … [Read more...] about በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ
ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት”
የዛሬ አምስት ዓመት ግድም ነው። የሚያምሩ ሁለት ሸበቶ እናቶችን ጨምሮ ተገልጋዮች ይበላሉ። ይጠጣሉ። ያነሳቸውን ይጠይቃሉ። የወቅቱ የኢሳት ባልደረቦችም በአንድ ኮርነር ክብ ሰርተው የሚበላወንም የሚጠጣውንም በዓይነት ሤራ እያዋለዱ ይጠዘጥዛሉ። ቨርጂኒያ ዳማ ሆቴል!! በድንገት ሁለቱ ሸበቶ ሴቶች ይነሱና እንደ ብራቅ ይጮሃሉ። ክብ ሰርተው የሚመገቡትን የኢሳት የማታ ማታ ኮማንዶዎች እያመለከቱ እሳት ጎርሰው “አፈር ብሉ፣ እምዬ ማሪያም አፈር ታብላችሁ፤ ሕዝብ እያጫረሳችሁ እናንተ እዚህ ሥጋ ትቆርጣላችሁ። ደም ብሉ …. ” እናቶቹ ስሜታቸውን መቆጣጠር አቅቷቸው “ያዙኝ ልቀቁኝ” አሉ። ወርውረው ለመማታት ገላጋዮችን ታገሉ። ተለምነው። ተገዝተው …. የገባቸው እናቶች። እንደ እኔ ያልደነዘዙ። “ሦስትን ወደ አራት” አስገራሚ ትርክት፣ አስገራሚ ሤራ ነው። ሤራው በርካቶችን የሰለበ … [Read more...] about ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት”
ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው?
ከሰሞኑን ከትግራይ ክልል አንድ ምሥጢራዊ ሰነድ ሾልኮ ወጥቶ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። በማኅበራዊ ሚዲያዎችም በርካቶች እየተቀባበሉት ይገኛሉ። ምሥጢራዊ ሰነዱ ፥ የሕገወጥ የሰዎች ዝውውር (በብዛት ኤርትራውያን በሕገ-ወጥ መንገድ ማዘዋወር የሚመለከት) እና ሌሎችም ጉዳዮች ላይ የተጠና ሰነድ ሲሆን በ4 ክፍሎች የተከፋፈሉ 69 ገፆች አሉት። በሰነዱ በጥናት የተለዩ የወንጀል ተግባራት ፦* ሥልጣን ያለአግባብ በመጠቀም* በወንጀል የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ በመያዝና በማዘዋወር (መኒ ላውንደሪንግ money laundering)* ሰው ማፈንና መሰወር* በሕገወጥ መንገድ ሰዎችን ከአገር ወደ አገር ማዘዋወር* የመንግሥት ስራ ምቹ ባልሆነ መንገድ መምራት* ኃላፊነት ባልተገባ መንገድ በመጠቀም* ሙስናመፈፀማቸውን ያረጋግጣል። በሰነዱ በተጠቀሱ የወንጀል ተግባራት በሠራዊት አመራር ያሉ … [Read more...] about ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው?









