የሰባተኛውን አጠቃላይ ምርጫ ተከትሎ፣ የቀድሞው የአብን ተመራጭና የአሁኑ የኢህአፓ/ትብብር እጩ ተወዳዳሪ የነበሩት ዶ/ር አበባው ደሳለው በሰጡት ቃለ መጠይቅ በምርጫው ማሸነፍ ባለመቻላቸው የተሰማቸውን ጥልቅ ብስጭትና ንዴት ገልጸዋል። እንደ እርሳቸው ተወዳድረው ከትብብሩ እና ከሌሎች ተፎካካሪ ፓርቲዎች በሕዝብ የተመረጡትንም በብልጽግና ችሮታና ድጋፍ የተመረጡ፣ በምርጫ ሳይሆን በቅርጫ ያሸነፉ በማለት ወርፈዋል። ወደ ፓርላማ አለመግባት ትክክለኛ ውሳኔ እንደሆነም ገልጸዋል። ከኢትዮጵያ ኢንሳይደር ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት የተከበሩ አቶ አበባው ብሔር ተኮር ከሆነው አብን ወጥተው ወደ ኢህአፓ የገቡበትን ምክንያት አስረድተዋል። “ኢህፓን የመረጥኩበት ምክንያት ደግሞ እንደሚታወቀው ጠንካራ ታጋዮች የወጡበት ፓርቲ ነው። ለተራ ጥቅም ብለው ለተራ ኢኮኖሚ ጉዳይ ብለው ህሊናቸውን የማይሸጡ … [Read more...] about ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ
operation dismantle tplf
“ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው”
በሀገር ውስጥ ለግማሽ ምዕተዓመት የሽብር ተግባራትን ሲፈጽም የነበረውና ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ/ህወሃት) ተብሎ የሚጠራው ሕገወጥ የአሸባሪዎች ቡድን፤ በፍጥነት ዓለምአቀፍ አሸባሪ ወደመሆን እየተጓዘ እንደሆነ በቅርብ የሚወጡ ሪፖርቶች እየጠቆሙ ነው። በሰኔ ወር 2026 የወጣውን የሚሊተሪ ታይምስ (Military Times) ዘገባ መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ የዜና እንዳለው ዩናይትድ ስቴትስ ጦሯን መቀነሷን ተከትሎ በአፍሪካ የአሸባሪዎች ስጋት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑ ያስረዳል። የአሜሪካ ጦር በአፍሪካ አህጉር ያለውን ውክልና እና የሠራዊት ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱን ተከትሎ፣ በሳህል እና በአፍሪካ ቀንድ አካባቢዎች የጂሃዲስት ቡድኖች ተጽዕኖ እና ጥቃት በአስደናቂ ሁኔታ እያደገ መሆኑን የስትራቴጂክ እና ዓለም አቀፍ ጥናቶች ማዕከል … [Read more...] about “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው”
አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ
በሰሜን ኢትዮጵያ በድጋሚ ግጭት ለመቀስቀስና ቀጣናዊ ሰላምን ለማደፍረስ ከሻዕቢያ ጋር ጽምዶ ፈጥሮ አደገኛ እንቅስቃሴ ላይ በሚገኘው ትህነግ (ህወሃት) አመራሮችና በቅርብ የቤተሰብ አባላቶቻቸው ላይ ያነጣጠረ የቪዛ እገዳ መጣሉን ተከትሎ የአሜሪካ መንግስት በይፋ አስታውቋል። ይህ ውሳኔ ይፋ የሆነው በኢትዮጵያ ውስጥ በሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ የመንቀሳቀስ ፍቃዱ የተሰረዘውና ሕገወጥ ተብሎ የተፈረጀው የትህነግ ታጣቂ ኃይል ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በቅርቡ በፈጠረው ቀጥተኛ የጦርነት ትንኮሳ ሳቢያ ነው። ትህነግ በተደጋጋሚ በቆሰቆሰው የሰሜኑ ጦርነት አንድ ሚሊዮን ያህል የንጹሃን ዜጎች ህይወት መጥፋቱ እንዲሁም በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወገኖች ለከፋ ረሃብና ለስደት መዳረጋቸው እየታወቀ ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ብሎ የሚጠራው አሸባሪ አሁንም ለሰላም እያሳየ ያለው … [Read more...] about አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ
የታርጋ ጫጫታ
የተዛባ እና የተሳሳተ መረጃ በማሰራጨትና ከዚያ በማትረፍ ሕዝብን ማደናገርና ሀገርን መበጥበጥ የገፊና ጎታች ሤራ ዋነኛ አካሄድ ነው። የአርሲው ትንሽ ጋብ ሲል ሰሞኑን ደግሞ የታርጋ ጫጫታ አየሩን ሞልቶታል። በተለይ እንደ ኤሊያስ መሠረት ያሉ ከሙያም፣ ከስብዕና እጅግ በጣም የወረዱ ሰዎች ለሕዝብ ተቆርቋሪ መስለው የሚያሰራጩት መረጃ የብልጽግና ካድሬ እና የመንግሥት መዋቅሩ የተረዳው አይመስልም ወይም ሆን ብሎ እያገዛቸው ነው። ለታርጋ ሃምሳ ስድስት ሺህ ብር እንዲከፍል ሕዝቡ ተገደደ፣ የአይ ኤም ኤፍ ስልታዊ የግብር ስብሰባ ሕዝቡን እያደኸየው ነው፤ እንደ ኬኒያ ሀገሪቱ ልትናወጥ ነው፤ ሆ ብሎ መነሳት አሁን ነው፤ የግፍ አገዛዝ ገመዱን እያጠበቀው ነው፤ በየማኅበራዊ ሚዲያ የሚታየው ጭስ ይህ ነው። አይ ኤም ኤፍ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ለኢትዮጵያ ብድር ለመፍቀድ እና በፊት … [Read more...] about የታርጋ ጫጫታ
ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ
አሜሪካ ያሉት መምህር ፋንታሁን ዋቄ “ለእምነታችሁ በደስታ ሙቱ” ሲሉ መንግሥት እንዲገለብጡ ለአዲስ አበባ፣ ለአሰላ እና ለአዳማ የኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ጥሪ አቀረቡ። መምህር ፋንታሁን ዋቄ “እጃችህ ላይ መድኃኒት አለ” በማለት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኃይማኖት ተከታዮች መንግሥት ላይ እንዲነሱ ጥሪ አቅርበዋል። አሜሪካ ተቀምጠው “የሰማዕታትን ማረፍ በደስታ በማሰብ በክርስትና የሚሞት በዚህ ዘመን መኖሩ እያስደሰተን በማሰብ እንሙት” ብለዋል። “ሞዐ ተዋህዶ” በሚል ስያሜ የሚጠራው የህቡዕ አደረጃጀት መሪ እንደሆኑ የሚናገሩት መምህር ፋንታሁን በቲክቶክ አውድ ሲናገሩ እንደተሰማው “ኃይል የእግዚአብሔር፣ ሠራዊት የጌዲዮን ነው” በማለት የዕምነቱ ተከታዮች “አሁን ብናገር ጠላት ይሰማል” በማለት ምሥጢር ያሉትን መድኃኒት እንዲጠቀሙ … [Read more...] about ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ
ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው
ሕገወጡ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) ሰሞኑን “በትግራይ ዲፕሎማሲ እና አድቮኬሲ ካውንስል” ስም ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ ለአውሮፓ ኅብረት እና ለአፍሪካ ኅብረት የጻፈው ደብዳቤ የራሱን ሕገ-ወጥ ድርጊቶች ለመሸፈን እና ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ለማታለል የሞከረበት የተለመደ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ነው። የደብዳቤውን ይዘት እና ወቅታዊ እውነታዎችን መሠረት በማድረግ እውነታውን በሚከተለው መልኩ እናቀርባለን፦ 1. የፕሪቶሪያን ስምምነት ስለማፍረስ እና ስለመሻር ደብዳቤው የኢትዮጵያ መንግሥት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ጥሷል ሲል ይከሳል። ነገር ግን እውነታው ፍጹም ተቃራኒ ነው። ትህነግ የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመሰረዝ በትግራይ ክልል የነበረውን ጊዜያዊ አስተዳደር በኃይል እና በሕገ-ወጥ መንገድ አስወግዷል። ትህነግ በራሱ ፍላጎት የሰላም … [Read more...] about ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው
በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ
ትብብር ለአንድነት ኢትዮጵያን በመወከል በየካ ክፍለ ከተማ ምርጫ የተወዳደሩት አቶ ጌትነት ወርቁ በአርሲ የተከሰተውን አስመልክቶ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ግልፅ ደብዳቤ በፌስቡክ ገጻቸው ከሦስት ቀን በፊት አጋርተው ነበር። አቶ ጌትነት ወርቁ እና መሰል የትብብር ፓርቲ አባላት ለምርጫ ለመወዳደር የገቡት በዓላማ እንደሆነ በተደጋጋሚ ሲነገር የቆየ ሲሆን ምርጫው ከተጠናቀቀ በኋላ የተለያዩ ምሥጢሮቻቸው ይፋ እየሆኑ መጥተዋል። በተለይ በምርጫው ክርክር ወቅት ከራሱ የትብብር ሰዎች፤ አቶ ጌትነትንም ጨምሮ፤ በምርጫው የሚወዳደሩት መንግሥት ለመመሥረት እንዳልሆነ ሲናገሩ መሰንበታቸው የሚረሳ አይደለም። እንዲያውም የፈለገውን ያህል ወንበር ብናገኝ መንግሥት ለመመሥረት አንችልም ብለው በሚዲያ መናገራቸው ትብብር ለምን ይሆን ወደ ምርጫ የገባው የሚል ጥያቄ ሲያስነሳ የቆየ ጉዳይ … [Read more...] about በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ
የጽምዶ ልክፍት
ትሕነግ (የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር - ህወሃት) ከ2010 ዓም ለውጥ በኋላ ሦስት መጠነ ሰፊ የተባሉ ወረራዎችን እንደፈጸም ይታወሳል። በእነዚህ ተዋጊዎችን እንደ ማዕበል (human wave) የማሰለፍ ስልት ከራሳቸው አንደበትና የጽሑፍ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት አንድ ሚሊዮን የሚደርሱ የትግራይ ተወላጆች ህይወት አልፏል። የፕሪቶሪያውን የሰላም አማራጭ ስምምነት ተከትሎ በትግራይ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች እና የሽግግር ወቅት ጊዜያዊ አስተዳደሩ በጦርነቱ ወቅት ተሳታፊ ለመሆን ዕድል የተመቻቸለት ሻዕቢያ በትግራይ እህቶች፣ እናቶችና ተወላጆች ላይ የፈጸመው ግፍም የሚዘነጋ አይደለም። ትሕነግ ለውጡን ተከትሎ ወደ ትግራይ ካፈገፈገ በኋላ “የፌዴራሊስት ኃይሎች” ብሎ የፈረሰውን ኢህአዴግ የሚተካ ሌላ አደረጃጀት ፈጥሮ ወደ አራት ኪሎ ለመመለስ የሚያግደው ምንም ኃይል እንደሌለ “ጦርነት … [Read more...] about የጽምዶ ልክፍት
ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው?
ራሱን የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) በማለት የሚጠራው ሕገወጥ የወንበዴዎች ቡድን ተክሎብን እና ጥሎብን የኼደው መርዝ እስካኹን አልፋታ ብሎን የመከራ ዘመናችንን አርዝሞታል። ሀገርን በዘር ከፋፍሎ፤ ሕዝብን እንደ ከብት በክልል ወስኖ፤ ኢትዮጵያዊነትን በሰፈርና በወንዝ ወስኖ፤ ለዘመናት አብሮ የኖረን ሕዝብ በጠላትነት እንዲተያይ አድርጓል። እንዳሰበው ባይሳካለትም ሀገራችን ከመፍረስ ድና አኹን ያለችበት ቁመና ላይ ትገኛለች። ትህነግ ግን ነጻ አወጣዋለኹ ብሎ ሲነግድበት የነበረውን ሕዝብ የምድር ሲዖል ውስጥ ጨምሮ እያሰቃየው ይገኛል። ወደ ጉዳያችን ስንመለስ፤ ትህነግ መርዙን ተፍቶብን ወደ ትግራይ ኼዶ ቢመሽግም አሁንም ግን ግድያ፣ ደም ማፍሰስ፣ ማፈናቀል፣ አልቆመም። በሀገሪቱ ላይ የሚፈጽመው ዕልቂት የገፊና ጎታች ሤራ እንደሆነ በተደጋጋሚ ያነሳነው ጉዳይ ነው። ጎልጉል በዚህ … [Read more...] about ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው?
ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም!
በኦነግ ሸኔ ዐማጽያን በንጹሐን ዜጎች ላይ በተለይም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ዒላማ ተደርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ተከትሎ፤ የቤተሰብ እና የወዳጆቻቸውን ሕይወት ላጡ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እና የቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው በአርሲ ዞን ለሚገኙ ወገኖቻችን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻሉ። እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ሲሆኑ፤ ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው። መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር ፍትሐዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከአንድ … [Read more...] about ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም!










