* "እኛ የገባነው ልናፈርሰው ነው" ሕዝቅኤል ገቢሣ በሰላማዊ ትግል መንግሥት ለመጣል ማቀዱን አስታውቆ ሃያ አንድ ቦርድ አባላትን ሰይሞ የሰነበተው የ-አብሮነት ማኅበር ሰባት ሥራ አስፈጻሚዎችን መምረጡ ታወቀ። ማኅበሩ “ለቦርድ አባላት” በሚል ባሰራጨው የ“እንኳን ደስ አላችሁ” መልዕክት አቶ ልደቱ፣ ከአማራ የማኅበሩ ፕሬዚዳንትና ሊቀመንበር ሆነዋል። መቅደስ አዳነ ከወላይታ (ምክትል)፣ አሸናፊ አብርሃም ከደቡብ (ጸሐፊ)፣ ሙሉጌታ ዘለቀ ከአማራ (ገንዘብ ያዥ)፣ የሕዝብ ግንኙነት ኦፊሰር ሕዝቅኤል ገቢሣ /በተለይ እንግሊዘኛና ትግርኛ ጠንቀቀው ስለሚያውቁ/ ከኦሮሞ፣ የድርጅት አስተባባሪ እስማኤል ጎርሴ ከሶማሌ፣ የውጭ ግንኙነት ኦፊሰር መስፍን አየነው ከትግራይ መመረጣቸው ይፋ አድርጓል። ቀደም ሲል ምርጫው ከመደረጉ በፊት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አባላቶች ሕቡዕ እንደሚሆኑ … [Read more...] about የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ
Politics
“የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል
ሼትል ትሮንቮል “መንግሥቱ ኃይለማሪያም ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በስደት ክሚኖሩበት ሀራሬ ደወሉለት፣ ሰላም ጓድ አንተም እንደ እኔ በወያኔ ተቸግረሃል፣ እባክህን እኔ እንዳደረኩት ወደ ሃራሬ እንዳትሰደድ ምክንያቱም ወያኔዎቹ አንተን ፍለጋ ሃራሬ ሲመጡ እኔንም ይውስዱኛል” በማለት ዝነኛ ጆክ ትዊት አድረገው የነበሩ ሰው ናቸው። አዲስ ሪፖርተር – የኖርዌይ ፕሮፌሰር ሼትል ትሮንቮል “ነጩ ወያኔ” በሚል ስያሜ ይጠራሉ። የትህነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ያህል በትህነግ ጉዳይ ወሳኝ ሰው ነበሩ። ዛሬም ድረስ አፍቃሪ ትህነግነታቸው ባይቀየርም የመከፋፈሉ ወጀብ እርሳቸውንም የናጣቸው ይመስላል። በትግራይ የተካሄደውን ምርጫ መቀሌ ተገኝተው “ሕጋዊ ነው” በማለት ያጸደቁና የተሟገቱ ናቸው። በተለይም በኅልውናው ጦርነት ወቅት ለትግራይ ታጣቂ ኃይሎች TDF የሚል የወል ስም ማውጣታቸውን … [Read more...] about “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል
በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ
* “ዳህላክ ነው ቤቴ”፤ “ደሞ በዓባይ (ድርድር) ከሞከሩንማ” ኢትዮጵያ ላይ ተረባርበው የነበሩ፣ ኢትዮጵያ ላይ ፍትሕ በማዛባት ዘምተው የነበሩ፣ ኢትዮጵያን ማሳጣት የዕለት ተዕለት ተግባራቸው የሆነ ወዘተ ሚዲያ አውታሮች “ኢትዮጵያ ኑክሊየር ታጠቀች” በማለት ለታላቁ የዓባይ ግድብ አድናቆታቸውን ቸረዋል። በጨለማ ውስጥ ለሚኖሩ ብርሃን ያዩ ዘንድ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ በራሷ ልጆችና ኪስ ይህን “ክስተት" የተባለ ፕሮጀክት ስታስመርቅ የተሰማው ታሪክ በዜጎች ዘንድ ሁሉ ከዳር እስከዳር ልዩ ስሜትን ዘርቷል። አስራ አምስት ሺህ ዜጎች የጠላት ተልዕኮ በተቀበሉ ቅጥረኞች ወጥመድ ማለቃቸው ግድቡ በኢትዮጵያዊያን፣ ጉልበት፣ ገንዘብና ዕውቀት ብቻ ሳይሆን አጥንትና ደም ጭምር የተገነባ፣ የታተመ የኢትዮጵያዊያን ሁሉ ማኅተባቸው እንደሆነ እዚያው ሥፍራው ላይ ሆነው ሁሉንም ያዩና የታዘቡ … [Read more...] about በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ
መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ
* “ዓለም እያዘነብን እየሳቀብን ነው አንድ እንሁን” - ዘመነ ካሤ አርበኛ ዘመነ ካሴ “ዓለም እያዘነብንም እየሳቀብንም ነው” በማለት “መተው ነገሬን ከተተው" እንደሚባለው በመተው "አንድ እንሁን" የሚል ጥሪ አሰማ። ፋኖ ኢትዮጵያን ሠርቶ ምስራቅ አፍሪካን ያረጋጋል ብሏል፤ አንድነት ለመፍጠር “አንድ ማንኪያ ቅንነት” ነው የሚያስፈልገው አለ። በጎጃም እና በደቡብ ጎንደር የተሰማራው የአገር መከላከያ በበኩሉ ስም፣ ቦታና ኃላፊነት ጠቅሶ በፋኖ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን አስታውቋል። የዘመነ መልዕክት የተሰራጨው የመከላከያ መረጃዎች እኩል ቀን ነሐሴ 16 በሪፖርት መልክ ይፋ ከሆነ በኋላ ነው። "የዕለቱ መልዕክት" በሚል የአማራ ፋኖ በጎጃም መሪ ዘመነ ካሴ "በቃ መተው እንልመድ" ሲል የተለያዩትን የፋኖ አመራሮችና አደረጃጀቶች ዘርዝሮ " ... አንድ መሆን አለበት" … [Read more...] about መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ
ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ
ሰሞኑን ሞዐ ተዋሕዶ አየሩን ሞልቶታል። በተለይ በቅርቡ ከሞዐ ተዋሕዶ አመራሮች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ፋንታኹን ዋቄ የሰጡት ቃለ ምልልስ ወደኋላ ሄደን ብዙ ነገሮችን እንድንዳስስ የሚያስደርግ ሆኗል። የዛሬ ሦስት ዓመት በቀነኒሳ ሆቴል ዶ/ር ወንደሰን በሚመራው ስብሰባ መግለጫ በሰጡበት ወቅት የተናገሩትና ሰሞኑን የተሰማውን ጉዳይ ባጭሩ ለማስቀመጥ እንሞክራለን። ይህንን በማድረግም የሞዐ ተዋሕዶን ሁኔታ ለየት ባለ ሁኔታ ለማየት እንሞክራለን፤ እንደተባለው ሞዐ ሃሳብ የሚያመጣና ወደ ሕዝቡ የሚያሰርጽ ንቅናቄ ነው? ወይስ ሌላ ተልዕኮ አለው? የሚለውን በንጽጽር እናያለን። የዛሬ ሦስት ዓመት አካባቢ በቀነኒሳ ሆቴል ከተካሄደው የሞዐ ተዋሕዶ ስብሰባ በኋላ የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ ከሶስት የሞዐ ተዋሕዶ አመራሮች ጋር ውይይት አድርጎ ነበር። በውይይቱ የተገኙት መምህር ገብረመድኅን እንየው፣ … [Read more...] about ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ
የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?
የሃይማኖትና የመንግሥትን መጣመር የሚደግፉም ሆነ ጥምረታቸውን በጽኑ የሚቃወሙ ጠንካራ የመከራከሪያ ነጥቦችን ያነሳሉ። ይህ ዘመናትን ያስቆጠረ ክርክር ባለንበትም ዘመን ሠለጠነ ከሚባለው ዓለም እስከ አገራችን የመወያያና የመከራከሪያ አጀንዳ ሆኖ ቆይቷል። ይህ አጭር ጽሑፍ በሁለቱ ጽንፎች መካከል የሚካሄደውን ክርክር ለማቅረብ ወይም ለአንዱ ለመወገን ያሰበ ሳይሆን የሁለቱ ጥምረት ምን ውጤት አመጣ? ታሪክስ ምን ያስተምረናል? የሚለውን በጣም በጥቂቱ ለማንሳት ነው። ለማሳያነትም የክርስትና እምነትና መጽሐፍ ቅዱስ የምንጠቀም ሲሆን ይህ ማለት ግን ስለ ሌሎች ሃይማኖቶች ታሪክ ምንም አይልም በሚል እንዳይወሰድ አደራ ለማለት እንወዳለን። የሦስቱ ታላላቅ ሃይማኖቶች አባት የሚባለው አብርሃም ይኖርበት ከነበረው ባቢሎን (የከለዳውያን ዑር) ወይም ያሁኗ ኢራቅ አካባቢ እግዚአብሔር … [Read more...] about የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?
“በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ
ሃራ ወይም ነጻ ተብሎ በሚጠራው መሬት ላይ ሠፍሮ የሚገኘው "የትግራይ የሰላም ኃይሎች" (TPF) ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ኃይል በያዝነው ዓመት መጨረሻ ሙሉ ትግራይን እንደሚቆጣጠር አስታወቀ። "ጸጥተኛ" ብለው ለሚጠሩት አቢዮት ሠራዊቱ እየተዘጋጀ እንደሆነም ተነግሯል። ይህ የተገለጸው በፈረንሳይኛ ቋንቋ በድረገጽ የሚታተመውና አፍሪክ XXI (Afrique XXI) የተባለው ጋዜጣ ከጥቂት ቀናት በፊት በትግራይ ላይ በሠራው ዘገባ ነው። ዘገባው በሃራ ምድር የሰፈሩትን የትግራይ የሰላም ኃይል/ቲፒኤፍ ተብለው ከሚጠሩት ታጣቂዎች ጋር ቃለ ምልልስ ካደረገ በኋላ ነው። የሰላም ኃይሉ አባላት በአብዛኛው ከዚህ በፊት በትህነግ ሥር ከነበረው የትግራይ መከላከያ ኃይል ወይም ቲዲኤፍ (TDF) ከሚባለው ከድተው የወጡ ናቸው። በተለይ ካለፈው መጋቢት ወር ጀምሮ በብዛት ከቲዲኤፍ እየኮበለሉ ወደ አፋር … [Read more...] about “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ
የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ
በቅርቡ “ሰማይ አንቀጥቅጥ” በሚል ስያሜ ተካሂዶ በቅብብሎሽ “የሻዕቢያ ተቀጣሪዎች” እና አፍቃሪ የትህነግ ሚዲያዎች ያራገቡት የበይነ መረብ ትዕይንት በዋናት የሻዕቢያና የበረከት ስምዖን ሤራ እንደሆነ ተሳታፊዎች አመልከቱ። ርዕዮት ዩቱብ ልዩ ገጸ ባህርይ ተዘጋጅቶለት ድራማውን ከልደቱ ጋር እንዲተውን የተደረገው ሆን ተብሎ እንደሆነም ተጠቁሟል። በአደባባይ ትህነግና ሻዕቢያን ለጆሮ በሚከብድ ቃላት የሚሳደበው የርዕዮት ዩቱብ ባለቤት ቴዎድሮስ ጸጋዬ ይህንን ገጸ ባህርይ እንዲጫወት የተደረገው ሆን ተብሎ ነው። የዜናው ባለቤቶች እንደሚሉት ቴዎድሮስ ከማንነቱ የተነሳ ለድራማው ተመራጭ አድርጎታል። ይህ ተፈጥሮው ታማኝ ስለሚያስመስለው ድራማውን በደንብ እየተጫወተ መሆኑም ተመልክቷል። የቴዎድሮስ ገጸ ባህሪ ልክ ልደቱ በ1997 ሕዝብ ጉድ እስኪል ኢህአዴግን እየተሳደበ በመጨረሻ ይፋ ከሆነው … [Read more...] about የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ
“ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ)
ልደቱ አያሌው ከቴዎድሮስ ጸጋዬ ጋር ያስተባበረው “አየር አንቀጥቅጥ” ትዕይንት ቅዳሜ ቀን ተካሂዷል። ልደቱ በስተመጨረሻ እንዳለው ከታሰበው በላይ የተሳካው የአየር ትዕይንት 15 ሰዎች ተናግረዋል፤ ሕዝብ በሳተላይት እና በተገኘው መንገድ ሁሉ ሰምቷል ብሏል። አገዛዙ ፈርቶ ኢንተርኔት አፍኗል፤ ዳታ ታቅቧል፤ ዩትዩብ እንዳይሠራ ተደርጓል ብለው ልደቱም፣ ቴዎድሮስም እየደጋገሙ ሲናገሩ ተሰምተዋል። ይህ የአየር ላይ ትዕይንት “ስልቴዎች” ማለትም ስብሃት፣ ልደቱ፣ ቴዎድሮስ በልዩ ሁኔታ የቀመሩትና ትህነግን በመታደግ ለሻዕቢያ የተሠራ ልዩ የስልቴዎች ስልት ነው። ንግግር ያደረጉት ሰዎች ጥቂቶቹን ስንቃኝ፤ … የድግሱ መሪ ቴዎድሮስ መደረጉ በራሱ ብዙ የሚለው ነገር አለ። ቴዎድሮስ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ወገኖቼን (የትግራይ ተወላጆችን በተለይም ወያኔዎችን) የፈጀች ኢትዮጵያ ጥንቅር … [Read more...] about “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ)
ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …?
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ “አሉኝ” የሚላቸውን መረጃዎች የሚያሰራጭበት ሚዲያ በመኖርና በመጥፋት መካከል እንደሆነ ጠቅሶ የተለያዩ አማራጮችን ሲያቀርብ የነበረው ኤሊያስ መሠረት በተቃውሞ ሽፋን ለብልጽግና እየሠራ እንደሆነ መቅመጫቸውን ኬኒያ ያደረጉ ክፍሎች ገልጸዋል። በአገር ቤት ያሉና ይህንኑ ዜና የሚደግፉ ተጨማሪ ማስረጃዎችን በመገጣጠም ዜናውን አጉልተዋል። ኤሊያስ መሠረት በተቃውሞ ሽፋን ለብልጽግና እንደሚሠራ መረጃ የሰጡት ክፍሎች ኤሊያስ መሠረት ናይሮቢ በከተመበት ወቅት በቅርበት የሚያውቁት ናቸው። ትህነግ በሥልጣን በነበረበት ዘመን በሥልት ዜናዎችን ሲያቀዛቅዝና ሲያድበሰብስ ጠንቀቀው የሚያውቁት ወዳጆቹ እንደሚሉት፣ ኤሊያስ መሠረት ወደ ብልጽግና የመሸጋገር ዝንባሌ የታየበት “ትህነግ ዳግም ይመለሳል” የሚለው ምኞቱ ሙሉ በሙሉ መክሰሙን ከተረዳ በኋላ ነው። ለትህነግ … [Read more...] about ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …?










