ትብብር ለአንድነት ኢትዮጵያን በመወከል በየካ ክፍለ ከተማ ምርጫ የተወዳደሩት አቶ ጌትነት ወርቁ በአርሲ የተከሰተውን አስመልክቶ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ግልፅ ደብዳቤ በፌስቡክ ገጻቸው ከሦስት ቀን በፊት አጋርተው ነበር። አቶ ጌትነት ወርቁ እና መሰል የትብብር ፓርቲ አባላት ለምርጫ ለመወዳደር የገቡት በዓላማ እንደሆነ በተደጋጋሚ ሲነገር የቆየ ሲሆን ምርጫው ከተጠናቀቀ በኋላ የተለያዩ ምሥጢሮቻቸው ይፋ እየሆኑ መጥተዋል። በተለይ በምርጫው ክርክር ወቅት ከራሱ የትብብር ሰዎች፤ አቶ ጌትነትንም ጨምሮ፤ በምርጫው የሚወዳደሩት መንግሥት ለመመሥረት እንዳልሆነ ሲናገሩ መሰንበታቸው የሚረሳ አይደለም። እንዲያውም የፈለገውን ያህል ወንበር ብናገኝ መንግሥት ለመመሥረት አንችልም ብለው በሚዲያ መናገራቸው ትብብር ለምን ይሆን ወደ ምርጫ የገባው የሚል ጥያቄ ሲያስነሳ የቆየ ጉዳይ … [Read more...] about በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ
Tibibir
የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ ተከትሎ “ትብብር” የተሰኘው ቡድን ያወጣው መግለጫ በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጠመው። የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ) እና የእናት ፓርቲ አመራሮች “ትብብር” የተባለውን ስብስብ ወክለው ኢኤምኤስ ለተባለው ዩትዩብ የተናገሩት በሀገር ውስጥና በዲያስፖራው ሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ አስነሳ። ሚስጥረሥላሴ ከኢህአፓና ጌትነት ከእናት ፓርቲ ሆነው “ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ ያልሆነ የጨረባ ምርጫ ነው” በማለት ውድቅ ለማድረግ ቢሞክሩም፣ ሕዝቡ ግን “ቀድሞውኑ ለገዢው ፓርቲ አጃቢና ድራማ አድማቂ ለመሆን የገባችሁ የፖለቲካ ድንኮችና ሆዳሞች ናችሁ” በማለት በብርቱ እያወገዛቸው ይገኛል። የፖለቲካ ተንታኞችና የውስጥ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት፣ የኢህአፓ እና የ“ትብብር” ጥምረት መሪዎች ቀድሞ የነደፉት … [Read more...] about የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ


