ስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከቀደምቶቹ አምስት ምርጫዎች ለየት ያለና ሕዝቡ በምርጫ ሒደት እምነት እንዲያገኝ የሚያስችለው እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ እንዲሁም መንግሥት በተደጋጋሚ ሲያስተጋቡ ቆይተዋል፡፡ ይኼ ምርጫ በመንግሥት ትኩረት እንደተሰጠው ከሚያሳዩ ጉዳዮች አንዱ የተመደበለት በጀት መጠን ሲሆን፣ በአገሪቱ የምርጫ ታሪክ ከፍተኛ የሆነው 2.5 ቢሊዮን ብር ለምርጫ ዝግጅት በፓርላማ ፀድቋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሳቢያ ምርጫው በአንድ ዓመት እንዲራዘም ከተደረገ በኋላ፣ ቦርዱ ለፓርላማ የ1.1 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ይኼ ከመንግሥት የቀረበለት በጀት ሲሆን፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (ዩኤንዲፒ) የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር የምርጫ ድጋፍ አማካይነት ደግሞ፣ በዓይነት የሚደረግ 1.8 ቢሊዮን ብር ገደማ … [Read more...] about “ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ
Election Board
ምርጫ ቦርድ የኦነግን ጥያቄ ውድቅ አደረገ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራሮች መካከል በተፈጠረ መከፋፈልና ውዝግብን የተመለከቱ እግዶች፣ አቤቱታዎችና ከሁለቱም ወገን የሚመጡ ማሳወቂያ ደብዳቤዎችን ሲቀበል መቆየቱ እንዲሁም ችግሩን ለመፍታት ቡድኖቹን በተናጠል እንዲሁም የፓርቲውን የስነስርአትና የቁጥጥር ኮሚቴን በማነጋገር ያሉትን አስተዳደራዊና ህጋዊ መንገዶች ሁሉ እንደተጠቀመና መፍትሄዎችን ለመስጠት ጥረት ሲያደርግ እንደነበር አስታውሶ፣ በመጨረሻም ጠቅላላ ጉባኤ በመጥራት ፓርቲው ካለበት ችግር ብቸኛ መውጫ መንገድ መሆኑን በመረዳትና በውዝግብ ውስጥ ያሉ አመራር ክፍሎችም ያመኑበት በመሆኑ፣ በአመራሮች መካከል ያለው ችግር በጠቅላላ ጉባኤ እንዲፈታ መወሰኑ ይታወሳል። ኦነግ መጋቢት 7 ቀን 2013 ዓ.ም በቁጥር 19/ABO/2013 በተጻፈ ደብዳቤ ድርጅቱ መጋቢት 4 ቀን 2013 ዓ.ም ጠቅላላ … [Read more...] about ምርጫ ቦርድ የኦነግን ጥያቄ ውድቅ አደረገ
ጃዋር ቀነ ገደብ ያስቀመጠውን የምርጫ ቦርድ ደብዳቤ ፈርሞ ተቀበለ
ለቀረበለት ሕጋዊ ደብዳቤ ዛቻን አስቀድሟል ከለውጡ በኋላ ወደ ፖለቲካ ሥልጣን የመጠጋጋት ህልምና ውጥን እንደሌለው ሲወተውት የነበረው ጃዋር በቅርቡ ኦፌኮን መቀላቀሉን ተከትሎ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ደብዳቤ ሊልክለት በዝግጅት ላይ መሆኑ ትላንት በመረጃ ገልጸን ነበር። ዛሬ (ማክሰኞ) የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ እንዳመለከተው ጃዋር የወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ፊርማ ያረፈበት ደብዳቤ እጁ ገብቷል፤ ፈርሞ ተቀብሏል። ደብዳቤው እንዳይዘጋጅ ያደረገው ሩጫ ሳይሳካ በመቅረቱ ዛቻ እየሰነዘረ መሆኑም ታውቋል። በተደጋጋሚ የሕግ የበላይነትን በማንሳት ዲስኩርና ማብራሪያ የሚሰጠው ጃዋር፣ ምርጫ ቦርድ በጻፈለት ደብዳቤ መቆጣቱና ወይዘሪት ብርቱካን ላነሱት የሕግ ጥያቄ መልስ ከመመለስ ይልቅ ዛቻን መመረጡን የጎልጉል መረጃ አቀባዮች ይፋ አድርገዋል። በሚያስተዳድራቸው ሠራተኞቹና አበል … [Read more...] about ጃዋር ቀነ ገደብ ያስቀመጠውን የምርጫ ቦርድ ደብዳቤ ፈርሞ ተቀበለ