• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች

March 18, 2026 10:48 am by Editor 1 Comment

የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢ ስለሆኑት የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶችና የንግድ ተቋማት ሲነሳ ግንኙነታቸው “በሬ ካራጁ” እንደሚሉት ዓይነት መሆኑን መጠቆም ጉዳዩን ምን አልባትም ማሳነስ ካልሆነ በቀር አይበዛም። ምክንያቱም አውሬው ኦሮሚያ ላይ በተቀመጡ የትህነግ ቅምጦች አማካይነት መረጃ እየተቅበለ በተሰጠው የቤት ሥራ መሠረት ኃላፊዎችን እያንገዋለለ ያስጠበጥብ ስለነበር ነው።

በዘመነ ት ህነግ ሪፖርተር ኦሮሚያ ላይ የሠራው ሤራና አሻጥር በዚህ አጭር ጽሑፍ የሚገለጽ አይደለም። ትህነግ ኦሮሚያን የተቆጣጠረው በሪፖርተር አማካኝነት ነበር ቢባል ምንም ማጋነን አይሆንም። በኦሮሚያ ላይ የሚከናወኑ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ፣ የኢኮኖሚ ጉዳዮች መረጃ ይጠባ የነበረው ሪፖርተር ነበር።

ለምሳሌ፤ ኢህአዴግ ሥልጣን ላይ በነበረ ጊዜ፤ በተዋረድ የተቀመጡ የትህነግ ካድሬዎችና ሰላዮች ጥይት በማቀበል ተረኛውን ያስወቅጡታል። ሪፖርተርም ምን ገዶት ተጠንቶ በተዘጋጁ ዓምዶቹ እየበላለተ መረጃዎቹን ይረጫል። ለነገሩ ለዛሬ ኦሮሚያን ተነሳ እንጂ አሠራሩ ሁሉም ጋር ነበር ይቻላል።

ነገሩን በሌላ መልኩ እናስረዳ፤ ለምሳሌ ከኦሮሚያ አንድ ባለሥልጣን ለማስነሳት ወይም በዘመኑ አባባል ገምግሞ ለመገፍተር ሲፈለግ መረጃ ለሪፖርተር ይሰጣል። ሪፖርተር ባለሥልጣኑን አብጠልጥሎ የተሰጠውን መረጃ ያትማል። የሚቀጥለው የሪፖርተር ዕትም ከመውጣቱ በፊት ግለሰቡ ከሥልጣን ይነሳል፤ ወይም ካገር ይወጣል ወይም የደረሰበት ይጠፋል።

ምሳሌውን በማስረጃ እናብራራው፤ አሊ አብዶ የአዲስ አበባ ከንቲባ/አስተዳዳሪ ይባል እንጂ መሪው፣ አድራጊና ፈጣሪው ደብረጽዮን ገብረሚካኤል እንደሆነ ተገልጾ ባንድ ወቅት መረጃ መሰራጨት ሲጀመር፣ ሪፖርተር የአዲስ አበባ አስተዳደር መበስበስን የሚያሳይ መረጃ በጆንያ ተላከለት። ወዲያው አሊ አብዶ በሪፖርተር አዲስ አበባን የገደለ ባለሙሉ ሥልጣን አስተዳዳሪ ተደርጎ በተከታታይ ተቀጠቀጠ። በመጨረሻም የት ህነግ ስውሩ ከንቲባ ስሙ እንዳይነሳ አሊ አብዶ ፊት ለፊት ተደርጎ ከረከሰ በኋላ ፓርላማ ቀርቦ “እኔ አዲስ አበባን ገድያለሁ፣ እኔ ዓቅም የለኝም” ወዘተ በማለት ራሱን በመርገም የደብረጽዮንን መልክ አጸዳ።

እዚህ ላይ አሊ አብዶ የተሳካለት፣ ጎበዝ፣ ብቁና ለአዲስ አበባ ወርድና ስፋት የሚመጥን መሪ ነበር ለማለት ሳይሆን ሪፖርተር የመብያው ጥርስ መሆኑን ለማሳየት ነው፤ በተለይ ኦሮሚያ ላይ። አሊ አብዶ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ኦሮሚያ የቢሮ ኃላፊ ከሆነ በኋላ ይህንኑ ምሥጢርና ደባ ግልጽ ወጥቶ ባይሆንም መስክሯል። ለመቀርጠፍ ብቻም ሳይሆን ለሚፈልጉት አካል፣ የፖለቲካም ሆነ የኢኮኖሚ ጥቅም (የኢኮኖሚ ጥቅም ጉዳይን ወደፊት የምንመለስበት ይሆናል) አስፈላጊ ሲሆን የገጽታ ግንባታ ላይ ሪፖርተር ፊት ተሰላፊ እንደሆነ አስታውሶ ማለፉ አይከፋም።

ወደ አሁኑ እንምጣ፤ አሁን ላይ ሪፖርተር ኦሮሚያ ላይ ብዙም ተጽዕኖ የለውም፤ ትህነግ ኦህዴድን ሲያነግሥ እንደነበረው ኦሮሚያ ብልጽግና ውስጥ እጁ ስለሌለ፣ ቢሞክርም ማንነቱን ስለሚረዱት አማረ አረጋዊ ስትራቴጂውን በመቀየር ጨዋ ጨዋ የሚጫወት እየመስለ፣ እንደ ድመት እየታከከ ቀን ቆጣሪ ተስፈኛ ሆኗል። ስለሸለሙት የዘነጉት መስሎት እንደቀድሞ ፕሬስን ሰቅሎ መቦለት ይዳዳዋል። በግል ቢሮው ግለ ታሪኩ በሠራተኞቹ መሳለቂያ፣ ማፈሪያ የሆነው አማረ፣ ስልቱን ከኦህዴድ ወደ ኦነግና ሸኔ ቀይሮ “ሸኔ አዲስ አበባ ዙሪያ ነው፤ ከዱከም ጀምሮ ኢንቨስተር ለቆ እየወጣ ነው” በማለት ያረጠ ፖለቲካ ለመጫወት ይሞክራል። የአውሬው ሪፖርተር አማረ፤ ኦሮሚያን መበጥበጥ ላይ የተቸከለውን ወያኔያዊ ዓላማውን ለማሳካት አሁንም እንደሚንከላወስ መረጃ ጠቅሶ ማሳየት ይቻላል።

ትህነግ ለውጡን አሻፈረኝ ብሎ ወደ መቀሌ ሲሸሽ አዲስ አበባ የተቀመጠው የትህነግ አውራ፣ ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲመሠረት መታሰቡ በተነገረ ማግስት፣ ዛሬ ከሻዕቢያ ጋር ሽርክና የፈጠሩትን እንደ ደብረጽዮንን ከነሙሉ ካቢኔው በመዘርዘር “የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር” ብሎ አስተዋውቆን እንደነበር የሚታወስ ነው። ከላይ እንደተባለው ብልጽግና ውስጥ ይህን መረጃ የሚሰጠው የለምና ፍላጎቱን በ”ታማኝ ምንጮች” አስደግፎ ሰበር አለ።

ከዚያም በኋላ ምኑንም ምኑንም እያተመ፣ (ዝርዝር ማቅረብ ይቻላል) ዛሬ ላይ ደረሰ። ደብረጽዮንም ወደፊት መጣ፤ ሸኔ የተባለ በትህነግ የሚዘወር ደም አፍሳሽ የወንበዴ ቡድን በተለያዩ ቦታዎች ግድያ ሲፈጽም፣ ሀገር ሲበጠብጥ ሪፖርተር ለሕዝብ ያዘነ ዘጋቢ ሚዲያ መስሎ መረጃዎችን ያወጣል። ዓላማው በገፊና ጎታች ስልት በቅብ ብል ሕዝብን ሆድ ማስባስ ነውና እንዲህ ያለው ዜና አይታለፍም ነበር። ዓላማውን ለማሳየት እንጂ ዜናው እንደዜና ሽፋን አያስፈልግም ለማለት አይደለም።

ጥያቄው የሚነሳው፣ እልቂቱን፣ መፈናቀሉን የሚዘግበው የአማረ ሪፖርተር፣ ይህን ተግባር የሚፈጽመውን ሸኔን አለመንካቱ ነው። ተበዳዮች፣ ሞትን ያመለጡ ዜጎች በገሃድ “ሸኔ ገደለን” እያሉ እየተናገሩ አማረ ሸኔን አይወቅስም። ይባስ ብሎ ለውጪ ሚዲያና የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ግብዓት የሚሆን መረጃ በተለይ በእንግሊዝኛው እንደሚመች አድርጎ ሲያቀርብ ነው የኖረው።

ይህ ብቻ አይደለም፤ የሸኔ ታጣቂዎች ወደ ሰላም ሲመለሱ፤ እጅ ሰጥተው ብረት ሲያወርዱ፣ በሰፊ ቁጥር በሰልፍ እየተግተለተሉ “ለሰላም እጅ ሰጥተናል” ሲሉ ይህ ለሪፖርተር ዜና አይሆንም። ከዚህ በታች እንደ ማሳያ የተጠቀሱትን መመልከቱ የሪፖርተርን ማንነት በግልጽ የሚያሳይ ነው።

የሪፖርተርን አውሬነት ያልተደረዱ ወይም ባልሰማ፣ ባላየ ሆነው ከሪፖርተር ጋር የሚሠሩ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶችና የክልል ቢሮዎች ምን እያደረጉ እንደሆነ የተስተዋለ አይመስልም። በተለይ የንግድ ተቋማት ለሪፖርተር የሚሰጡት እጅግ ብዙ የማስታወቂያ ገንዘብ ብትችል ኦሮሚያን አፍርስልን ካልሆነ ግን በጥብጥልን ብለው የሚሰጡት መሆናቸውን አውቀውት ይሆን።

ከብዙዎቹ አንዱ የሆነውን ሲንቄ ባንክን እንውሰድ፤ ባንኩ የሪፖርተር የፕላቲኒየም አጋር ነው፤ ከዚህ በፊት ደግሞ ሪፖርተር ላይ ማስታወቂያ ሲያወጣ የኖረ ነው፤ ድረገጹም ላይ የሚታተመው ጋዜጣ ላይ። እንዴት ነው ነገሩ የሲንቄ ባንክ ሰዎች የት ህነግ ወንበዴዎች እነ ደብረጽዮን እነ ፈትለወርቅ ናቸው፧ እንዴት ሆኖ ነው የኦሮሚያ የንግድ ድርጅቶች ንግዳቸውንና ሪፖርተር ላይ የሚያስተዋውቁት፧ በት ህነግ ዘመን ቢሆን ኖሮ ተገድ ደው ነው እንል ነበር።

ከላይ እንዳልነው አውሬው ሪፖርተር ኦሮሚያን በመዳፉ ላይ አድርጎ የትህነግን ዓላማ ሲያስፈጽም የኖረ ነበር። አሁን ስሉሱ ዞሮ ባዶ የቀረ ቢመስልም የወሬ ቋቱ ነው እንጂ የብር ቋቱ በነሲንቄ ባንክና በመሳሰሉት ጢቅ ብሎ እየሞላለት ነው።

አውሬ ምን ቢሆን ለማዳ እንስሳ አይሆንም፤ ዛሬ አንገቱን የደፋ ቢመስልም የሞላለት ዕለት መፍጨትና ማድቀቅ ይጀምራል፤ እስካሁንም ምን ያህል እንደገፋበት፤ ምን ያህሉ እንደተሳካለት፤ ምን ያህሉ እንደከሰረ የሚታወቅ ነው። አሳሳቢው ዝምታ ግን የኦሮሚያ የንግድ ድርጅቶች ያለማቋረጥ አውሬውን መመገብ መቀጠላቸው ነው። የሚመግቡት ሲያጡ ራሳቸው ምግብ ይሆኑታል። ክፋቱ ግን ዳፋው ለኦሮሚያ መትረፉ ነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: Feeding the Beast, Feeding the Fox, operation dismantle tplf, Oromia Business entities, Reporter, Siinqee bank

Reader Interactions

Comments

  1. Guta says

    March 18, 2026 02:45 pm at 2:45 pm

    Yes.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule