• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ

April 2, 2026 10:16 am by Editor Leave a Comment

የውጭ የደህንነት ተቋማት በአንድ ሀገር ውስጥ ወደፊት ስልጣን ወይም ተፅዕኖ ሊኖራቸው የሚችሉ ወጣቶችን ገና በለጋ እድሜያቸው የመመልመልና የራሳቸውን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ግብ በሚያሳካ መልኩ ኮትኩቶ የማሳደግ ስልትን በስፋት ይተገብራሉ። ይህ ተግባር በዘርፉ “የልሂቃን ቀረጻ” (Elite Capture or Cultivation) ተብሎ የሚጠራ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም የተመረጡ ወጣቶችን የዓለም እይታ (Worldview) ከሀገራዊ ጥቅም ይልቅ የውጭ ሃገር ፍላጎትና ጥቅምን በሚያሳካ መልኩ አድርጎ መቅረጽ ነው። እነዚህ ተቋማት የአንድን ወጣት የወደፊት የመሪነት ዝንባሌ ቀድመው በመረዳት፣ በትምህርት እና በተለያዩ ስልጠናዎች ስም ከሀገሩ በማውጣት የአስተሳሰብ አድማሱን በእነሱ የፍላጎት ልክ ይቀርፁታል።

ይህ “Formative age” ወይም የማንነት ቀረጻ ምቹ እድሜ የአንድ ሰው ስብዕና እና መሰረታዊ እምነት የሚገነባበት ወሳኝ ወቅት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ “ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፤ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም” እንደሚለው ሁሉ፣ በዚህ የእድሜ ክልል የሚሰጡ ስልጠናዎችና የሚፈጠሩ ግንኙነቶች ግለሰቡ ለቀሪው ዘመኑ የሚከተለውን የፖለቲካ መስመር ይወስኑታል። በመሆኑም፣ ምንም እንኳ ግለሰቡ “እኔ በራሴ ነፃ ፈቃድና እውቀት ነው የምንቀሳቀሰው” ብሎ ቢያስብም፣ የልቦና ውቅሩና የውሳኔ አሰጣጡ አስቀድሞ በሰለጠነበት “የአስተሳሰብ ማዕቀፍ” (Frame of Reference) የታጠረ እንዲሆን ይደረጋል። በዚህም ምክንያት፣ የውጭ ኃይሎች አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኙት ግለሰቡን እንደ ስትራቴጂያዊ መሳሪያ ይጠቀሙበታል።

የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ጉዞ የዚህ ውስብስብ ኦፕሬሽን ውጤት መሆኑን ለመረዳት የግድ የመረጃና ደህንነት ባለሙያ መሆን አይጠበቅብንም። እርሱ ራሱ “አልፀፀትም” በሚል ርዕስ ለንባብ ያበቃውን የትግል ህይወት ታሪክ መጽሐፍ በጥሞና ማንበብና “ለምን?” ብሎ መጠየቅ ብቻ በቂ ነው። ጀዋር በዚህ መጽሐፉ፣ በጉልምስናው ወራት ወደ ሲንጋፑር ተወስዶ በወጣት አመራር ስልጠና ስም የህዝባዊ እምቢተኝነት የፖለቲካ ስልቶችን ከሀ እስከ ፐ እንዳስተማሩት በግልጽ ይተርካል። ይህም ለጀዋር ለወደፊቱ የፖለቲካ ስራው የሚያስፈልገውን ቴክኒካዊ እውቀትና ክህሎት እንዲገበይ ያደረጉበት ነበር። ጋዜጣ ላይ የሚወጡ የፓለቲካ ቅስቀሳ ጽሁፎችን እንዴት እንደሚፃፉ፣ ሚድያ እንዴት እንደሚመራ፣ የሕዝባዊ እምቢተኝነት አመራር፣ ስትራቴጂና እቅድ ዝግጅት ስልጠና እንደታሰጠው ጀዋር ያለምንም ሃፍረት ሳይደብቅ በመፅሀፉ ላይ ይገልፃል።

በሲንጋፑር ቆይታው ወቅትም የባዕድነትና የብቸኝነት ስሜት እንዳይሰማው በሚል ሰበብ የስድሳዎቹን ትውልድ የፖለቲካ አመለካከትና ስልት ተሞክሮ እንዲቀስም ታቅዶ ከተዘጋጀ ግለሰብ ጋር እንዲገናኝ ተደርጓል። የቀድሞ የመኢሶን አባል ከነበረ ሰው ጋር የቅርብ ቤተሰባዊ ዝምድና እንዲፈጥር በማድረግ፣ ስለ “ያ ትውልድ” የአብዮት ትግልና የርዕዮተ-ዓለም ፍጭት እንዲጠመቅ ተደርጓል። ይህ ስልታዊ ግንኙነት ጀዋር ገና በወጣትነቱ የ60ዎቹን የፖለቲካ መንፈስ፣ ጥላቻና ግትርነት ላይ የተመሰረተ ስብዕና እንዲላበስ በማድረግ፣ ለወደፊት የፖለቲካ ጉዞው መሰረታዊ የሆነውንና ለመለወጥ አስቸጋሪ የሆነውን የልቦና ውቅር የገነባበት አጋጣሚ ሆኗል።

ይህ የልቦና ውቅር የመቅረጽ ስራ በአሜሪካ ቆይታውም በከፍተኛ ደረጃ ቀጥሏል። ጀዋር እዚያም በነበረው ቆይታ ከቀድሞ የኢሕአፓ አባላትና እንደ ያሬድ ጥበቡና ነአመን ዘለቀ ካሉ የግራ ዘመም ፖለቲካ አራማጆች ጋር እንዲቀራረብ ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረውለታል። ምንም እንኳን ጀዋር በዕድሜ የአዲሱ ትውልድ አባል ቢሆንም፣ በውስጡ የሰረጸው የፖለቲካ አስተሳሰብ ግን የዚያኛው ትውልድ ቅጂ ነው። ይህም የልቦና ውቅሩ ከአሁኑ ዘመን ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ይልቅ፣ ተሸንፎ በወደቀው የባለፈው ክፍለ ዘመን የርዕዮተ-ዓለም ትግልና የሴራ ፖለቲካ ላይ ብቻ ተቸንክሮ እንዲቀር አድርጎታል።

በዚህም ምክንያት፣ የጀዋር የፖለቲካ ትግል ከህዝባዊ እምቢተኝነትና ከአመፅ ውጪ ሌላ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ የሆነ አማራጭ መንገድን ለማሰብ ተቸግሮ ይታያል። አሁን ዓለም ያለችበትን ውስብስብ የጂኦ-ፖለቲካ ፉክክር፣ የኃያላን ሀገራትን ፍላጎትና ቀጣናዊ ስጋቶችን ተረድቶ የሀገሩን ህልውና ለማስቀጠል የሚያስችል የትግል ስልት መቀየር ሲገባው፣ እርሱ ግን በአሮጌው መንገድ ላይ ብቻ ተቸንክሮ ቀርቷል። ልዩነቶችን አጥብቦ፣ በአንድ ሀገር ልጅነት መንፈስ ተባብሮ ሀገራዊ ህልውናን ከማስጠበቅ ይልቅ፣ ሁልጊዜም የታሪካዊ ጠላቶቻችንን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ግብ የሚያሳካውን የግጭት አዙሪት ይመርጣል።

ይህ ዓይነቱ የግጭትና የህዝባዊ አመጽ ትግል ስልት፣ ኢትዮጵያ ከውስጥ በራሷ ዜጎች እንድትዳከም በማድረግ የብልፅግና እና የዲሞክራሲ ሀገረ መንግስት ግንባታዋን ለዘመናት ወደ ኋላ ሲጎትት የኖረ አጥፊ መንገድ ነው።

ጀዋር ልክ እንደ ጋሪ ፈረስ ግራና ቀኝ መመልከት እንደተሳነውና በአንድ አቅጣጫ ብቻ እንዲጓዝ እንደተገደደ መረዳት አይከብድም። የውጭ ኃይሎች ሆን ብለው የቀረጹትን የፖለቲካ የልቦና ውቅር ሀገራዊ ችግሮችን በሰከነ፣ በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት እንዳይችል ትልቅ እንቅፋት ሆኖበታል።

ጀዋር ይህ ማንነቱ፣ ሃገራችን ዛሬ ከምትፈልገው የትብብርና የሰጥቶ መቀበል ውይይትና ድርደር ፖለቲካ ይልቅ፣ በጠባብና በአንድ አቅጣጫ በሚነዳ የትግል ስልት ውስጥ ታስሮ እንዲቀር አድርጎታል። ጀዋር ለሀገር የሚያስብ ቢመስልም፣ በተግባር ግን እየተከተለ ያለው መንገድ የውጭ ኃይሎችን ስትራቴጂያዊ ፍላጎት የሚያገለግልና የሃገርን አንድነት የሚሸረሽር ነው። ይህን የሕሊና ትብታብ ተረድቶ ከባዕዳን የአስተሳሰብ እስር ቤት መውጣት ካልተቻለ፣ የፖለቲካ ትግሉ ምንጊዜም ለሃገር ግንባታ ሳይሆን ለሀገር መፍረስ መሳሪያ መሆኑ አይቀሬ ነው።

አለባቸው ጉብሳ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, jawar massacre, Jawar Mohammad, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule