በቀጣይ በጀት ዓመት ደግሞ 20 ቢሊዮን ብር ተመድቧል የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር (300 ሚሊዮን ዶላር) ድጋፍ ለማድረግ ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ከኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳንና የኤርትራ ዳይሬክተር ኦስማኔ ዶኔ ጋር ተፈራርመዋል። የድጋፍ ስምምነቱ በጦርነቱ በአማራ፣ አፋር፣ ትግራይ፣ ኦሮሚያና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በግጭት የተጎዱ አካባቢዎችና ማህበረሰብ ለመልሶ ግንባታና መልሶ ማቋቋም ስራዎችን በአስቸኳይ ለመደግፍ ያለመ ነው። ድጋፉ በተመረጡ የግጭት ተጎጂ ወረዳዎች የጤና፣ የትምህርትና የውሃ መሰረት ልማት መዘርጋት ብሎም ለፆታዊ ጥቃት የተጋለጡ ሴቶችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም ይውላል ተብሏል። የፌዴራል መንግስት … [Read more...] about በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ
በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ
የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የብሔራዊ መረጃ ደህንነት ባደረጉት ክትትል በአንድ የእንጨት ስራ ድርጅት ውስጥ ተደብቆ የተቀመጠ ከ3 ሺህ በላይ ጥይት ከእነ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ ሁለቱ ተቋማት በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 አዲሱ ገበያ ቀለበት መንገድ አካባቢ በሚገኝ አንድ የእንጨት ስራ ድርጅት ውስጥ ተደብቆ የተቀመጠ ጥይት ስለመኖሩ ከህዝብ የደረሳቸውን ጥቆማ መነሻ በማድረግ ሲከታተሉ ቆይተው፥ ግንቦት 8 ቀን 2014 ዓ.ም በህግ አግባብ በድርጅቱ ውስጥ ባደረጉት ብርበራ በ4 ማዳበሪያ ተጠቅልሎ በድብቅ የተቀመጠ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተይዟል፡፡ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 2 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገ እንደሚገኝም የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ ህብረተሰቡ ህገ … [Read more...] about በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ
በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ
አንድ የውጪ ሀገር ዜግነት ባለው ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተደረገ ብርበራ ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላር እና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ። ግለሰቡ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው 24 ኮንዶሚኒየም ጀርባ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ባለ 3 ወለል ፎቅ ተከራይቶ የሚኖር መሆኑን ገልጿል። ተጠርጣሪው ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የውጭ አገር ዜጎችን እየተቀበለ በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ የተለያዩ ህገ ወጥ ተግባራትን ሲፈጽም እንደነበር ከህብረተሰቡ ጥቆማ ማግኘቱንም ነው የገለጸው። ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነዉ መረጃ እንደሚያመለክተዉ ፤ጥቆማውን መነሻ በማድረግ የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ተቀናጅተው ባደረጉት ክትትል ግንቦት 4 ቀን 2014 ዓ.ም በግለሰቡ መኖሪያ ቤት በተደረገ ፍተሻ በመኝታ ክፍል ውስጥ የተገኘ 5 ሺህ … [Read more...] about በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ
አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል
50 ሚሊዮን ሕዝብ የሚኖርበት የአማራ ክልል ዓመታዊ በጀት ሰማኒያ ቢሊዮን ነው በትግራይ ክልል ለአምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተሰጠ መሆኑን የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ። እስካሁን ወደ ትግራይ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ይዘው ከሄዱ አንድ ሺህ 626 ከባድ ተሽከርካሪዎች የተመለሱት ተሽከርካሪዎች 596 ብቻ እንደሆኑ አመልክተዋል። ክልሉን የሚያስተዳድረው ትህነግ በበኩሉ የሚገባው እርዳታ ከሚፈለገው አንጻር በቂ እንዳልሆነ ገልጿል። ዕርዳታ ጭነው የሚገቡትን ከባድ ተሽከረካሪዎች ለምን እንደሚያግታቸው ምክንያት አላቀረበም። የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴን ጠቅሶ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቀው፤ ምግብ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑና መድኃኒት እንዲሁም የትራንስፖርትና የጥሬ … [Read more...] about አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል
እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ
በየጊዜው እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ሰለባ ላለመሆን ዜጎች ማንነታቸው ከማይታወቁ ግለሰቦች ጋር በበይነመረብ በሚደረጉት ግንኙነት ላይ ጥንቃቄ እንዲወስዱ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እና የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ጥምር ግብረ- ኃይል አሳሰበ። ግብረ-ኃይሉ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሚፈጸሙ የማጭበርበር ወንጀሎች በይዘትም ሆነ በአፈጻጸም ስልታቸው ውስብስብ እየሆኑ ከመምጣታቸው ባሻገር በርካታ ግለሰቦች የጉዳቱ ሰለባ እንዲሆኑ እያደረገ ነው። የማጭበርበር ወንጀሎቹ በዋናነት የሚፈጸሙት በውጭ ሀገር የሚኖሩ፣ በቱሪስት ቪዛ ወደ አገር ውስጥ በሚገቡ የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ባላቸው ግለሰቦች መሆኑንም በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡ ኢትዮጵያዊያን በስፋት የሚጠቀሟቸው ማህበራዊ … [Read more...] about እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ
የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ሠራዊት ኢታማጆር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርኃኑ ጁላ ከዑጋንዳ የመከላከያ ሚኒስትር ጋር በወቅታዊ የሁለቱ አገሮች ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይታቸው የሁለቱ አገሮች የመከላከያ ዘርፍ ስምምነት ያለበት ደረጃ የተዳሰሰ ሲሆን በቀጣይ ስምምነቱን ለማደስ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ ይህም ሥምምነቱን የማደስ ሥራ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር እንዲፈፀም መመሪያ ተሰጥተዋል ተብሏል፡፡ ሁለቱ ኃላፊዎች በዋናነት ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘገብ ስለነበረውና አሸባሪው የሕወሓት ቡድን የሥልጠናና ሌሎች ድጋፎችን በአሜሪካ፣በግብጽና በደቡብ ሱዳን በመታገዝ በዑጋንዳ አማካኝነት እገዛ እያገኘ ነው የሚለውን ወሬ የዑጋንዳ መከላከያ ሚኒስትር ፈፅሞ ከዕውነት የራቀ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ የመከላከያ ሚኒስትሩ ሀገራቸው ኢትዮጵያን የአፍሪካ እናት … [Read more...] about የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ
በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ
በማኅበራዊ ሚዲያ የትህነግን ጉይ እየተከታተለ መረጃ የሚያጋራው አስፋው አብርሃ በትግራይ ያለውን ሁኔታ አስመልክቶ ካጋራው መረጃ ጥቂቱ እንዲህ ይነበባል፤ በትግራይ ልጁን ለወያኔ ያልሰጠ ወላጅ እየታሰረ ነው። አሁን ይኼ ውጪ አገር የሚኖር ልጅ ነው። በአንድ ወቅት "ወያኔ ቅዱስ ነው " ብሎ FB ላይ ለጥፎ ነበር። አሁን “ወላጅ እናቴ ታስራለች። በሽተኞችን ሳይቀር እየተሸከሙ ያስሯቸዋል” ይላል የባይቶናው ክብሮም በርሄ። ("ልጆቻችሁን ደብቃችኋል ፤አምጡ" እየተባሉ ነው የሚታሰሩት..) የትግራይ ወጣቶች የሚመዘኑበት መስፈርት “ታግሏል ወይስ አልታገለም” የሚል ብቻ ሆኗል። ልጁን ለወያኔው ትግል አሳልፎ ያልሰጠ የትግራይ ወላጅ ደግሞ ለእስር የሚዳረግበት ትልቅ ወንጀል ሆኗል። ይሄ ፅሑፍ ገራሚ ነው። ፅሑፉ ልጃቸውን አምጡ ተብለው ስለታሰሩ አንድ አባት የሚያትት … [Read more...] about በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ
መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል
ከመካከለኛው ምስራቅ አካባቢ የሚሰሙ ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት ኢትዮጵያ ከትህነግ ጋር ወደ ዳግም ጦርነት ልትገባ እንደምትችል ጠቁመዋል። ትህግም ለውጊያ እየተዘጋጀሁ ነኝ ሲል ተሰምቷል። ኤርትራ ደግሞ በሩሲያ ሠራሽ ድሮኖች ራሷን አጠናክራለች። ከተለያዩ የዜና ምንጮች ለመገንዘብ እንደሚቻለው የኢትዮጵያ መካላከያ ሠራዊት አዲስ የማጥቃት ዘመቻ ሊጀምር ይችላል እየተባለ ነው። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ኢትዮጵያ አዳዲስ ድሮኖችን ጨምሮ ተጨማሪ ተዋጊ ጀቶችን ወደ አገር ቤት በዚህ ማስገባቷ ተሰምቷል። ቱርክ ሰራሹ ባይራክ 32 ድሮን እና ተጨማሪ ጀቶች ወደ አዲስ አበባ ሳይገቡ አልቀረም። ከዚህ በፊት በተለያየ ዙር ሲሰለጥኑ የኖሩና በመጀመሪያው የክተት አዋጅ፣ የተመዘገቡ ወታደሮች እስካሁን ማስልጠኛ ካምፕ ውስጥ ቆይተው ሰሞኑን ወደ ወደ ተለያየ ክልል በተለይም ወደ አማራ ክልል ገብተዋል። … [Read more...] about መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል
ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ
ትህነግ ለሌላ አውዳሚ ጦርነት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሀይል እየመለመለ መሆኑን አንድ ዓለም አቀፍ ጋዜጠኛ አጋለጠ። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጉዳዩን በሚገባ ተገንዝቦ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት መወጣት እንዳለበትም ገልጿል። በአሸባሪው ትህነግ ጠብ አጫሪነት በተቀሰቀሰው ጦርነት ከፍተኛ ጉዳት በደረሰባቸው የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች ጉብኝት ያደረገው "የስኩፕ ኢንዲፔንደንት ዜና" ዋና ኤዲተር አላስቴየር ቶምሶን፤ የአሸባሪው ትህነግ ዋነኛ ፍላጎት ዳግም ጦርነት መቀስቀስ መሆኑን ከኢዜአ ጋር በነበረው ቆይታ ገልጿል። የሽብር ቡድኑ ከዚህ ቀደም በርካቶችን በጦርነት በመማገድ ለሞት መዳረጉን አስታውሶ፤ ቡድኑ አሁንም ተመሳሳይ ተግባር ለመድገም እየተዘጋጀ ስለመሆኑ ነው የተናገረው። ለዚህ ደግሞ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ተዋጊዎች እየመለመለና እያሰለጠነ መሆኑን በአስረጂነት … [Read more...] about ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ
ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች
ሩስያ የክፉ ቀን ወዳጄ ላለቻት ኤርትራ ድሮኖችን በድጋፍ የሰጠችው ለቀጠናው ሰላም ኤርትራ ወሳኝ ሃገር በመሆኗ እና ሩስያ ቀጣይ በኤርትራ ከምጽዋ 40 ኪ/ሜ ርቅት ላይ በኣፍኣቤት ለምትገነባው የጦር ሰፈር እንደ መጀመርያ ግብአትነት በመቁጠር ነው። የድሮን ድጋፉ የተሰጣት ኤርትራ ለአለፉት 3 ወራት በሩስያ ስልጠና የተሰጣቸውን 26 የድሮን ባለሙያዎቿን ጭምር አቀባበል በማድረግ ዛሬ በባፃ የድሮን ጣብያ በድምቀት ተቀብላለች። በዚህ ርክክብ ወቅት የተገኙት የኤርትራው ፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአደረጉት ንግግር "ይህ ከሩስያ የተደረገልን ድጋፍ የኤርትራን የጦር ኃይል በጥራት፣ በልምድ፣ በእውቀትና በታጠቀው የጦር መሳርያ በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ ያደርገዋል" ሲሉ ተደምጠዋል። ባለፈው ወር የኤርትራው ውጭ ጉዳይ ሚ/ር ኦስማን ሳሌህ ሩሲያን በጎበኙት ወቅት የሩሲያው ውጭጉዳይ … [Read more...] about ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች