
“ትዕይንተ ሕዝብ አዘጋጅ ግብረ-ኃይል የቴክኒክ ኮሚቴ” በሚል ልደቱና ነዓምን በሻዕቢያ ምሪት በመሠረቱት ቡድን ውስጥ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መሪ ጃልመሮ በአማካሪው በኩል ጃዋር መሀመድን እንደተካ ልደቱ አረጋገጠ።
ይህ ይፋ ይሆነው ከሦስት ቀን በፊት በተደረገው የቡድኑ ስብሰባ ላይ “ጃዋር ስብሰባ የማይገኝበት ምክንያት ምንድን ነው፧” በሚል ከተሰብሳቢዎች ለቀረበ ጥያቄ ልደቱ መልስ ሲሰጥ ነው።
ብረት ያነሳውና አሸባሪው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በስብሰቡ ውስጥ እንዲገባ የተወሰነበትን ውሳኔ ልደቱ በስብሰባው ይፋ አላደረገም። ልደቱ ባያብራራም ውሳኔው ግን ነዓምንና ጃዋር በሻዕቢያና እንደ ግብፅ ያሉ ሌሎች የውጭ ኃይሎች ምሪት እያደራጁት ያለው ስብሰብ ውሳኔ መሆኑ ታውቋል።
በዚህ ስብሰባ ላይ ግን የጃልመሮ ሠራዊትና ድርጅት በከፍተኛ ደረጃ ክስ ቀርቦበት ነበር። “አብረን መቅመጥ አንችልም” በማለት የተቃወሙ ነበሩ። ሰላማዊ ትግል ወይም ሕዝባዊ እምቢተኛነት በሚል የተሰበሰበ ቡድን ውስጥ የጃልመሮ ዓይነት ቡድን መግባቱ ማነው ይህንን ስብስብ እየመራ ያለው ከሚለው ጀምሮ ብዙ ጥያቄ ጭሯል።
በስብሰባው የተሳተፉ ለአዲስ ሪፖርተር የዋሽንግቶን ዲሲ ተባባሪ እንዳስታወቁት፣ ጃዋርን ተክቶ የገባው ጅሬኛ ጉደታ በተከታታይ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃትና ዘግናኝ ተግባር እየፈጸመ ነው በሚል የሚከሰሰውና በቅርቡ አምነስቲ አስደንጋጭ ሪፖርት ያወጣበት የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አባል ሆኖ ሳለ እዚህ ስብሰብ ውስጥ መግባቱ አነጋግሯል። ጃዋርን መተካቱ ደግሞ ጃዋር ከጃል መሮ ጋር አብሮ እየሠራ ነው የሚለውን ሃሜት ያጸና ሆኗል ብለዋል።
ጅሬኛ ጉደታ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት (OLA) ቃል አቀባይ እና ከፍተኛ አማካሪ ነው። ጅሬኛ፣ በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሱትን ታጣቂዎች በተመለከተ በተለያዩ ወቅቶች ማናቸውንም መግለጫዎችን በመስጠት የሚታወቅ ግለሰብ ነው። የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ታጣቂዎችን የሚወክለው ጅሬኛ ጉደታ፤ የኩምሳ ድሪባ ወይም ጃል መሮ አማካሪመ ነው። በኢትዮጵያ ሕዝባዊ እምቢተኛነት ወይም ዓመፅ ለማስነሳት በተደራጀው ቡድን ውስጥ ጃዋርን ወክሎ በመግባት ከእነ ልደቱ ጋር “የሰላማዊ ትግል አመቻች” እንዲሆን ተደርጓል።
ልደቱ በተደጋጋሚ “ሰላማዊ ትግል ብቻ” ቢልም አሁን አሁን እየወጣበት ያለው መረጃ እርሱ ከሚናገርው ጋር የሚቃረን ሆኗል። በቅርቡ “ትዕይንተ ሕዝብ አዘጋጅ ግብረ፡ኃይል የቴክኒክ ኮሚቴ” ይፋ ባደረገው የጥምር ቡኖች ስብሰባ ቃለ ጉባኤ ከታጣቂ ኃይሎች ጋር በመናበብ እንዲሠራ፣ ለታጣቂ ኃይሎች የአብረን እንሥራ ጥሪ መደረጉን፣ የትጥቅ ትግሉንና ሰላማዊ የሚባለውን ዓመፅ አብሮ ለማስኬድ ዕቅድ ስለማውጣትና ዓመፅ ሲካሄድ ታጣቂ ኃይሎች እንዴት ዓመፁን እንደሚያግዙ ለመምከር በተያዘው ዕቅድ ልደቱ አያሌው ስሙ ቀዳሚ እንደሆነ ተመልክቷል። ልደቱ በፊት ከሚኖርበት አትላንታ ወደ ዋሽንግቶን ዲሲ የተዘዋወረው በነዓምን ዘለቀ በኩል የኑሮ ክፍያ ተደርጎለት እንደሆነ አብረውት የሚሠሩ ይናገራሉ።
አብዛኛውን ጊዜውን በሲልቨር ስፕሪንግ ከተማ ከያሬድ ጋር በአንድ ካፌ የሚያሳልፈው ልደቱ እንዴት ወደ ዲሲ አካባቢ ሊመጣ እንደቻለ ከነገረው ባልደረባው የሰሙ እንዳሉት፣ ክፍያ በነዓምን በኩል ስለሚፈጸምለት ደስተኛ እንዳልሆነም እንዳስታወቀ ነው። ልደቱ ምክንያቱን በግልጽ ባይናገርም ነዓምን ለሻዕቢያ ስለሚሠራ ከዚያ ጋር ይያያዝብኛል ከሚል እንደሆነ ይገመታል።
በተያያዘ የአብሮነት እና ከስምንት የተለያዩ ማህበራትና ሻዕቢያ እንዳደራጃቸው ከሚታወቁ ቡድን መሪዎች እሁድ ለሰኞ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር እኩለ ሌሊት አካባቢ በጋራ እንደሚመክሩ በተነገረው መሠረት ስብሰባውን አካሂደዋል።
በስብሰባው እንዲካፈሉ የተጋበዙ እንዳሉት የስብሰባው ዋና ዓላማ በዋሽንግቶን ዲሲ እና በሎንዶን ለማካሄድ በታሰበው ስብሰባ ላይ እንዴት በጥምረት እንደሚሠራ ለመምከርና ዕቅድ ለማውጣት፣ በሀገር ቤት ዓመፅ የሚነሳበትን አግባብ አስመልክቶ እንዴት በጋራ መሥራት እንደሚገባ ለመምከር ነበር።
እንደ ታማኝ በየነና አንዳርጋቸው ጽጌ ዓይነቶች በይፋ ቅስቀሳውን እንዲቀላቀሉ በዚህ ስብሰባ ላይ መመሪያ እንደሚሰጥ አጀንዳውን የሰሙ አመልክተዋል የነበረ ቢሆንም ስብሰባው በታቀደው መሠረት ስምምነት ላይ ሳይደረስ ተጠናቅቋል። ሆኖም ለዛሬ ረቡዕ በተጠራው ስብሰባ ምርጫውን ሕገወጥ ለማድረግ ሁሉም እንዴት ተባብረውና ተናብበው እንደሚሠሩ አንድ ደረጃ ላይ እንደሚደርሱ በነዓምን በኩል የተሰጠው የውስጥ መመሪያ ያመለክታል።
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ


Leave a Reply