• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል

March 25, 2026 01:04 pm by Editor Leave a Comment

“ትዕይንተ ሕዝብ አዘጋጅ ግብረ-ኃይል የቴክኒክ ኮሚቴ” በሚል ልደቱና ነዓምን በሻዕቢያ ምሪት በመሠረቱት ቡድን ውስጥ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መሪ ጃልመሮ በአማካሪው በኩል ጃዋር መሀመድን እንደተካ ልደቱ አረጋገጠ።

ይህ ይፋ ይሆነው ከሦስት ቀን በፊት በተደረገው የቡድኑ ስብሰባ ላይ “ጃዋር ስብሰባ የማይገኝበት ምክንያት ምንድን ነው፧” በሚል ከተሰብሳቢዎች ለቀረበ ጥያቄ ልደቱ መልስ ሲሰጥ ነው።

ብረት ያነሳውና አሸባሪው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በስብሰቡ ውስጥ እንዲገባ የተወሰነበትን ውሳኔ ልደቱ በስብሰባው ይፋ አላደረገም። ልደቱ ባያብራራም ውሳኔው ግን ነዓምንና ጃዋር በሻዕቢያና እንደ ግብፅ ያሉ ሌሎች የውጭ ኃይሎች ምሪት እያደራጁት ያለው ስብሰብ ውሳኔ መሆኑ ታውቋል።

በዚህ ስብሰባ ላይ ግን የጃልመሮ ሠራዊትና ድርጅት በከፍተኛ ደረጃ ክስ ቀርቦበት ነበር። “አብረን መቅመጥ አንችልም” በማለት የተቃወሙ ነበሩ። ሰላማዊ ትግል ወይም ሕዝባዊ እምቢተኛነት በሚል የተሰበሰበ ቡድን ውስጥ የጃልመሮ ዓይነት ቡድን መግባቱ ማነው ይህንን ስብስብ እየመራ ያለው ከሚለው ጀምሮ ብዙ ጥያቄ ጭሯል።

በስብሰባው የተሳተፉ ለአዲስ ሪፖርተር የዋሽንግቶን ዲሲ ተባባሪ እንዳስታወቁት፣ ጃዋርን ተክቶ የገባው ጅሬኛ ጉደታ በተከታታይ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃትና ዘግናኝ ተግባር እየፈጸመ ነው በሚል የሚከሰሰውና በቅርቡ አምነስቲ አስደንጋጭ ሪፖርት ያወጣበት የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አባል ሆኖ ሳለ እዚህ ስብሰብ ውስጥ መግባቱ አነጋግሯል። ጃዋርን መተካቱ ደግሞ ጃዋር ከጃል መሮ ጋር አብሮ እየሠራ ነው የሚለውን ሃሜት ያጸና ሆኗል ብለዋል።

ጅሬኛ ጉደታ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት (OLA) ቃል አቀባይ እና ከፍተኛ አማካሪ ነው። ጅሬኛ፣ በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሱትን ታጣቂዎች በተመለከተ በተለያዩ ወቅቶች ማናቸውንም መግለጫዎችን በመስጠት የሚታወቅ ግለሰብ ነው። የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ታጣቂዎችን የሚወክለው ጅሬኛ ጉደታ፤ የኩምሳ ድሪባ ወይም ጃል መሮ አማካሪመ ነው። በኢትዮጵያ ሕዝባዊ እምቢተኛነት ወይም ዓመፅ ለማስነሳት በተደራጀው ቡድን ውስጥ ጃዋርን ወክሎ በመግባት ከእነ ልደቱ ጋር “የሰላማዊ ትግል አመቻች” እንዲሆን ተደርጓል።

ልደቱ በተደጋጋሚ “ሰላማዊ ትግል ብቻ” ቢልም አሁን አሁን እየወጣበት ያለው መረጃ እርሱ ከሚናገርው ጋር የሚቃረን ሆኗል። በቅርቡ “ትዕይንተ ሕዝብ አዘጋጅ ግብረ፡ኃይል የቴክኒክ ኮሚቴ” ይፋ ባደረገው የጥምር ቡኖች ስብሰባ ቃለ ጉባኤ ከታጣቂ ኃይሎች ጋር በመናበብ እንዲሠራ፣ ለታጣቂ ኃይሎች የአብረን እንሥራ ጥሪ መደረጉን፣ የትጥቅ ትግሉንና ሰላማዊ የሚባለውን ዓመፅ አብሮ ለማስኬድ ዕቅድ ስለማውጣትና ዓመፅ ሲካሄድ ታጣቂ ኃይሎች እንዴት ዓመፁን እንደሚያግዙ ለመምከር በተያዘው ዕቅድ ልደቱ አያሌው ስሙ ቀዳሚ እንደሆነ ተመልክቷል። ልደቱ በፊት ከሚኖርበት አትላንታ ወደ ዋሽንግቶን ዲሲ የተዘዋወረው በነዓምን ዘለቀ በኩል የኑሮ ክፍያ ተደርጎለት እንደሆነ አብረውት የሚሠሩ ይናገራሉ።

አብዛኛውን ጊዜውን በሲልቨር ስፕሪንግ ከተማ ከያሬድ ጋር በአንድ ካፌ የሚያሳልፈው ልደቱ እንዴት ወደ ዲሲ አካባቢ ሊመጣ እንደቻለ ከነገረው ባልደረባው የሰሙ እንዳሉት፣ ክፍያ በነዓምን በኩል ስለሚፈጸምለት ደስተኛ እንዳልሆነም እንዳስታወቀ ነው። ልደቱ ምክንያቱን በግልጽ ባይናገርም ነዓምን ለሻዕቢያ ስለሚሠራ ከዚያ ጋር ይያያዝብኛል ከሚል እንደሆነ ይገመታል።

በተያያዘ የአብሮነት እና ከስምንት የተለያዩ ማህበራትና ሻዕቢያ እንዳደራጃቸው ከሚታወቁ ቡድን መሪዎች እሁድ ለሰኞ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር እኩለ ሌሊት አካባቢ በጋራ እንደሚመክሩ በተነገረው መሠረት ስብሰባውን አካሂደዋል።

በስብሰባው እንዲካፈሉ የተጋበዙ እንዳሉት የስብሰባው ዋና ዓላማ በዋሽንግቶን ዲሲ እና በሎንዶን ለማካሄድ በታሰበው ስብሰባ ላይ እንዴት በጥምረት እንደሚሠራ ለመምከርና ዕቅድ ለማውጣት፣ በሀገር ቤት ዓመፅ የሚነሳበትን አግባብ አስመልክቶ እንዴት በጋራ መሥራት እንደሚገባ ለመምከር ነበር።

እንደ ታማኝ በየነና አንዳርጋቸው ጽጌ ዓይነቶች በይፋ ቅስቀሳውን እንዲቀላቀሉ በዚህ ስብሰባ ላይ መመሪያ እንደሚሰጥ አጀንዳውን የሰሙ አመልክተዋል የነበረ ቢሆንም ስብሰባው በታቀደው መሠረት ስምምነት ላይ ሳይደረስ ተጠናቅቋል። ሆኖም ለዛሬ ረቡዕ በተጠራው ስብሰባ ምርጫውን ሕገወጥ ለማድረግ ሁሉም እንዴት ተባብረውና ተናብበው እንደሚሠሩ አንድ ደረጃ ላይ እንደሚደርሱ በነዓምን በኩል የተሰጠው የውስጥ መመሪያ ያመለክታል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: lidetu ayalew, Neamin, olf shanee, Shene, wolaitta

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule