“ትዕይንተ ሕዝብ አዘጋጅ ግብረ-ኃይል የቴክኒክ ኮሚቴ” በሚል ልደቱና ነዓምን በሻዕቢያ ምሪት በመሠረቱት ቡድን ውስጥ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መሪ ጃልመሮ በአማካሪው በኩል ጃዋር መሀመድን እንደተካ ልደቱ አረጋገጠ። ይህ ይፋ ይሆነው ከሦስት ቀን በፊት በተደረገው የቡድኑ ስብሰባ ላይ “ጃዋር ስብሰባ የማይገኝበት ምክንያት ምንድን ነው፧” በሚል ከተሰብሳቢዎች ለቀረበ ጥያቄ ልደቱ መልስ ሲሰጥ ነው። ብረት ያነሳውና አሸባሪው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በስብሰቡ ውስጥ እንዲገባ የተወሰነበትን ውሳኔ ልደቱ በስብሰባው ይፋ አላደረገም። ልደቱ ባያብራራም ውሳኔው ግን ነዓምንና ጃዋር በሻዕቢያና እንደ ግብፅ ያሉ ሌሎች የውጭ ኃይሎች ምሪት እያደራጁት ያለው ስብሰብ ውሳኔ መሆኑ ታውቋል። በዚህ ስብሰባ ላይ ግን የጃልመሮ ሠራዊትና ድርጅት በከፍተኛ ደረጃ ክስ ቀርቦበት ነበር። “አብረን … [Read more...] about “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል
Shene
ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ
* ሸኔም ላይ ጉዳት ደርሷል ተብሏል በሁሉም የጎጃም ዞኖች እና በደቡብ ጎንደር የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት ክፍሎች በፋኖ ላይ በወሰዱት እርምጃ አመራሮችን ጨምሮ በርካታዎችን መግደላቸው፣ መማረካቸው እንዲሁም መሥሪያዎችንና ተተኳሾችን መማረካቸውን የመከላከያ ሠራዊት በማኅበራዊ ገጹ አስታውቋል። በሸኔም ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በ6ኛ ዕዝ የኮር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ጋዲሳ ዲሮን ጠቅሶ፤ በሰሜን ሸዋ ዞን ደራ በፅንፈኛው እና አሸባሪው ሸኔ ላይ የምንወስደውን እርምጃ አጠናክረን ቀጥለናል አመርቂ ውጤትም ተገኝቷል ይላል የወጣው መረጃ። ከዚህም በተጨማሪ ኮሎኔል ጋዲሳ ዲሮ ሰሞኑን በፅንፈኛ ቡድኑ ላይ ከፍተኛ እርምጃ በመውሰድ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሣራ ማድረስ ተችሏል ማለታቸውን ዘግቧል። በፋኖ ላይ የደረሰውን በተመለከተ፤ መረጃው የምስራቅ ዕዝ ዘመቻ መምሪያ … [Read more...] about ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ
ፋኖና ኦነግ ሸኔ “ነውጠኛ ቡድኖች” በመባላቸው ለጥገኝነት ማመልከቻ ተቀባይ እንደማይሆኑ ተሰማ
ፋኖና ኦነግ ሸኔ በማጣቀስ በውጭ አገራት የሚቀርቡ የጥገኝነት መጠየቂያ ማመልከቻዎች ተቀባይነት እንደማያገኙ ይህንኑ ጉዳይ በማስፈጸም የሚሠሩ አንድ ባለሙያ ለጎልጉል ጥቆማ ሰጡ። ድርጅቶቹ “ነውጥ ቡድኖች" ወይም “violent group s” በሚል የተፈረጁበት አግባብ መኖሩንም አክለው ገልጸዋል። ከአገራቸው በተለያዩ ምክንያቶች ተሰድደው ጥገኝነት የሚጠይቁ ወገኖች ከለላ ለማግኘት በሚያስገቡት የስደተኝነት ማመልከቻ በአሁኑ ሰዓት እንደየብሔራቸው ወይም ብሔራቸውን በመቀየር በብዛት በማስረጃነት የሚጠቀሙት የፋኖና የኦነግ ሸኔን ትግል እንደሆነ ይታወቃል። “ለምሳሌ በካናዳ ድርጅቶቹ “violent groups” ተብለዋል" የሚሉት የሕግ ባለሙያ ይህን የተረዱት በሥራቸው አማካይነት የደንበኞቻቸውን ጉዳይ ሲከታተሉ ነው። ባለሙያው ከተሞቹን ለይተው በስም ባይጠሩም መረጃውን የሰሙት … [Read more...] about ፋኖና ኦነግ ሸኔ “ነውጠኛ ቡድኖች” በመባላቸው ለጥገኝነት ማመልከቻ ተቀባይ እንደማይሆኑ ተሰማ



