• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ፋኖና ኦነግ ሸኔ “ነውጠኛ ቡድኖች” በመባላቸው ለጥገኝነት ማመልከቻ ተቀባይ እንደማይሆኑ ተሰማ

January 28, 2024 03:36 am by Editor 1 Comment

ፋኖና ኦነግ ሸኔ በማጣቀስ በውጭ አገራት የሚቀርቡ የጥገኝነት መጠየቂያ ማመልከቻዎች ተቀባይነት እንደማያገኙ ይህንኑ ጉዳይ በማስፈጸም የሚሠሩ አንድ ባለሙያ ለጎልጉል ጥቆማ ሰጡ። ድርጅቶቹ “ነውጥ ቡድኖች” ወይም “violent group s” በሚል የተፈረጁበት አግባብ መኖሩንም አክለው ገልጸዋል።

ከአገራቸው በተለያዩ ምክንያቶች ተሰድደው ጥገኝነት የሚጠይቁ ወገኖች ከለላ ለማግኘት በሚያስገቡት የስደተኝነት ማመልከቻ በአሁኑ ሰዓት እንደየብሔራቸው ወይም ብሔራቸውን በመቀየር በብዛት በማስረጃነት የሚጠቀሙት የፋኖና የኦነግ ሸኔን ትግል እንደሆነ ይታወቃል።

“ለምሳሌ በካናዳ ድርጅቶቹ “violent groups” ተብለዋል” የሚሉት የሕግ ባለሙያ ይህን የተረዱት በሥራቸው አማካይነት የደንበኞቻቸውን ጉዳይ ሲከታተሉ ነው። ባለሙያው ከተሞቹን ለይተው በስም ባይጠሩም መረጃውን የሰሙት ከሚመለከታቸው አካላት እንደሆነ አልሸሸጉም።

ሁሉም አገራት በኢትዮጵያ ባሏቸው ኤምባሲዎችና ዲፕሎማቶች፣ ከዓለም ዓቀፍ ድርጅት ሪፖርቶችና በምሥጢር በሚቀርቡላቸው የስለላ ሪፖርት ስለፈለጉት ዜጎች ከሚያውቁት በላይ መረጃ እንዳላቸው ያስታወቁት ባለሙያው “ይህ ጸሐይ የሞቀው የዓለም ዕውነት ነው” በማለት ነው።

በዚሁ መነሻ ጥገኝነት የሚሰጡት የምዕራቡ ዓለም አገራት ስለ ፋኖና ኦነግ ሸኔ አየር ላይ በቡድኖቹ ደጋፊዎችና የራሳቸው ሚዲያዎች የሚባለውን ሳይሆን አገራቱ እንደ መረጃ የሚወስዱት በራሳቸው አገባብ የራሳቸው መረጃ በመሰብሰብ ነው። በዋናነት ስለ አገራቱ ባላቸው መረጃ ተንተርሰው  የስደተኞችን ማመልከቻ እንደሚያስተናገዱ የጠቆሙት የመረጃው ባለቤት “ስደተኛ ተቀባይ አገራት ስለሁሉም እንቅስቃሴ ባዕድ አይደሉምና ራስን በመረጃ ማብቃት ግድ ነው” ብለዋል።

“እኔ” አሉ የሕግ ባለሙያው “እኔ ይህን የምለው ስደት ጠያቂዎች ተስፋቸው እንዳይጨልም ነው። የስደት ማመልከቻ ምላሽ እንደሚቀያየር ቢታመንም አሁን ላይ ያለው እውነት ግን ይህ ነው” በማለት መረጃውን አጋርተዋል።

ከለላ ሰጪ አገራት እንደ ፖለቲካ ፍላጎታቸው፣ ዓላማቸውና በወቅቱ ካለው መንግሥት ጋር ካላቸው ግንኙነት አንጻር እያወቁ እንዳላወቁ በመሆን ዓላማቸው እንዲሳካ ሲሉ የስደት ማመልከቻ ላይ ያላቸው ቁጥጥር እንደሚጠብቅና እንደሚላላ ይታወቃል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የጥገኝነት ማመልከቻ ጭራሽ ቁጥጥር አልባ የሚሆንበትና ለይስሙላ ማመልከቻ የሚቀርበበት አግባብ እንዳለ አስታውሰው “አሁን ላይ ድርጅቶቹ “violent groups” ስለተባሉ ተጠንቀቁ” ሲሉ ጥገኝነት ጠያቂዎችን መክረዋል። የሚለወጥ ነገር ካለ ሲለወጥ መረጃውን እንደሚያካፍሉም ጠቁመዋል።

የሕግ ባለሙያው ባሉበት አካባቢ ያለውን ጠቅሰው የሰጡትን መረጃ ተከትሎ ያነጋገርናቸው “ስለተባለው ጉዳይ ለጊዜው መረጃ” እንደሌላቸው ጠቁመው “አሁን የሰላም ድርድር ጥያቄ ቀርቧል፤ የተወሰነ ርቀትም እየሄደ እንደሆነ ይሰማል፤ ይህንን እያካሄዱ ያሉት አገራት ደግሞ ጥገኝነት የሚፈቅዱት ዋናዎቹ አገራት ናቸው። የሰላም ስምምነቱን የማይቀበሉ ከሆነ “violent groups” ከሚለው ከፍ ብሎ ሊሄድ የሚችል ፍረጃ እንደሚኖር አመላካች ነው” ብለዋል።

በሌላ አነጋገር አሁን ላይ በስፋት እየተነገረ ያለው ድርድር ወደ ፍሬ እንዳይመጣ ቡድኖቹ የሚያደናቅፉ ከሆነ እንደነ አልቃይዳ በዓለምአቀፍ ደረጃ የአሸባሪ ቡድኖች ቋት ውስጥ የሚመደቡ ይሆናል። ይህም ከሁለቱ ቡድኖች የሚሰጥ የድጋፍ ማስረጃ በየትኛውም ዓለም በጸረ-አሸባሪነት ትግል ውስጥ ያሉ አገራት ለጥገኝነትን የማይቀበሉት ይሆናል። እንዲህ ያለውን መረጃ ይዘው የሚመጡም የአሸባሪ ድርጅት አባል ተብለው ጥገኝነት በሚጠይቁበት አገር ክስ ሊመሠረትባቸው እንደሚችል ቀደምት አሠራሮች ይጠቁማሉ።

በዘመነ ትህነግ የሥርዓቱ ሰዎች ባገኙት መድረክ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 11 በመቶ አድጓል እያሉ ሲደሰኩሩ በመቆየታቸው በየአገራቱ የሚገኙ ጥገኝነት ጠያቂዎች ጉዳያቸው ውድቅ ሲደረግባቸው መቆየቱ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው። ከጥገኝነት ሰጪ አገራቱ ሲነገር የነበረው ምክንያት “አገራችሁ በልማት እያደገች ነው፤ 11 በመቶ ዕድገት በተከታታይ እያስመዘገበች ነው፤ ስለዚህ መሰደድ የለባችሁም” የሚሉ ተስፋ አጨላሚና ቅስም ሰባሪ ምክንያቶች ይሰጡ እንደነበር ይታወሳል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Asylum seekers, Fano, operation dismantle tplf, Shene

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    January 28, 2024 07:36 pm at 7:36 pm

    በዘር በጎሳ በቋንቋ እያላከኩ ተጨቆንኩ አስራቡኝ ገደሉን ገለመሌ እያሉ ጥገኝነት ማግኘት ቀርቷል። ዛሬ የውሸት ፊኛ ነፍተው ማመልከቻ ያስገቡ ሁሉ እየተደረሰባቸው ወደ መጡበት እየተሸኙ ነው። ትላንት ኤርትራዊው ኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት አርጋን እያለ በአረብና በአውሮፓ ምድር በዚህም በዚያም ጥገኝነት ሲያገኝ፤ ወዲያው ትግሬውና አማራውም በኤርትራ ስም ሲነግድ ፤ቆይቶ አሁን ደግሞ ሌሎች ብሂርተኞች ጥገኝነት ፈላጊ ሆኑ። እውነትን ለማወቅ የዘገዪ ወይም ሆን ብለው ኢትዮጵያን ማፈራረስ የሚፈልጉ እንደ ግብጽ ያሉ በዚህም በዚያም እሳት እያቀበሉና አይዞአችሁ በማለት ባህር ቢያሻግሯቸውም ጊዜው አሁን የስደተኛ አይደለም። ተሰዳጅ ከመብዛቱ የተነሳ ሃገራት ለረጅም ጊዜ የነበራቸውን የስደተኞች አቀባበል ፓሊሲ እየቀየሩ ይገኛሉ። በቅርቡ በፓናማ በኩል ብዙ ሺህ ዶላር ከፍለው ወደ አሜሪካ ሊገቡ ሲሉ የተይዙት ቻይናዊያን ወደ ሃገራቸው እንደተመለሱ ማንበብ ያስፈልጋል። ገና ብዙ ገመና ይመጣል!
    አሁን በሜክሲኮ በኩል በሺህ የሚቆጠር ህዝብ መጉረፉም ለመከራ እንጂ ለጤና አይሆንም። በተለይ ዶናልድ ትራምፕ ከተመረጠ እየተለቀሙ ወደ መጡበት እንደሚመለሱ የታወቀ ነው። ዛሬ በአሜሪካ፤ በጀርመን፤ በምስራቅ አውሮፓ የነጭ አክራሪዎችና የናዚ ተከታዪች ቁጥር መብዛት ከስደተኛ ጥላቻ ጋር የተያያዘ ነው። በእርግዝና ለጉብኝት መጥተው ልጆቻቸን በአውሮፓና በአውስትራሊያ እንዲሁም በሰሜን አሜሪካ በመውለድ ዜግነት የሚገኝበት መንገድ ሁሉ በቅርቡ ይዘጋጋል። እልፍ ሃብትና ንብረት በሃገራቸው ላይ እያላቸው ከሃገር በመውጣት ባልሰሩበት የመንግስት ተጠዋሪ የሆኑ ወስላቶች ሁሉ የሚጋለጡበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም። ባጭሩ ዓለም ሰልችቶታል። አዋጊና ተዋጊው፤ ተጋዳዩና አጋዳዪ ሌላውን እሳት ውስጥ እየወሸቀ የራሳቸውን ዘመድና አዝማድ ወደ ውጭ በተዘረፈ ሃብትና ንብረት ማመቻቸቱም በሩ እየጠበበ ነው። ፋኖ በለው ኦነግ ሸኔ፤ ወያኔ በለው ሻቢያ ከአሁን በህዋላ ምንም ምክንያት ቢደረደር ጥገኝነት የማግኘት መንገድ እየጠበበና ለመዘጋት ጥቂት እንደቀረው በጉልህ ማየት ይቻላል።
    ዝም ብሎ ውሃ በቀጠነ ጦርነትን እንደ መፍትሄ ከመውሰድ ይልቅ አማራጭ መንገዶችን በሰከነ እይታ መፈተሽ አስፈላጊ ነው። መንግስትም ቢሆን እዚህ ጋ የእኔን ስም ጠርቶ ሲያነጥስ ሰምቼዋለሁ በማለት ሰውን እያፈሱ እስር ቤት ከመክተት ይልቅ ነገሮችን ለማስከን ሆደ ሰፊ መሆን መቻል አለበት። በምንም ሂሳብ አንድ የመንግስት ሃይል በራሱ ህዝብ ላይ ድሮና አውሮፕላን መጠቀም የለበትም። በመገዳደል የሚመጣው ረሃብና መከራ ብቻ ነው። የኦነጉም ሆነ የፋኖው ትግል ሁለ አቅፍ እስካልሆነ ድረስ ትርፍ አያመጣም። ሰው በሰውነቱ የሚከበርባት ኢትዮጵያ እንድትኖር ካስፈለገ ህገ መንግስቱ መቀየር አለበት። ሻቢያና ወያኔ ከዚያም ኦሮሞው የተጋቱት የፈጠራ የፓለቲካ አተላ ለቆሻሻ መዳረግ አለበት። የዛሬ መቶ ዓመት አማራ ይህን ሰራኝ፤ ሚኒሊክ እንዲህ አረገ እያለ በማያውቀው ታሪክ የራስን ሰንካላ ሃሳብ እየሰኩ ህዝብን ማወናበድ መቆም አለበት። ቂምና በቀል የተላበሰ የፓለቲካ ድርጅት ዘላቂነት የለውምና ሌላውን ስንኮንን ዛሬ ላይ በብሄር ነጻነት ስም የሚፈጸመውን በደልና ገመና መመዘን አስፈላጊ ነው። ያለፈ በደልን የሚያሰላ ህዝብ ፈውስ የለውም። ሁሌ እንደተገዳደለና እንደተሰደደ ነው የሚኖረው። ችግሩ ያኔና ዛሬ ዓለም አንድ አለመሆኗ ነው። መጠጊያ የለም። ቀን እያለ ሃገራችን የሁላችን መኖሪያ እንድትሆን አጥብቀን እንስራ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule