* በሶስት ወራት ብቻ ከ6,600 በላይ ወጣቶች በህገ-ወጥ መንገድ ተሰድዋል" - የትግራይ የወጣቶች ጉዳይ ቢሮ በትግራይ ክልል ከተሞች በሚገኙ አውራ መንገዶች "ልጄ በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ስደት ሲሄድ በአጋቾች ተይዞ ይህንን ብር ክፈል፣ ካልከፈልክ ትገደላለህ ብለውኛል እርዱኝ" የሚሉ በትልቅ ባነር በተቀመጠ የወጣቶች ፎቶ አስደግፈው እርዳታ የሚለሙኑ ወላጆች ተበራክተዋል። ከነዚሁ ወላጆች የአክሱም ከተማ ነዋሪዋ ወ/ሮ ኣስካለ ውብኣንተ አንድዋ ሲሆኑ፤ ይጦረኛል ብለው ኮስኩሰው አስተምረው ያሳደጉት ወንድ ልጃቸው ህገ-ወጥ ስደት የነጠቃቸው እናት ናቸው። "ልጄ በጦርነቱ ማግስት በአከባቢው የስራ እድል በማጣቱ በህገ-ወጥ መንገድ የተለያዩ ሃገራት ደንበር አቋርጦ ሊብያ ሲደርስ ለሰው ህይወት ቁብ በሌላቸው ሽፍቶ እጅ ወድቆ ቁም ስቅሉን እያሳዩት ነው" ብለዋል። "አካል … [Read more...] about በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል
Middle Column
“የድህነት መጠሪያችንን በልጆቻችን መበቀል” አለብን
አብርሆት የትውልዶችን ልቦና በእውቀት ለማብራት የተቋቋመ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኀበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በሕንፃው ምሰሶዎች ጥበብ የሚለው ቃል በ18 የራሳቸው ፊደል ባላቸው ቋንቋዎች ተፅፎ የሚገኘውም ለዚህ ተልዕኮ ያለውን ቁርጠኝነት ለማመላከት ነው ብለዋል። አብርሆት ቤተመፃህፍት በብልሃት ክህሎት የተጎናፀፉ ወጣቶችን የማብቃት አላማውን በትጋት በመወጣት ላይ እንደሚገኝም አስታውቀዋል፡፡ ዛሬ በአብርሆት ያገኘኋቸው ወጣቶች እንደ ሮቦቲክስ እና የፈጠራ ትግበራ ሥራዎች ላይ ተጠምደው ስላገኘኋቸው አድናቆት እና ማበረታቻ ይገባቸዋል ብለዋል። መጪው ትውልድ ከኢትዮጵያ የልማት ግቦች ጋር በተናበበ ሁኔታ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በኮዲንግ፣ በሳይበር ሴኩሪቲ እና በመሳሰሉት ዘርፎች ክህሎታቸውን … [Read more...] about “የድህነት መጠሪያችንን በልጆቻችን መበቀል” አለብን
የትግራይ አበጋዞች ሽኩቻ
ከበረሃ ውንብድና አገረ መንግሥትን ወደመምራት ሳያስበው የተቀበለው ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር በማለት በነጻ አውጪ ስም አንዲት ሉዓላዊት አገር ጠርንፎ በአናሳዎች በግፍ ሲገዛ የነበረው የወንበዴዎች ቡድን ጎራ ለይቶ በአደባባይ መካሰስ ከጀመረና ውዝግቡም እየተካረረ መጥቶ ትግራይን እንደ አፍጋኒስታን ወይም ኢራቅ በጦር አበጋዞች ከፋፍሎ ወደለየለት ደረጃ እየወሰዳት መሆኑ በቅርቡ የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ። የቡድኑ መሪ የሆነው ደብረጽዮን እነ ጌታቸው የሚከሱኝ በፊትም ጦርነት ውስጥ ያስገባንና ሚሊዮኖችን ያስጨፈጨፈው ትህነግ ነው፤ አሁንም መልሶ ጦርነት ውስጥ ሊከተን ነው፤ ጦርነት ናፋቂ ነው እያሉ ነው፤ ነገር ግን ተጨፈጨፈ የተባለው ሕዝብ ማስረጃ የታለ? ባለተጨበጠና ባልተረጋገጠ፤ ማስረጃ በሌለው እኔን መክሰስ ብቻ ስለፈለጉ ባልሞተ ሕዝብ ይከስሱኛል በማለት … [Read more...] about የትግራይ አበጋዞች ሽኩቻ
የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አመራሮች በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ክስ ተመሰረተባቸው
* በሁሉም ባንኮች ያለው ሒሳብ ታገደ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስን ጨምሮ አራት አመራሮች በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር እና ሌሎች ተያያዝ ጉዳዮች ክስ ተመሰረተባቸው። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በሁሉም ባንኮች ያለው ሒሳብ ታገደ። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፤ ዐቃቤ ነዋይዋ ዶ/ር ኤደን አሸናፊ፣ ዋና ፀሐፊ አቶ ዳዊት አስፋው እና ምክትል ፀሐፊ አቶ ገዛኸኝ ወልዴም ከተከሳሾቹ መካከል ነው። ክሱን የመሰረቱት ሻለቃ አትሌት ኃይሌ_ገብረሥላሴ፣ አትሌት ገዛኸኝ አበራ፣ የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ ቴኒስ ፌዴሬሽን ናቸው። በከሳሾቹ ጠበቆች በኩል ክሱ የቀረበለት የፌደራል አንደኛ ደረጃ ፍርድ ቤት አራድ ምድብ ችሎት ኮሚቴው ፤ ግንቦት 5 እና ሰኔ 4፤ 2016 ዓ.ም. ያካሄዳቸው ጠቅላላ ጉባኤዎች እና ውሳኔዎች እንዲታገዱ ትዕዛዝ … [Read more...] about የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አመራሮች በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ክስ ተመሰረተባቸው
ገዱ: “የዘር ማጥፋት ወንጀለኛ ነው እንክሰስው”፤ “ባለውለታ ነው እንጠቀምበት”
ሰሞኑን ለጥገኝነት ማመልከቻቸው ደጋፊ ነው የተባለለትን ዘለግ ያለ ጽሑፍ ያቀረቡት ገዱ አንዳርጋቸው በትግራይ ማኅበረሰብ ዘንድ የተከፋፈለ ዕይታ የፈጠሩ መሆናቸው ተነገረ። ““የዘር ማጥፋት ወንጀለኛ ነው፤ እጃችን ገብቷል እንክሰሰው” ባዮች በርተተው የታዩ ቢሆንም “ባለውለታችን ነውና አሁንም እንጠቀምበት” የሚሉ በሌላ ወገን ድምጻቸውን እያሰሙ ነው። በዘመነ ትህነግ የሥርዓቱ ተላላኪና ጉዳይ ፈጻሚ የነበሩት ገዱ አንዳርጋቸው የዚያን ጊዜው አለቆቻቸውን ለማስደሰት ያልታዘዙትን፣ ያልተጠየቁትን እላፊ በመሄድ በመፈጸም አለቆቻቸውን እጅ በመንሳት ይታወቃሉ። ለዚህ ታማኝነታቸው በአማራ ሕዝብ ላይ የመጨረሻውን ሥልጣን እንዲያገኙና ሎሌነታቸውን የበለጠ በደስታ እንዲፈጽሙ አድርጓቸዋል የሚሉ ጥቂት አይደሉም። እንደማሳያም የወልቃይትን ጉዳይ ይጠቅሳሉ። ገዱ አንዳርጋቸው ከዚህ በታች ያለው … [Read more...] about ገዱ: “የዘር ማጥፋት ወንጀለኛ ነው እንክሰስው”፤ “ባለውለታ ነው እንጠቀምበት”
“እንደ ጌታቸው ዐቢይን አልተሳደብኩም፤ ለምን ሥልጣን ከለከሉኝ?” ደብረጽዮን
ጌታቸው ረዳ በድምጸ ወያኔ በርካታ ምሥጢር ይፋ አድርገዋል፤ ወደ ሚዲያ የወጣበት አንዱ ምክንያት “በስብሰባ ላይ መናገር ስላልቻልሁ” ነው በማለት ተናግሯል። ደብረጽዮንን ጨምሮ የተለያዩ የትህነግ አመራሮችም ሆኑ የወታደር አዛዦች የፕሪቶሪያውን ስምምነት “ባክህን አድነን ፈርም፤ አለበለዚያ ወደ ቆላ ተምቤን ልንሄድ ነው” እያሉ ይገፉት እንደነበር ገልጾዋል። እነ ደብረጽዮን ይህን ባደረጉ ማግስት “ከጀግና ወደ ባንዳ ወደ ይሁዳ” እንዳወረዱትም ጌታቸው በግልጽ አመልክቷል። የፕሪቶሪያው ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ደብረጽዮን በየቦታው እየዞረ “በቅልጥማችን ወይም በጉልበታችን ፌዴራል መንግሥትን ወደ ጠረጴዛ አመጣነው” ሲል ተደምጧል። በነጻ ሚዲያ ላይ ከስዩም ተሾመ ጋር ውይይት ያደረገው አርአያ ተስፋማርያም ሌላ የሰጠው መረጃ አለ፤ “በ3ኛው ዙር መከላከያ መቀሌ ሊገባ ሲል እየገሰገሰ ሳለ … [Read more...] about “እንደ ጌታቸው ዐቢይን አልተሳደብኩም፤ ለምን ሥልጣን ከለከሉኝ?” ደብረጽዮን
የዘመናት ማነቆዎችን የበጣጠሰውና ተስፋን የሰነቀው የብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ሥርዓት ማሻሻያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ማሻሻያን አስመልክቶ የሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፦ ኢትዮጵያ በትናንትናው ዕለት መንግሥት አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራምን አስመልክቶ የሰጠውን መግለጫ ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በዛሬው ዕለት የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ማሻሻሉን ያስታውቃል። ከዛሬ ጀምሮ ሥራ ላይ የሚውስው ይህ ማሻሻያ ኢትዮጵያን ተወዳዳሪ ወደሆነና በገበያ ላይ ወደተመሠረተ የውጭ ምንዛሪ ሥርዓት እንደሚያሸጋግራትና በኢኮኖሚ ውስጥ ለረጅም ጊዜ ተንሰራፍቶ የቆየውን የማክሮ ኢኮኖሚ አለመረጋጋትና መዛባት እንደሚያሻሽል ይታመናል። የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ማሻሻያው በአዲሱ የውጭ ምንዛሪ መመሪያ መሠረት የሚተገበር ይሆናል። ይህ የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ማሻሻያ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሀ ግብር ላይ የተመሠረተና … [Read more...] about የዘመናት ማነቆዎችን የበጣጠሰውና ተስፋን የሰነቀው የብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ሥርዓት ማሻሻያ
ቆሻሻ የሚጥሉና ዘንባባ የሚገጩ ቅጣት አንሷል ተባለ
በአዲስ አበባ በየቦታው ቆሻሻ ለሚጥሉና በቅርቡ የተተከሉትን ዘንባባዎች ለሚገጩ የሚከፈለው ቅጣት ያነሰ መሆኑን በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገለጹ። ተግባሩን ለመከላከል የሌሎች አገራት ልምድ ተግባራዊ እንዲደረግና ጥፋቱን ለመቀነስ የቅጣት መጠኑ መጨመር እንዳለበት ነው ነዋሪዎች የተናገሩት። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለከተሞች የሚገኙ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ጋር ባደረገው ኢመደበኛ ጥናት ሁሉም ተጠያቂዎች የሰጡት ምላሽ ጥፋቱን በሚፈጽሙ ላይ የተበየነው ቅጣት ከዚህ መጨመር እንዳለበት ነው። ሌላው የሰጡት ምላሽ የሌሎች አገራትን ተሞክሮ በማጥናት በአገራችን ላይ ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት ሲሆን፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘ እንደ ጥንቃቄ የሰጡት ምላሽ ሁሉም ሰው አውቆ ዘንባባ ስለማይገጭ እንደ አገጫጩ ምክንያትና ዐውድ ቅጣቱም በዚያው መልኩ አጥፊዎችን ከአደጋ አድራሾች … [Read more...] about ቆሻሻ የሚጥሉና ዘንባባ የሚገጩ ቅጣት አንሷል ተባለ
በእስክንድርና በዘመነ ሽኩቻ ፋኖ አንድ መሆን የማይችል ሆኗል – ኮሎኔል አሰግድ
የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ዋና አዛዥ ኮሎኔል አሰግድ መኮንን እጁን ሰጠ በአማራ ክልል በርካታ የታጣቂ ቡድን አባላት እና አመራሮች በመንግሥት የቀረበላቸውን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ሰላማዊ ሕይወት እየመሩ መሆኑን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል አስታውቋል፡፡ የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይሉ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች በአንዳንድ አካባቢዎች የሚታዩትን የፀጥታ ችግሮች በንግግርና በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በመንግሥት ለታጣቂ ቡድን አባላት እና አመራሮች በተደጋጋሚ የሰላም አማራጮች ሲቀርቡ ቆይተዋል፡፡ ይሁንና በክልሎችም ሆነ በፌዴራል መንግሥት እየቀረበ ያለው የሰላም አማራጭ እንዳይሳካ እና ወደ መሬት እንዳይወርድ በተለይም ደግሞ ውጭ ሆነው በትግሉ ስም ጥቅም የሚያግበሰብሱ አንዳንድ ጽንፈኛ … [Read more...] about በእስክንድርና በዘመነ ሽኩቻ ፋኖ አንድ መሆን የማይችል ሆኗል – ኮሎኔል አሰግድ
ቱሪዝም በአማራ ክልል ሊቆም ነው
"... አሁን ቱሪስት የለም" የላሊበላ ነዋሪ እስከ 2 ቢሊዮን የሚጠጋ ብርም ከዘርፉ ይገኝ ነበር የአማራ ክልል ቱሪዝም በግጭቱ ምክንያት ሥራ ለማቆም መቃረቡን የክልሉ የባህልና የቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ‼️ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የዐማራ ክልልን ይጎበኛሉ ተብለው ከታቀዱት የውጭ ሀገር ጎብኝዎች ቁጥር የመጡት 20 በመቶ ብቻ መኾናቸውን የገለጸው የባህል እና ቱሪዝም ቢሮ፣ የክልሉ ቱሪዝም በእጅጉ በመዳከሙ ሥራ ለማቆም መቃረቡን አስታውቋል፡፡ የቢሮው ኃላፊ ዶ/ር አየለ አናውጤ ትናንት ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ በክልሉ ተለዋዋጭ ገጽታ እያሳየ የቀጠለው የትጥቅ ግጭት፣ “ዘርፉን ጨርሶ ለማስቆም እየተቃረበ ነው፤” ብለዋል፡፡ በቱሪዝም ዘርፍ የተሰማሩ ወጣቶችም፣ በግጭቱ ሳቢያ ከሥራ ገበታ ውጭ መኾናቸውን አመልክተዋል፡፡ (VOA) ጥር 7 2016 የታተመው … [Read more...] about ቱሪዝም በአማራ ክልል ሊቆም ነው