በክህደት የሚታወቀው ትሕነግ “ዝረፉ፣ ጨፍጭፉ፣ አውድሙ” ብሎ ልኮ ላስጨረሳቸው ሁሉ በጅምላ “የሰማዕትነት ማዕረግ” አከናንቦ ሐዘን አውጇል። ይህ የትሕነግ የሰማዕትነት ማዕረግ የመንዙን መብረቅ እሸቴን፣ ኮሎኔል ማራኪዋ ምክትል ዐሥር አለቃ ገበያነሽ ደባልቄን፣ የክምር ድንጋዩ ትንታግ ጌጤ መኳንንት አባ ረፍርፍ፣ በስልኩ ብቻ 15 የጁንታ ታጣቂዎችን ማርኮ፤ 40ዎቹን እንዲደመሰሱ ያደረገው የጋይንቱ ጀግና ሰፊው በቀለ ናደው፣ የምድር ድሮኖች (አፋር) - የዕቶን ውስጥ ነበልባሎችን፣ አገር ብለው ከየአቅጣጫው የተመሙ የኢትዮጵያን ልጆች “አሸባሪ” አድርጎ መፈረጅ መሆኑን ስንቶች ተረዳን? ሸዋ ደብረብርሃን አፍንጫ ሥር፣ ወሎ፣ ጎንደር፣ አፋርን አካልሎ ደጋግሞ የወረረ፣ የዘረፈ፣ መነኩሴ የደፈረ፣ ንጹሐንን የጨፈጨፈና ንብረት ያወደመ፣ እንስሳት ሳይቀር የረሸነ፣ … [Read more...] about እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ!
tdf
ትህነግ በሰሜን ወሎ የፈጸመው ጭፍጨፋ የሳተላይት መረጃ
ከሰሞኑን በእንግሊዙ የቴሌግራፍ ጋዜጣ የወጣው የምርመራ ሪፖርት መነጋገሪያ ሆኗል። ሪፖርቱ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ አከባቢ አጋምሳ ተብላ የምትጠራ ከአፋር ክልል የጥቂት ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ መንደር ሙሉ በሙሉ መውደሙን በሳተላይት ምስል በታገዘ ሁኔታ ቀርቧል። ሪፖርቱን ያዘጋጀው ጋዜጠኛ ዘካሪያስ ዘላለም፥ በተደረገው የምርመራ ስራና ከአከባቢው ወደ ደሴ የተፈናቀሉት ንጹሃኖች በማነጋገር የጦር ወንጀል የተፈጸመው በአከባቢው ይንቀሳቀሱ የነበሩት የ "ትግራይ ሃይሎች" መሆኑን ደርሰንበታል ብሏል። በተጠቃው አከባቢ ላይ አብዛኛው ነዋሪ በግብርና ስራ የሚተዳደሩ ሲሆኑ ከሳተላይት ምስሎችን በመመልከት ከ50 በላይ ጎጆ ቤቶች መቃጠላቸውንና ቃጠሎዉ ከሃምሌ 26 እለት ጀምሮ መፈጸሙንም ማረጋገጥ መቻሉን የጋዜጣው ሪፖርት ያስረዳል። ጋዜጠኛው፥ የሳተላይት ምስል … [Read more...] about ትህነግ በሰሜን ወሎ የፈጸመው ጭፍጨፋ የሳተላይት መረጃ