• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ትህነግ በሰሜን ወሎ የፈጸመው ጭፍጨፋ የሳተላይት መረጃ

August 19, 2021 09:57 am by Editor Leave a Comment

ከሰሞኑን በእንግሊዙ የቴሌግራፍ ጋዜጣ የወጣው የምርመራ ሪፖርት መነጋገሪያ ሆኗል።

ሪፖርቱ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ አከባቢ አጋምሳ ተብላ የምትጠራ ከአፋር ክልል የጥቂት ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ መንደር ሙሉ በሙሉ መውደሙን በሳተላይት ምስል በታገዘ ሁኔታ ቀርቧል።

ሪፖርቱን ያዘጋጀው ጋዜጠኛ ዘካሪያስ ዘላለም፥ በተደረገው የምርመራ ስራና ከአከባቢው ወደ ደሴ የተፈናቀሉት ንጹሃኖች በማነጋገር የጦር ወንጀል የተፈጸመው በአከባቢው ይንቀሳቀሱ የነበሩት የ “ትግራይ ሃይሎች” መሆኑን ደርሰንበታል ብሏል።

በተጠቃው አከባቢ ላይ አብዛኛው ነዋሪ በግብርና ስራ የሚተዳደሩ ሲሆኑ ከሳተላይት ምስሎችን በመመልከት ከ50 በላይ ጎጆ ቤቶች መቃጠላቸውንና ቃጠሎዉ ከሃምሌ 26 እለት ጀምሮ መፈጸሙንም ማረጋገጥ መቻሉን የጋዜጣው ሪፖርት ያስረዳል።

ጋዜጠኛው፥ የሳተላይት ምስል ሪሰርች ባለሙያዎች ሪፖርቱ ላይ አብረው መስራታቸውን የገለፀ ሲሆን ተቀማጭነቱ በእንግሊዝ የደረገው የDX Open Network ተቋም ባለሙያዎች ምስሎቹን በማጥናት በንጹዓኖች ንብረት የደረሰው ጉዳት በቅርብ ርቀት እንጂ በአየር ሃይል ድብደባ የተፈጸመ አለመሆኑ አረጋገጠዋል።

የአከባቢ ነዋሪዎች ስለ ወድመቱ ሲጠየቁ በቆቦ ሮቢት እና ዙሪያው በአጠቃላይ 3 መንደሮች ቤት ለቤት በመዞር ወይ ደግሞ በከባድ ብረት ድብደባ መውደማቸው የተናገሩ ሲሆን ለግዜው አንዲት መንደር ሙሉ ለሙሉ መጥፋቱንና ቢያንስ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሲቪል መኖሪያ የነበረ ንብረት ወደ አመድ መቀየሩን ተረጋግጧል።

ይህንን ሪፖርት ተከትሎ ለህወሃት ቃል አቀባይ የሆነው ፍሰሃ ተመስገን የ “ትግራይ ሃይሎች” በንጹሃኖች መኖሪያ እርምጃ ወስደዋል የሚለው “ሙሉ ለሙሉ ሃሰት ነው” በማለት ምላሽ ሰጥተዋል። (tikvahethiopia)

በሌላ በኩል በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በአጋምሳ መንደር ላይ የህወሓት የሽብር ቡድን የፈጸመውን ጭፍጨፋ በማጣራት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንደሚያሳውቅ የአማራ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ ቤት አስታወቀ፡፡

የሽብር ቡድኑ በየደረሰበት አሰቃቂ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ፈጽሟል ያሉት  የጽ/ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ይህን ድርጊት በማስረጃ አስደግፎ ማሳወቅ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

አሸባሪው ህወሓት በአካባቢው ይኖሩ የነበሩ የአንድ መንደር ሰዎችን ሙሉ ለሙሉ መግደሉን ተናግረዋል፡፡

ይህም የሽብር ቡድኑ በቆቦ አጋምሳና አካባቢው ላይ የፈጸመው የዘር ፍጅት የቡድኑ የተለመደ ተግባር ማሳያ ነው ብለዋል፡፡

ይህ የሽብር ቡድን በየደረሰበት ተመሳሳይ ድርጊት እየፈጸመ መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ ወደፊት ተመሳሳይ የጅምላ ግድያ የተፈጸመባቸውን አካባቢዎች የክልሉ መንግስት እንደሚገልጽ ተናግረዋል፡፡

የአጋምሳውን የጅምላ ጭፍጨፋ አጣርተን ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ እናሳውቃለን ብለዋል፡፡ (በሰለሞን ጸጋዬ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column, News, Politics, Social Tagged With: agamssa, north wollo, operation dismantle tplf, tdf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule