• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ትህነግ በሰሜን ወሎ የፈጸመው ጭፍጨፋ የሳተላይት መረጃ

August 19, 2021 09:57 am by Editor Leave a Comment

ከሰሞኑን በእንግሊዙ የቴሌግራፍ ጋዜጣ የወጣው የምርመራ ሪፖርት መነጋገሪያ ሆኗል።

ሪፖርቱ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ አከባቢ አጋምሳ ተብላ የምትጠራ ከአፋር ክልል የጥቂት ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ መንደር ሙሉ በሙሉ መውደሙን በሳተላይት ምስል በታገዘ ሁኔታ ቀርቧል።

ሪፖርቱን ያዘጋጀው ጋዜጠኛ ዘካሪያስ ዘላለም፥ በተደረገው የምርመራ ስራና ከአከባቢው ወደ ደሴ የተፈናቀሉት ንጹሃኖች በማነጋገር የጦር ወንጀል የተፈጸመው በአከባቢው ይንቀሳቀሱ የነበሩት የ “ትግራይ ሃይሎች” መሆኑን ደርሰንበታል ብሏል።

በተጠቃው አከባቢ ላይ አብዛኛው ነዋሪ በግብርና ስራ የሚተዳደሩ ሲሆኑ ከሳተላይት ምስሎችን በመመልከት ከ50 በላይ ጎጆ ቤቶች መቃጠላቸውንና ቃጠሎዉ ከሃምሌ 26 እለት ጀምሮ መፈጸሙንም ማረጋገጥ መቻሉን የጋዜጣው ሪፖርት ያስረዳል።

ጋዜጠኛው፥ የሳተላይት ምስል ሪሰርች ባለሙያዎች ሪፖርቱ ላይ አብረው መስራታቸውን የገለፀ ሲሆን ተቀማጭነቱ በእንግሊዝ የደረገው የDX Open Network ተቋም ባለሙያዎች ምስሎቹን በማጥናት በንጹዓኖች ንብረት የደረሰው ጉዳት በቅርብ ርቀት እንጂ በአየር ሃይል ድብደባ የተፈጸመ አለመሆኑ አረጋገጠዋል።

የአከባቢ ነዋሪዎች ስለ ወድመቱ ሲጠየቁ በቆቦ ሮቢት እና ዙሪያው በአጠቃላይ 3 መንደሮች ቤት ለቤት በመዞር ወይ ደግሞ በከባድ ብረት ድብደባ መውደማቸው የተናገሩ ሲሆን ለግዜው አንዲት መንደር ሙሉ ለሙሉ መጥፋቱንና ቢያንስ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሲቪል መኖሪያ የነበረ ንብረት ወደ አመድ መቀየሩን ተረጋግጧል።

ይህንን ሪፖርት ተከትሎ ለህወሃት ቃል አቀባይ የሆነው ፍሰሃ ተመስገን የ “ትግራይ ሃይሎች” በንጹሃኖች መኖሪያ እርምጃ ወስደዋል የሚለው “ሙሉ ለሙሉ ሃሰት ነው” በማለት ምላሽ ሰጥተዋል። (tikvahethiopia)

በሌላ በኩል በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በአጋምሳ መንደር ላይ የህወሓት የሽብር ቡድን የፈጸመውን ጭፍጨፋ በማጣራት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንደሚያሳውቅ የአማራ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ ቤት አስታወቀ፡፡

የሽብር ቡድኑ በየደረሰበት አሰቃቂ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ፈጽሟል ያሉት  የጽ/ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ይህን ድርጊት በማስረጃ አስደግፎ ማሳወቅ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

አሸባሪው ህወሓት በአካባቢው ይኖሩ የነበሩ የአንድ መንደር ሰዎችን ሙሉ ለሙሉ መግደሉን ተናግረዋል፡፡

ይህም የሽብር ቡድኑ በቆቦ አጋምሳና አካባቢው ላይ የፈጸመው የዘር ፍጅት የቡድኑ የተለመደ ተግባር ማሳያ ነው ብለዋል፡፡

ይህ የሽብር ቡድን በየደረሰበት ተመሳሳይ ድርጊት እየፈጸመ መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ ወደፊት ተመሳሳይ የጅምላ ግድያ የተፈጸመባቸውን አካባቢዎች የክልሉ መንግስት እንደሚገልጽ ተናግረዋል፡፡

የአጋምሳውን የጅምላ ጭፍጨፋ አጣርተን ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ እናሳውቃለን ብለዋል፡፡ (በሰለሞን ጸጋዬ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Law, Left Column, News, Politics, Social Tagged With: agamssa, north wollo, operation dismantle tplf, tdf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule