* በስጋት ከቀያቸው የተፈናቀሉት የትግራይ ተወላጆች ቤታቸው ሳይፈርስ፣ ንብረታቸው ሳይጎድል ለዓመታት ጠብቋቸዋል በትላንትናው የፓርላማ ውሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢሉባቦር ዞን ሁሩሙ ወረዳ ይኖሩ የነበሩ የትግራይ ተወላጆችን አስመልክቶ የተናገሩ የብዙዎችን ልብ የነካና ኢትዮጵያዊነትን አድምቆ ያሳየ መረጃ ነበር። “ለምሳሌ ጦርነት ሲጀመር” አሉ ዐቢይ “ከኢሉባቡር ሸሽተው ትግራይ የሄዱ አርሶ አደሮች ነበሩ። ከዛ የመጣችሁ ሰዎች አጥኑ ይሄን ጉዳይ ትክክለኛ መረጃ ነው። “ሰዎቹ ሸሽተው ትግራይ ገብተዋል፤ ኢሉባቡር ያሉ አርሶአደሮች ከእነርሱ ማሳ ቡና ለቅመው ሸጠው ገንዘቡን በአካውንታቸው ያስገባሉ፤ ሰዎቹ የሉም። ከእርሻቸው ላይ የተመረተ ምርት ሸጠው ገንዘቡን በራሳቸው አካውንት ያስገባሉ። “ሰዎቹ 'የኛ ሰዎች በሌለንበት ሰርተው አካውንታችን እያስገቡ ነውና በቃ … [Read more...] about አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ
Social
የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ
የዛሬ እንግዳችን አስከፊውን የሕገወጥ ስደት ገፅታ ታስቃኘናለች። “ሕይወታችንን የሚያሻሽልልን አንዳች ተዓምር እናገኛለን” በሚል ቀቢፀ ተስፋ ባሕር ማዶን መናፈቅ ማቆም እንደሚገባን ልቦለድ ከሚመስለው የግል ተሞክሮዋ እያጣቀሰች ታወጋናለች። ውቅያኖስ ቀዝፈው ለባሕር አውሬና ለጥልቁ ባሕር ወለል ሲሳይ የሚሆኑ ወገኖቻችንን ሕገወጥ ጉዞ ይብቃችሁ ትላለች። ለዓመታት በሕገወጥ ስደት በርካታ ሀገራትን ድንበር አቋርጣ ገብታለች። በተደጋጋሚ ለደላሎችና አጭበርባሪዎች ሲሳይ ሆናለች። ከአንዱ ሀገር ወደሌላኛው ድንበር ጥሳ፣ ጀልባ ተሳፍራ፣ ከእስር ቤት አምልጣ በሕገወጥ መንገድ “ሕይወቴን አሻሽልበታለሁ” ያለችውን ሥራ ሞክራለች። በውጤቱ ግን ተስፋዋን ያጨለመ ክህደት፣ ሕይወቷን ሊቀጥፍ ከጫፍ የደረሰ አጋጣሚ ጋር አጋፍጧታል። በመጨረሻም ከ20 ዓመታት መንከራተት በኋላ ለሀገሯ መሬት በቅታ … [Read more...] about የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ
Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women
Warning: this article contains extremely graphic and distressing testimony and images For two years, Tseneat carried her rape inside her. The agony never faded. It attacked her from the inside out. The remnants of the attack stayed in Tseneat’s womb – not as a memory or metaphor, but a set of physical objects: Eight rusted screws. A steel pair of nail clippers. A note, written in ballpoint pen and wrapped in plastic. “Sons of Eritrea, we are brave,” the note reads. “We have … [Read more...] about Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women
የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት?
በኢትዮጵያ የአጼዎች እና የሥልጣኔ መናገሻነት ስማቸው ከሚጠቁሱት ታሪካዊ ስፍራዎች መካከል ጎንደር አንዷ ናት። ጎንደርን ማዕከል ያደረገው የ17ኛው እና የ18ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ የእድገት፣ የምርት መፍለቂያ፣ የሃይማኖት ማዕከል እንዲሁም በኪነጥበብ ታላቅ ስፍራ የደረሰችበት ወቅት እንደሆነ ይጠቀሳል።። የእነዚህ ታላላቅ ተግባራት ማሳያዎች መካከል ደግሞ ከጎንደር ነገሥታት መካከል አንዱ በነበሩት አጼ ፋሲለደስ በ17ኛው ክፍለ ዘመን የተገነባው የፋሲል ግንብ ነው። በአስደናቂነቱ፣ በታሪካዊነቱ እና በኪነ ህንጻ ጥበቡ ብዙ የተባለለት እና እና በዩኔስኮ የዓለማችን ቅርስ አንዱ ሆኖ የተመዘገበው የፋሲል ግንብ ተሰነጣጥቆ እና አርጅቶ መቆየቱ በርካቶች ሲያነሱት የነበረ ጉዳይ ነው። የጥገና እድሳት እየተከናወለት ያለው ታሪካዊው የፋሲል ግንብ በቅርቡ ይፋ መደረጉን ተከትሎ … [Read more...] about የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት?
ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ?
መግቢያ ሰሞኑን የፋሲል ቤተመንግሥት እድሳት ጉዳይ መነጋገሪያ ሆኗል፤ ምክንያቱ ደግሞ የግንቡ የውጭ ገፅታ ቀለም ከተለመደው ተቀይሮ መታየቱ ነው። ውዝግቡን ተከትሎም በእድሳቱ ስራ ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ ያላቸውም ሆኑ ሌሎች የቅርስ ጥበቃ ባለሙያዎች ምላሾችን ሰጥተዋል። ሆኖም የተሰጡት ምላሾች ውዝግቡን የማቆም አቅም ያላቸው አይመስልም። በፕሮጀክቶች ቅደም ተከተል ላይ ያለንን ጥያቄ ለጊዜው ያዝ እናድርገውና የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የዓለም ቅርስ የሆነው የፋሲል ቤተመንግሥት መታደሱን የሚቃወም የለም። በተለይም ግቢው ውስጥ የተሰራው ላንድስኬፕና ለቱርስቶች የተዘጋጀው የማረፊያ ቦታ በጥሩ ጎኑ የምንመለከተው ነው፤ እንዲሁም የግንቡ መዋቅራዊ ዝንፈቶችን ለማስተካከል የተወሰደው እርምጃም መልካም የሚባል ነው። ሆኖም የብዙዎቻችን ጥያቄና ውዝግብ መንስኤ የሆነው በግንቡ ውጫዊ ገፅታ … [Read more...] about ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ?
የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የተጣለበት ዕግድ ተነሳለት
በፓሪስ ኦሊምፒክ ዋዜማ የተቀሰቀው የእነ ኃይሌና የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውዝግብ ወደ ሕግ ማምራቱ ይፋ ሲሆን “ቀድሞም ቢሆን መሆን የነበረበት ጉዳይ ይህ ነበር። አበጃችሁ” ሲሉ ጉዳይን በረጋ መንፈስ የሚከታተሉ አስተያየት ሰጥተው ነበር። በሕግ ሕግን ማስከበርና፣ በሕግ መብትን ማስጠበቅ እንደሚቻል የሚያሳይ፣ ለሌላው ወገን ደግሞ በሕግ ራስን መከላከልና በሕግ መጠየቅ እንዳለ የሚያስተምር አግባብ እንደሆነ አመልክተው ነበር። ሻለቃ ኃይሌና አትሌት ገዛኸኝ አበራ የሚመሩትና ሁለት ፌዴሬሽኖች የተካተቱበት ወገን ዶክተር አሸብር የሚመሩትን የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከስሰው ኮሚቴው የሚያንቀሳቅሳቸውን የባንክ ሂሳቦችና፣ የዕለት ተለት ክንውን ማካሄድ እንዳይችል አስወስነው የነበረው በሕግ በመሆኑ ዜናው ፍሞ ነበር። ጅማሮውን የትግላቸው ውጤት አድርገው ያቀረቡም ጥቂቶች … [Read more...] about የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የተጣለበት ዕግድ ተነሳለት
የ፲፪ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት የዘንድሮና የአምናው መጠነኛ ንጽጽር
በ2016 ዓም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 684 ሺህ 205 ተማሪዎች ያለፉት 36 ሺህ 409 ወይም 5.4 በመቶ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከትላንት በስቲያ ማስታወቃቸው ይታወሳል። ከዚህ በታች ያለውን መረጃ ያሰባሰብነው ከመንግሥታዊ ሚዲያና ከቲክቫህ ነው። በአጠቃላይ 1 ሺህ 363 ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ ያላሳለፉ ሲሆን በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ 4 ትምህርት ቤቶች ከሐረሪ ክልል ውጭ ሁሉም ክልሎች ላይ አንድም ተማሪ ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን አመላክተዋል።በአጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት ከ500 በላይ ያመጡ ተማሪዎች ባለፈው ዓመት 273 የነበሩ ሲሆን በአሁኑ 1ሺ 220 ተማሪዎች ከ500 በላይ ያመጡ ናቸው ተብሏል።እንዲሁም በዘንድሮ 12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱት ውስጥ 5.4 በመቶ ፈተናውን አልፈዋል ይህም ማለት … [Read more...] about የ፲፪ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት የዘንድሮና የአምናው መጠነኛ ንጽጽር
የኢቲቪ ባለሥልጣናት ኦሊምፒክና አትሌቲክስ ላይ ያነጣጠረ ፕሮፓጋንዳ እንዲሠራ አዘዙ
የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ባለሥልጣናት በኦሊምፒክና በአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ላይ ትኩረት ያደረገ የፕሮፓጋንዳ ሥራ እንዲሠራ መመሪያ መስጠታቸው ተሰማ። መመሪያው ተግባራዊ መሆኑን ተከትሎ ኢቲቪ የሚያቀርበው ዘገባ የሕግ ጥያቄ ማስደገፊያ እንዲሆን ተደርጎ ለመረጃነት እየተዘጋጀ መሆኑ ከሌሎች ወገኖች ተደምጧል። ከፓሪሱ ኦሊምፒክ መጀመር ቀደም ብሎ በማኅበራዊ ሚዲያው የተጀመረው ዘመቻ ሁለት ቡድኖች ጎራ ለይተው ውዝግብ መጀመራቸውን አመላካች እንደነበር ይታወሳል። ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴና አትሌት ገዛኸኝ አበራ ጎራ ለይተውና ተመሳሳይ አቋም ይዘው የለኮሱት ተቃውሞ ውድድሩ ከመጀመሩ ቀናት በፊት ሲሆን፣ ማኅበራዊ ሚዲያው ተቃውሟቸውን ለመግዛትና ለማሰራጨት ጊዜ አልወሰደም። ከወራት በፊት በተጠናቀቀ ምርጫ ላይ ቅሬታ በማንሳት የተጀመረው ክስ ውድድሩ ከተጀመረ በኋላም ከፓሪስ በሚወጡ ዐውዳቸውን … [Read more...] about የኢቲቪ ባለሥልጣናት ኦሊምፒክና አትሌቲክስ ላይ ያነጣጠረ ፕሮፓጋንዳ እንዲሠራ አዘዙ
“የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አእምሮና የደም ዝውውር ሊኖረው ነው”
ሁሉም ባይባልም አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ዋና የፖለቲካ ፕሮግራም ሶሻል ዴሞክራሲ ወይም ሊበራል ዴሞክራሲ ወይም ምርጫን ማዕከሉ ያደረገ ዴሞክራሲያዊ ፖሊሲ ነው። የኢኮኖሚ ፕሮግራማቸው ደግሞ ገበያ መር ኢኮኖሚ ነው። እነዚሁ ፓርቲዎች በምርጫ ክርክር ሲደረግ በዋናነት እያነሱ የሚከራከሩት መንግሥት ኢኮኖሚውን ተቆጣጥሮታል፤ የዕዝ ኢኮኖሚ ነው አገሪቱን ለችግር የዳረጋት፣ የኢኮኖሚው አካሄድ በገበያ እንጂ በመንግሥት መመራት የለበትም በሚል የከረረ ተቃውሞ በማቅረብ ሲቃወሙ ላለፉት በርካታ ዓመታት ሰምተናል። ባለፈው ሰኞ መንግሥት የአገሪቱን ዐቢይ (ማክሮ) ኢኮኖሚ ወደ ገበያ መር የሚወስድ ውሳኔ ይፋ ሲያደርግ እነዚሁ ተቃዋሚዎች “እሰይ ስለቴ ሰመረ” ባይሉም ቢያንስ ለዓመታት ሲሟገቱለት የነበረው ሃሳብ ድል አድርጎ በማየታቸው ጥንቃቄ የተሞላበት ድጋፍ ሊያሰሙ የሚጠበቅ … [Read more...] about “የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አእምሮና የደም ዝውውር ሊኖረው ነው”
የፖሊሲ ጥሰት በፈጸሙ 44 የግል ኮሌጆች ላይ እርምጃ ተወሰደ
የ18 የግል ኮሌጆች ፍቃድ ታገደ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን አደረግኩት ባለው ድንገተኛ የቁጥጥር ስራ የፖሊሲ ጥሰት ፈፅመዋል ያላቸውን 18 የግል ኮሌጆች ፍቃድ አግዷል፡፡ ከታገዱት በተጨማሪ መለስተኛ የፖሊሲ ጥሰት በፈፀሙ 26 የግል ኮሌጆች የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ባለሥልጣኑ በትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት በ2016 ዓ.ም ድንገተኛ ቁጥጥር የተደረገባቸው 59 የግል ኮሌጆች ሲሆኑ 18ቱ ታግደዋል፤ 26ቱ ከቀላል እስከ ከባድ የቃል ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡ በድምሩ 44 የግል ኮሌጆች እርምጃ ተወስዶባቸዋል ተብሏል፡፡ ተቋማቱ እንደደረሳቸው አስተዳደራዊ እርምጃ መሰረት በአስር ቀናት ውስጥ እርምትና ማስተካከያ በማድረግ በጽሁፍና በአካል በመቅረብ ሪፖርት እንዲያደርጉ ባለስልጣኑ … [Read more...] about የፖሊሲ ጥሰት በፈጸሙ 44 የግል ኮሌጆች ላይ እርምጃ ተወሰደ










