የዛሬ እንግዳችን አስከፊውን የሕገወጥ ስደት ገፅታ ታስቃኘናለች። “ሕይወታችንን የሚያሻሽልልን አንዳች ተዓምር እናገኛለን” በሚል ቀቢፀ ተስፋ ባሕር ማዶን መናፈቅ ማቆም እንደሚገባን ልቦለድ ከሚመስለው የግል ተሞክሮዋ እያጣቀሰች ታወጋናለች። ውቅያኖስ ቀዝፈው ለባሕር አውሬና ለጥልቁ ባሕር ወለል ሲሳይ የሚሆኑ ወገኖቻችንን ሕገወጥ ጉዞ ይብቃችሁ ትላለች። ለዓመታት በሕገወጥ ስደት በርካታ ሀገራትን ድንበር አቋርጣ ገብታለች። በተደጋጋሚ ለደላሎችና አጭበርባሪዎች ሲሳይ ሆናለች። ከአንዱ ሀገር ወደሌላኛው ድንበር ጥሳ፣ ጀልባ ተሳፍራ፣ ከእስር ቤት አምልጣ በሕገወጥ መንገድ “ሕይወቴን አሻሽልበታለሁ” ያለችውን ሥራ ሞክራለች። በውጤቱ ግን ተስፋዋን ያጨለመ ክህደት፣ ሕይወቷን ሊቀጥፍ ከጫፍ የደረሰ አጋጣሚ ጋር አጋፍጧታል። በመጨረሻም ከ20 ዓመታት መንከራተት በኋላ ለሀገሯ መሬት በቅታ … [Read more...] about የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ
sudan
የሱዳን ወታደራዊ አመራር ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዶክን በቁጥጥር ሥር አደረገ
የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ በሀገሪቱ ወታደራዊ አመራር የቁም እስረኛ እንዲሆኑ መደረጋቸውን መገናኛ ብዙሀን ዘግበዋል። አል ሃዲት ቲቪ እንደዘገበው ከሃምዶክ በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ኢብራሒም ለ-ሼክ፣ የመረጃ ሚኒስትሩ ሃምዛ ባሉል፣ በሚዲያ ጉዳዮች የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ፋይሳል ሞሐመድ ሳሌህ በተጨማሪ በቁጥጥር ሥር ውለዋል ብሏል። ከእነዚህ በተጨማሪ የገዢው ምክርቤት አፈቀላጤ ሞሐመድ አል-ፊኪ ሱሊይማን እና የዋና ከተማዋ ካርቱም ገዢ አይማን ኻሊድም መያዛቸው ተዘግቧል። ባለፈው ወር በሱዳን የመፈንቅለ መንግሥት ከተሞከረ በኋላ አገሪቱ በተቃውሞ ሰልፍና ከሚሊታሪው ጋር ሲጋጩ በነበሩ የሲቪል ማኅበረሰቦች ስትናጥ ከርማለች። እንደ አልጃዚራ ዘገባ የመገናኛ መሥመሩ በከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል ከሰዎች ጋርም ግንኙነት ለማድረግ በጣም አስቸጋሪ ሆኗል። … [Read more...] about የሱዳን ወታደራዊ አመራር ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዶክን በቁጥጥር ሥር አደረገ


