• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሱዳን ወታደራዊ አመራር ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዶክን በቁጥጥር ሥር አደረገ

October 25, 2021 01:30 am by Editor 1 Comment

የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ በሀገሪቱ ወታደራዊ አመራር የቁም እስረኛ እንዲሆኑ መደረጋቸውን መገናኛ ብዙሀን ዘግበዋል።

አል ሃዲት ቲቪ እንደዘገበው ከሃምዶክ በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ኢብራሒም ለ-ሼክ፣ የመረጃ ሚኒስትሩ ሃምዛ ባሉል፣ በሚዲያ ጉዳዮች የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ፋይሳል ሞሐመድ ሳሌህ በተጨማሪ በቁጥጥር ሥር ውለዋል ብሏል።

ከእነዚህ በተጨማሪ የገዢው ምክርቤት አፈቀላጤ ሞሐመድ አል-ፊኪ ሱሊይማን እና የዋና ከተማዋ ካርቱም ገዢ አይማን ኻሊድም መያዛቸው ተዘግቧል።

ባለፈው ወር በሱዳን የመፈንቅለ መንግሥት ከተሞከረ በኋላ አገሪቱ በተቃውሞ ሰልፍና ከሚሊታሪው ጋር ሲጋጩ በነበሩ የሲቪል ማኅበረሰቦች ስትናጥ ከርማለች።

እንደ አልጃዚራ ዘገባ የመገናኛ መሥመሩ በከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል ከሰዎች ጋርም ግንኙነት ለማድረግ በጣም አስቸጋሪ ሆኗል። ወታደራዊ አመራሩ ወደ ካርቱም የሚወስዱትን መንገዶች በሙሉ ዘጋግቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ሐምዶክ የሽግግር መንግሥቱ በተከፋፈለበት ወቅት “(ይህ ክፍፍል) ሽግግሩን የገጠመው “በጣም አስከፊውና አደገኛው ቀውስ ነው” ማለታቸው ይታወሳል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: hamdok, sudan

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 25, 2021 08:58 am at 8:58 am

    ዓለማችን ልትወጣበት ወደማትችልበት ሽክርክሪት ገብታለች። የሱዳኑ ቀውስ የታለመና የታቀደ በመሆኑ ለግብጽና ለሌሎች ጽንፈኛ መለዪ ለባሾች የወረፋ የስልጣን መውጫ መሰላል ነው። ሱዳን ልክ እንደ ግብጽ ሁሌም ጠበንጃ አንጋች የሚፍገመግማት ሃገር ናት። ግን የሱዳን ደም አፍሳሽ ወታደሮች ያልገባቸው ጊዜው መቀየሩን ነው። የወታደራዊ መንግሥት ዛሬ ለአለንበት ዓለም አይመጥንም። ወደፊትም ተቀባይነት አይኖረውም። ለፈስፋሳው አብደላ ሃምዶክ የራሱን ቤት ከማስተካከል ይልቅ በድንበር ይገባኛልና በወያኔ ድጋፍ ሰጭነት ጊዜውን በማባከኑ ይኸው ዛሬ ላለበት ውርደት ደርሷል። ራሱ የሱዳን ወታደራዊ ሃይሎች ነበሩ ተደጋጋሚ የግድያ ሙከራ ያደረጉበት። ሲጀመር አሜሪካን መጠለያ ያደረገ ውጤቱ ፍሬ ፈርስኪ ነው። ሆን ተብሎ ሰው በአደባባይ በመውጣቱ ወታደሩ ስልጣን እንዲወስድ ያስጠየቁት፤ መገቢ መንገዶች እንዲዘጉና ምግብና ሌላም ነገር ለከተማዋ እንዳይደረስ የተደረገው ልክ እንደ ግብጽ መሬ ሌላ መለዪ ለባሽ በሱዳን ለማስቀመጥ እንዲረዳ ነው።
    ሱዳን በባህረ ሰላጤው ሃብታም ሃገሮች እንካችሁ የምትኖር፤ ብዙም ምርት የሌላት፤ አልፎ አልፎ ከነዳጅ በሚገኝ ሃብት እዚህም እዚያም ለህዝብ ጣል የሚደረግባት ሃገር ናት። ይመስለኛል ሻቢያ ይህ ሁሉ እንደሚመጣ ቀድሞ ስለተረዳ ጦሩን በተጠንቀቅ ካቆመ ሰንብቷል። የወያኔ ፍራቻ እንዳልሆነ አውቃለሁ። እንግዲህ በዚህ የአፈሙዝ ስልጣን ንጥቂያ ሰበብ የሚመጣውን ለመተንበይ ቢያዳግትም የቀድሞው ወታደራዊ መሪ አመራሮች ሁሉ ከእስር የሚፈቱና መልሰው ኮፍያ ለባሾች እንደሚሆኑ ይገመታል። በዳርፉር፤ በኢትዮጵያ ድንበርና በደቡብ ሱዳን በኩል ያሉት ፍትጊያዎችም ከአሁኑ በባሰ ሁኔታ መልሰው ሊቀጣጠሉ ይችላሉ። ሱዳን የድንበር ይገባኛል ጥያቄ ከግብጽ ጋር ሳይቀር ነው ያላት። አልሲሲ በካይሮ አሁን ደስተኛ ነው። ሲመክር፤ ሲዘክር የቆየበት መልሶ በሱዳን እሱን መሰል ወታደራዊ መኮንኖች በአፈሙዝ ስልጣን ላይ መውጣታቸው አስፈንድቆታል። የሱዳን ህዝብ ግን ልክ እንደ ሌላው የአፍሪቃ ህዝብ ከመከራ ወደ መከራ ይሸጋገራል። ለውጥ የምንለው ይህን ነው። እንሰንብት ብዙ እናያለን ገና። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule