• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሱዳን ወታደራዊ አመራር ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዶክን በቁጥጥር ሥር አደረገ

October 25, 2021 01:30 am by Editor 1 Comment

የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ በሀገሪቱ ወታደራዊ አመራር የቁም እስረኛ እንዲሆኑ መደረጋቸውን መገናኛ ብዙሀን ዘግበዋል።

አል ሃዲት ቲቪ እንደዘገበው ከሃምዶክ በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ኢብራሒም ለ-ሼክ፣ የመረጃ ሚኒስትሩ ሃምዛ ባሉል፣ በሚዲያ ጉዳዮች የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ፋይሳል ሞሐመድ ሳሌህ በተጨማሪ በቁጥጥር ሥር ውለዋል ብሏል።

ከእነዚህ በተጨማሪ የገዢው ምክርቤት አፈቀላጤ ሞሐመድ አል-ፊኪ ሱሊይማን እና የዋና ከተማዋ ካርቱም ገዢ አይማን ኻሊድም መያዛቸው ተዘግቧል።

ባለፈው ወር በሱዳን የመፈንቅለ መንግሥት ከተሞከረ በኋላ አገሪቱ በተቃውሞ ሰልፍና ከሚሊታሪው ጋር ሲጋጩ በነበሩ የሲቪል ማኅበረሰቦች ስትናጥ ከርማለች።

እንደ አልጃዚራ ዘገባ የመገናኛ መሥመሩ በከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል ከሰዎች ጋርም ግንኙነት ለማድረግ በጣም አስቸጋሪ ሆኗል። ወታደራዊ አመራሩ ወደ ካርቱም የሚወስዱትን መንገዶች በሙሉ ዘጋግቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ሐምዶክ የሽግግር መንግሥቱ በተከፋፈለበት ወቅት “(ይህ ክፍፍል) ሽግግሩን የገጠመው “በጣም አስከፊውና አደገኛው ቀውስ ነው” ማለታቸው ይታወሳል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: hamdok, sudan

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 25, 2021 08:58 am at 8:58 am

    ዓለማችን ልትወጣበት ወደማትችልበት ሽክርክሪት ገብታለች። የሱዳኑ ቀውስ የታለመና የታቀደ በመሆኑ ለግብጽና ለሌሎች ጽንፈኛ መለዪ ለባሾች የወረፋ የስልጣን መውጫ መሰላል ነው። ሱዳን ልክ እንደ ግብጽ ሁሌም ጠበንጃ አንጋች የሚፍገመግማት ሃገር ናት። ግን የሱዳን ደም አፍሳሽ ወታደሮች ያልገባቸው ጊዜው መቀየሩን ነው። የወታደራዊ መንግሥት ዛሬ ለአለንበት ዓለም አይመጥንም። ወደፊትም ተቀባይነት አይኖረውም። ለፈስፋሳው አብደላ ሃምዶክ የራሱን ቤት ከማስተካከል ይልቅ በድንበር ይገባኛልና በወያኔ ድጋፍ ሰጭነት ጊዜውን በማባከኑ ይኸው ዛሬ ላለበት ውርደት ደርሷል። ራሱ የሱዳን ወታደራዊ ሃይሎች ነበሩ ተደጋጋሚ የግድያ ሙከራ ያደረጉበት። ሲጀመር አሜሪካን መጠለያ ያደረገ ውጤቱ ፍሬ ፈርስኪ ነው። ሆን ተብሎ ሰው በአደባባይ በመውጣቱ ወታደሩ ስልጣን እንዲወስድ ያስጠየቁት፤ መገቢ መንገዶች እንዲዘጉና ምግብና ሌላም ነገር ለከተማዋ እንዳይደረስ የተደረገው ልክ እንደ ግብጽ መሬ ሌላ መለዪ ለባሽ በሱዳን ለማስቀመጥ እንዲረዳ ነው።
    ሱዳን በባህረ ሰላጤው ሃብታም ሃገሮች እንካችሁ የምትኖር፤ ብዙም ምርት የሌላት፤ አልፎ አልፎ ከነዳጅ በሚገኝ ሃብት እዚህም እዚያም ለህዝብ ጣል የሚደረግባት ሃገር ናት። ይመስለኛል ሻቢያ ይህ ሁሉ እንደሚመጣ ቀድሞ ስለተረዳ ጦሩን በተጠንቀቅ ካቆመ ሰንብቷል። የወያኔ ፍራቻ እንዳልሆነ አውቃለሁ። እንግዲህ በዚህ የአፈሙዝ ስልጣን ንጥቂያ ሰበብ የሚመጣውን ለመተንበይ ቢያዳግትም የቀድሞው ወታደራዊ መሪ አመራሮች ሁሉ ከእስር የሚፈቱና መልሰው ኮፍያ ለባሾች እንደሚሆኑ ይገመታል። በዳርፉር፤ በኢትዮጵያ ድንበርና በደቡብ ሱዳን በኩል ያሉት ፍትጊያዎችም ከአሁኑ በባሰ ሁኔታ መልሰው ሊቀጣጠሉ ይችላሉ። ሱዳን የድንበር ይገባኛል ጥያቄ ከግብጽ ጋር ሳይቀር ነው ያላት። አልሲሲ በካይሮ አሁን ደስተኛ ነው። ሲመክር፤ ሲዘክር የቆየበት መልሶ በሱዳን እሱን መሰል ወታደራዊ መኮንኖች በአፈሙዝ ስልጣን ላይ መውጣታቸው አስፈንድቆታል። የሱዳን ህዝብ ግን ልክ እንደ ሌላው የአፍሪቃ ህዝብ ከመከራ ወደ መከራ ይሸጋገራል። ለውጥ የምንለው ይህን ነው። እንሰንብት ብዙ እናያለን ገና። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule