• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ

March 19, 2026 11:54 am by Editor Leave a Comment

  • ሀገር ሙሉ ሕዝብ በሴፍቲኔት እየተረዳ አይደለም
  • የዓለም ባንክ የሰጠው ዕርዳታ ለ700 ሺህ ሕዝብ ብቻ የሚውል ነው

ሰላሳ ዓመት ሞላኝ የሚለውና ብዙዎችም የሚዲያ ጽናት፣ አውራ፣ ወዘተ እያሉ የሚጠሩት አውሬው ሪፖርተር ሀገር ለማፍረስ ቀስ እያለ በመሸርሸር ሥራ ላይ እንደተሠማራ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በተደጋጋሚ በርካታ መረጃዎች አውጥቶበታል፤ ማውጣቱንም ይቀጥላል።

አፍቃሪ ትህነግ የሆነው ሪፖርተርና ባለቤቱ አማረ አረጋዊ ዜና መቀሸብ የተካኑበት ሞያቸው ነው። አካሄዱ ግልጽና ጽንፈኛ የመቃወም ስልት የተከተለ ሳይሆን እንደ ምስጥ ከውስጥ የመቦርቦርና ቀፎ አድርጎ የማስቀረት ነው። በዚህ ስልት የሚዘገቡትን የዜና ዘገባዎችን ማሰራጨት ለሪፖርተር አይጠበቅበትም፤ አፈ-ሰማይ የሆነው የማኅበራዊ ሚዲያ ተቀላቢ፤ ይህ ሁሉንም ማለትም በመንግሥትም፣ በግልም፣ በግብፅም፣ በሻዕቢያም፣ ወዘተ የሚቀለቡትን የሚጨምር ነው፤ በሙሉ ዜናውን ያላንዳች ችግር በማሰራጨት ለሪፖርተር በትጋት ይሠራሉ።

ከሁለት ሳምንት በፊት የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ በሴፍቲ ኔት ለሚታገዙ የሚውል 200 ሚሊዮን ዶላር ማጽደቁን ይፋ አድርጎ ነበር። ሪፖርተር ይቺን ዜና ያቀረባት ልክ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በሴፍቲ ኔት እየተረዳ እንደሆነ በማስመሰል ነው። የሰጠው ርዕስም፤ “የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ለሴፍቲኔት ፕሮግራም የሚውል የ200 ሚሊዮን ዶላር ብድር ማፅደቁን አስታወቀ” የሚል ነበር። ይህንን የሪፖርተር መረጃ ብስራት fm፣ አዲስ ስታንዳርድ፣ ጌጡ፣ ወዘተ ተቀባብለውታል፤ አቀባብለውታል።

ገንዘቡን የሰጠው የዓለም ባንክ እንኳ በዚህ ልክ ልበ-ሙሉነት ርዕስ አልሰጠውም። በባንኩ ድረገጽ ላይ የወጣው መረጃ የተሰጠው ርዕስ እንዲህ የሚል ነው፤ Ethiopia: A New Phase of Support for Safety Nets will Foster Resilience and Create Pathways to Decent Jobs.

ይህ የዓለም ባንክ ዕርዳታ የሪፖርተር ባለቤት የሆነው ትህነግ ኢትዮጵያን ሲግጥ በነበረበትም ጊዜ ሲሰጥ የኖረ ነው። የዛሬ 14 ዓመት የተሰጠውን ዕርዳታ ብቻ ብንመለከት ለማኅበራዊ ሴፍቲ ኔት ብቻ ባንዴ 370 ሚሊዮን ዶላር ነበር የሰጠው። የዋለውም ባጠቃላይ ለ8.3 ሚሊዮን ዜጎች ሲሆን:

  • ከዚህ ውስጥ ሥር የሰደደ የምግብ ዕጦት ለደረሰባቸው 7.6 ሚሊዮን ዜጎች
  • ከተሰጠው ውስጥ 70 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ በአፍሪካ ቀንድ በደረሰው ድርቅ ለተጎዱ
  • ሴፍቲኔቱ የሚያካልላቸው ወረዳዎች 319፤ ክልሎቹም አፋር፣ አማራ፣ ድሬዳዋ፣ ሐረሪ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሊ፣ ደቡብ ሕዝብና ትግራይ ናቸው። 

ያሁኑስ ገንዝብ? ስንት እና ለምን ተግባር እንዲሁም ለነማን ነው የሚውለው?

  • የተሰጠው ገንዘብ ሁለት መቶ (200) ሚሊዮን ነው
  • የሚውለው ለ700 ሺህ ዜጎች ነው
  • ዓላማው ለሥራ ፈጠራ ለሚውሉ ፕሮጀክቶች፣
  • ለምግብ ደኅንነት
  • የአየር ንብረት ለመቋቋም (በቅርቡ በጋሞ ለደረሰው አደጋ አስቀድሞ መከላከያ ሊውል ይችላል)
  • በኑሮ ውድነት ምክንያት ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ ቤተሰቦች ነው።

በአጠቃላይ ገንዘቡ የሚውለው ዜጎችን ከተረጂነት በማላቀቅ በዘላቂነት ራሳቸውን የሚችሉበትን መንገድ ለማመቻቸት ወይም በሁለት እግራቸው እንዲቆሙ ለማገዝ ነው። እንጂ ከትህነግ ዘመን ጀምሮ እስካሁን ድረስ ለኅሊና በሚሰቀጥጥ ትህነግ በሴፍቲኔት እያሰቃየ እንዳለው የትግራይ ወገናችን በድህነት እንዲቀጥል ለማስደረግ አይደለም።

እንዲያውም በትክክል ከተሠራ የዜናው ዋና ርዕስና ሐሳብ መሆን የነበረበት ሌላ ነው። ከላይ እንደተገለጸው የዛሬ 14 ዓመት ለ8.3 ሚሊዮን የሴፍቲኔት ተረጂ የዓለም ባንክ ከረዳና አሁን ደግሞ ለ700 ሺህ ብቻ ከረዳ 7.6 ሚሊዮን የሴፍቲኔት ተረጂ ምን ሆነ? ቁጥሩ መጨመር ሲገባው በዚህ ልክ ለምን ቀነሰ? በሌላ አነጋገር ከ90 በመቶ በላይ የሆነው የሴፍቲኔት ተረጂ ምን ሆነ? መልሱን ሪፖርተር ሊጽፈው አይችልም። “የሙያ ሥነምግባሩ” አይፈቅድለትም። መልሱ ግን ቀላል ነው – ከተረጂነት ስለተላቀቁ ነው!!

የትህነግ ሰዎች እጅግ ጭከና በተሞላበት ሁኔታ የትግራይህን ሕዝብ እስካሁን ድረስ በሴፍቲኔት አቆራምደው እያሰቃዩና የነሱ ተገዢ እያደረጉ የሚፈጽሙትን ግፍ መዘገብ ለሪፖርተር የሙያ ግዴታ አይደለም። እጅግ የሚያሳዝነውና ግራ የሚያጋባው እንዲህ ዓይነቱን የሀገር ጸር የሆነ ሚዲያ መንግሥትም፣ የመንግሥት የልማት ድርጅቶችም፣ የግል ንግድ ባለቤቶችም፣ ሁሉም በሚባል ደረጃ በማስታወቂያና በስፖንሰርነት አይዞህ፣ ሀገር ቦርቡርልን እያሉ በገንዘብ እየተከንባከቡ መደገፋቸው ነው።

ሪፖርተርም ባለቤቱም አውሬዎች ናቸው። አውሬ ደግሞ ወዳጅ የለውም፤ አውሬ አይለምድም፤ ያሳደገውን፣ ያበላ ያጠጣውንም ስልቅጥ አድርጎ የሚበላ፤ የበላበትን ወጭት ሰባሪ ጨካኝ ነው። ጊዜው እስኪደርስለት ግን አድብቶና አድፍጦ ይጠብቃል፤ መበላቱን ያላወቀ ደግሞ “ኑርልኝ” እያለ አውሬውን ይቀልባል፤ ይሸልማል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics, Right Column Tagged With: Feeding the Beast, Feeding the Fox, operation dismantle tplf, Reporter

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule