• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ

June 4, 2026 12:04 am by Editor Leave a Comment

ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ ተከትሎ “ትብብር” የተሰኘው ቡድን ያወጣው መግለጫ በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጠመው። የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ) እና የእናት ፓርቲ አመራሮች “ትብብር” የተባለውን ስብስብ ወክለው ኢኤምኤስ ለተባለው ዩትዩብ የተናገሩት በሀገር ውስጥና በዲያስፖራው ሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ አስነሳ።

ሚስጥረሥላሴ ከኢህአፓና ጌትነት ከእናት ፓርቲ ሆነው “ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ ያልሆነ የጨረባ ምርጫ ነው” በማለት ውድቅ ለማድረግ ቢሞክሩም፣ ሕዝቡ ግን “ቀድሞውኑ ለገዢው ፓርቲ አጃቢና ድራማ አድማቂ ለመሆን የገባችሁ የፖለቲካ ድንኮችና ሆዳሞች ናችሁ” በማለት በብርቱ እያወገዛቸው ይገኛል።

የፖለቲካ ተንታኞችና የውስጥ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት፣ የኢህአፓ እና የ“ትብብር” ጥምረት መሪዎች ቀድሞ የነደፉት ስልት በምርጫው ሂደት ውስጥ ተሳታፊ መስለው በመቆየት፣ ሂደቱ ሊጠናቀቅ ሲል “ምርጫው ፍትሐዊ ስላልሆነ ራሳችንን አግልለናል” በማለት ምርጫውን እና በቀጣይ የሚደረገውን የመንግሥት ምሥረታ ቅቡልነት ለማሳጣት ነበር። ይሁን እንጂ አስቀድሞ የተነደፈላቸውን ስልት ሳይከተሉ በምርጫው ከተሳተፉ በኋላ፤ ምርጫው ተጠናቆ ውጤቱ ከመታወቁ በፊት የተሳተፉበትን ምርጫ “የጨረባ” በማለታቸው፣ በዲያስፖራውና በሀገር ውስጥ የነበራቸው ደጋፊ ሙሉ በሙሉ እምነት አጥቶባቸዋል።

“ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” – የጎልጉል ዘገባ

መሪዎቹ በዩቲዩብ ጥያቄ ላቀረበላቸው ወንድማገኝ ምላሽ በሰጡበት ወቅት፣ ከተመልካቾች የተሰጡት በመቶዎች የሚቆጠሩ አስተያየቶች ፓርቲውና ጥምረቱ ምን ያህል ሕዝብ እንደተጸየፈውና ከባድ ተቃውሞ እያቀረበ እንደሆነ በግልጽ የሚያሳይ ነው።

ከተሰጡት መራራና እጅግ ከረር ያሉ የሕዝብ ትችቶች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦

  • “ለብልፅግና ጥቅም አገልግላችኋል”፦ በርካታ አስተያየት ሰጪዎች ትብብሩና ኢህአፓ “ለአጃቢነት የገቡ ማፈሪያዎች ናቸው፤ አስመሳይ በመሆናቸው ለብልፅግና ጠቅመውታል” ሲሉ፣ ሌሎች ደግሞ “የሙሽራ አጃቢዎች በሕዝብ መታመን ባይችሉም ባጋጣሚው መንገድ ያረጋገጡት ጥቅማቸው ለነሱ በቂያቸው ነው” በማለት መሪዎቹ የግል ጥቅማቸውን አሳደው የሕዝብን ድምጽ በቅርጫት መጣላቸውን ገልጸዋል።
  • “አሁን መለፍለፉ ፋይዳ የለውም”፦ ሕዝቡ ምርጫው ገና ሳይጀመር እንዳይሳተፉ በተደጋጋሚ ሲማጸናቸው እንደነበር ያስታወሱት አስተያየት ሰጪዎች፣ “ወንበር ስታጡ ነው አሁን የምትቀባጥሩት፤ በክብር መጀመሪያውን ባትሳተፉ ኖሮ ትከበሩ ነበር። የማያጠግብ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል” በማለት ተሳልቀውባቸዋል።
  • “የታሪክና የስም ክህደት”፦ የፓርቲውን ስም አስመልክቶ ከተሰጡት ትችቶች መካከል፣ “የኢህአፓ ስም በፅናት፣ በዕውነትና በፖለቲካ ትግል የተገነባ የሰማዕታት ታሪክ ሆኖ ሳለ፣ ዛሬ ለሆድ አደርነትና ለአጋጣሚ ፈላጊነት (Opportunism) መገልገያ ሲደረግ ማየት ያሳዝናል፤ ይህ የሞቱትን ወገኖች ታሪክ መሳደብ ነው” የሚሉ ጠንካራ ወቀሳዎች ቀርበዋል።
  • “እንኳን ሲሸጡን ሲያስማሙን ይገባናል” እና ሌሎች ጠንካራ ስድቦች፦ በርካታ የዲያስፖራና የሀገር ውስጥ ተመልካቾች መሪዎቹን በቀጥታ “ባንዳዎች፣ ሆዳሞችና ዱቄቶች” ሲሉ ጠርተዋቸዋል። አንዱ ተመልካች “እንኳን ሲሸጡን ሲያስማሙን ይገባናል” በማለት መሪዎቹ ገና ከጅምሩ ሕዝብን አሳልፈው ለመስጠት እንደገቡ የገለጸ ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ “ይህች ቀባጭ አይጥ የድመት አፍንጫ እያሸተተች ነው፤ ኢህአፓ የኮርማዎች ዘመን አይሆንሽም” በማለት የአመራሮቹን ድፍረት አውግዟል።
  • በሚስጥረሥላሴ ላይ ያነጣጠሩ፡- በትችቶቹ ውስጥ የአመራሮቹን የግል ጥቅም አሳዳጅነት የሚኮንኑ አስተያየቶች በስፋት የታዩ ሲሆን፣ “እነዚህን ማሀይሞች ባታመጧቸውስ፤ እንዴት እንደጠላዋቸው በተለይ ይች ተንከሲስ አስመሳይ፤ ኢሕአፓ ከእንግዲህ ኢትዮጵያ ውስጥ መቀጠል የለበትም፤ ብልፅግና አጋድሞ ቢግጣችሁ ደስ ባለኝ” የሚል መራር አስተያየት ተሰጥቷል፤ ሌላው ደግሞ “ኢህአፓ አስመሳይ አድርባይ ፓርቲነው” ያለ ሲሆን “ሚስጥረ ስላሴ ሳይሆን ምስጢረ ሴረኛ ነሽ መባል ያለብሽ” ብሏል፤ “ሚስጥረ ያራዳ ልጅ በአሜሪካ ኤምባሲ በኩል ከነ አቢይ ጋር ተደራድራ 200 ሚልየን ተቀባብላለች አሉ ቪላ አየሰራች ነው ኦልድ ኤርፓርት” በማለት አላግጦባታል።

በተለይ ሚስጥረ ሥላሴ ምርጫ ስታደርግ ፎቶዋ ወጥቶ እንደነበር በመጥቀስ ለቀረበላት ጥያቄ ስትመልስ፤ እኔ በዚያ ምርጫ ጣቢያ በዚያ ሰዓት እንደምገኝ ማን እንደነገራቸው አላውቅም፤ ያለ እኔ ፈቃድ ፎቶዬን አንስተው በሚዲያ ላይ መበተናቸው ሕገወጥ ተግባር ነው፤ በቀጣይ አስፈላጊውን አካሄድ የምከተል ይሆናል በማለት ተናግራለች። ሆኖም ግን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ የውጪ አገር ታዛቢዎችን ጨምሮ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በምርጫ ጣቢያ አካባቢ ፎቶ ሲነሱና ቪዲዮ ሲቀረጹ የዋሉ ሲሆን የትኞቹም ያለፈቃዳችን ፎቶ ተነሳን ብለው ሲሞግቱ አልተደመጡም። ከዚህ ይልቅ የሚስጥረ ምላሽ “ስመርጥ መታየት አልፈልግኹም ነበር” የሚል ይመስላል። ፎቶውም ያንኑ የሚመሰክር ይመስላል በማለት የጎልጉል አስተያየት ሰጪ ተናግረዋል።

ኢህአፓም ሆነ እናት ፓርቲ ከምርጫው በፊት በትብብሩ ስም እንዲሁም በራሳቸው ፓርቲ ስም በምርጫው ሒደት ሲሳተፉ የቆዩ ነበር። በምርጫ ክርክሮች በአብዛኛዎቹ ተሳትፈዋል፤ ዕጩዎቻቸውንም አስመዝግበዋል። ምንም እንኳን መንግሥት ለመመሥረት የሚያስችል ዕጩ እንደሌላቸው ራሳቸው በተደጋጋሚ ተናግረው የነበረ ቢሆንም በምርጫ ክርክሩ ወቅት ግን “በምርጫ አሸንፈን መንግሥት ስንመሠረት” እያሉ በድፍረት ሲናገሩ ነበር።

በተለይ ኢህአፓ በአስር ከተሞች ታላቅ ሰልፍ አደርጋለሁ ብሎ ከዚያም የምርጫ ቅስቀሳ አደርጋለሁ ብሎ ቃል ከገባና አንዳንዶች እንደሚሉትም ከዳያስፖራው ብር ከተሰጠው በኋላ ምንም ሳያደርግ መቅረቱ፤ እንዲሁም ለዚሁ ዓላማ የተሠራ የሚመስለውን የቴዲ አፍሮ “ዳስ ጣል” ሙዚቃ እያሰሙና ሕዝብ ያነሳሳልናል ብለው ያሰቡትን ሰንደቅ ዓላማ እያሳዩ አዲስ አበባ ላይ ያደረጉት “የምርጫ ቅስቀሳ” አስር ሰው ብቻ የወጣበት መሆኑ ከፍተኛ ትችትና ወቀሳ አስከትሎባቸዋል።  

በአጠቃላይ፣ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት “ለምርጫው አስቻይ ሁኔታ ሊኖር ይገባል፣ ሕዝባዊ ሰልፍ እንጠራለን” እያሉ ሲቀጥፉ የነበሩት እነዚህ የ“ትብብር” እና የኢህአፓ መሪዎች፣ አሁን ላይ የደረሰባቸውን ውድቀትና የሕዝብ አመኔታ ማጣት ለመሸፈን “የጨረባ ምርጫ ነው፤ ምክር ቤት አንገባም” የሚል ወላዋይና ፋይዳ-ቢስ አቋም ይዘው ብቅ ማለታቸው ይበልጥ እንዳስናቃቸው ሕዝቡ በቁጣ በሰጣቸው ምላሽ አረጋግጧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Election 2026, enat party, eprp, EPRP-D, ethiopian terrorists, Tibibir

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule