ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ ተከትሎ “ትብብር” የተሰኘው ቡድን ያወጣው መግለጫ በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጠመው። የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ) እና የእናት ፓርቲ አመራሮች “ትብብር” የተባለውን ስብስብ ወክለው ኢኤምኤስ ለተባለው ዩትዩብ የተናገሩት በሀገር ውስጥና በዲያስፖራው ሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ አስነሳ። ሚስጥረሥላሴ ከኢህአፓና ጌትነት ከእናት ፓርቲ ሆነው “ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ ያልሆነ የጨረባ ምርጫ ነው” በማለት ውድቅ ለማድረግ ቢሞክሩም፣ ሕዝቡ ግን “ቀድሞውኑ ለገዢው ፓርቲ አጃቢና ድራማ አድማቂ ለመሆን የገባችሁ የፖለቲካ ድንኮችና ሆዳሞች ናችሁ” በማለት በብርቱ እያወገዛቸው ይገኛል። የፖለቲካ ተንታኞችና የውስጥ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት፣ የኢህአፓ እና የ“ትብብር” ጥምረት መሪዎች ቀድሞ የነደፉት … [Read more...] about የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ
EPRP-D
“ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል”
ሰኞ የሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ከተጠናቀቀ በኋላ ኢህአፓ እንደሚሰነጠቅ ተነገረ። አሁን ላይ ፓርቲው በተለይ አመራሩ ኹለት ሊባል በሚችል ጎራ ተከፋፍሎ ውስጥ ለውስጥ እየተናቆረ እንደሆነ ተገልጿል። ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ከተጠናቀቀ በኋላ ለምርጫ በጥምረት ስም የገባው ኢህአፓ እንደሚሰነጠቅ ለጎልጉል የደረሰው መረጃ ይጠቁማል። በተለይ በአመራር ደረጃ ያለው መለያየትና መከፋፈል ፓርቲውን ለመሰንጠቅ አደጋ እንዳበቃው ከመረጃው ለመረዳት ተችሏል። የፓርቲው መሪ አቶ አብርሃም ሃይማኖትም የክፍፍሉን ኹኔታ በሚዲያ ቀርበው የተናገሩ ሲሆን በተለይ በአመራሩ መካከል ከምርጫ ጋር በተያያዘ የተከሰተው አለመግባባት የከረረና እርሳቸውንም ከኃላፊነት እንዲወጡ እያስገደዳቸው መኾኑን ተናግረዋል። አንከር ከተባለ ዩትዩብ ጋር የተነጋገሩት አቶ አብርሃም በርካታ የፓርቲውን ምሥጢሮች ይፋ … [Read more...] about “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል”


