በሀገር ውስጥ ለግማሽ ምዕተዓመት የሽብር ተግባራትን ሲፈጽም የነበረውና ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ/ህወሃት) ተብሎ የሚጠራው ሕገወጥ የአሸባሪዎች ቡድን፤ በፍጥነት ዓለምአቀፍ አሸባሪ ወደመሆን እየተጓዘ እንደሆነ በቅርብ የሚወጡ ሪፖርቶች እየጠቆሙ ነው። በሰኔ ወር 2026 የወጣውን የሚሊተሪ ታይምስ (Military Times) ዘገባ መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ የዜና እንዳለው ዩናይትድ ስቴትስ ጦሯን መቀነሷን ተከትሎ በአፍሪካ የአሸባሪዎች ስጋት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑ ያስረዳል። የአሜሪካ ጦር በአፍሪካ አህጉር ያለውን ውክልና እና የሠራዊት ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱን ተከትሎ፣ በሳህል እና በአፍሪካ ቀንድ አካባቢዎች የጂሃዲስት ቡድኖች ተጽዕኖ እና ጥቃት በአስደናቂ ሁኔታ እያደገ መሆኑን የስትራቴጂክ እና ዓለም አቀፍ ጥናቶች ማዕከል … [Read more...] about “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው”
ethiopian terrorists
አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ
በሰሜን ኢትዮጵያ በድጋሚ ግጭት ለመቀስቀስና ቀጣናዊ ሰላምን ለማደፍረስ ከሻዕቢያ ጋር ጽምዶ ፈጥሮ አደገኛ እንቅስቃሴ ላይ በሚገኘው ትህነግ (ህወሃት) አመራሮችና በቅርብ የቤተሰብ አባላቶቻቸው ላይ ያነጣጠረ የቪዛ እገዳ መጣሉን ተከትሎ የአሜሪካ መንግስት በይፋ አስታውቋል። ይህ ውሳኔ ይፋ የሆነው በኢትዮጵያ ውስጥ በሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ የመንቀሳቀስ ፍቃዱ የተሰረዘውና ሕገወጥ ተብሎ የተፈረጀው የትህነግ ታጣቂ ኃይል ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በቅርቡ በፈጠረው ቀጥተኛ የጦርነት ትንኮሳ ሳቢያ ነው። ትህነግ በተደጋጋሚ በቆሰቆሰው የሰሜኑ ጦርነት አንድ ሚሊዮን ያህል የንጹሃን ዜጎች ህይወት መጥፋቱ እንዲሁም በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወገኖች ለከፋ ረሃብና ለስደት መዳረጋቸው እየታወቀ ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ብሎ የሚጠራው አሸባሪ አሁንም ለሰላም እያሳየ ያለው … [Read more...] about አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ
ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው
ሕገወጡ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) ሰሞኑን “በትግራይ ዲፕሎማሲ እና አድቮኬሲ ካውንስል” ስም ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ ለአውሮፓ ኅብረት እና ለአፍሪካ ኅብረት የጻፈው ደብዳቤ የራሱን ሕገ-ወጥ ድርጊቶች ለመሸፈን እና ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ለማታለል የሞከረበት የተለመደ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ነው። የደብዳቤውን ይዘት እና ወቅታዊ እውነታዎችን መሠረት በማድረግ እውነታውን በሚከተለው መልኩ እናቀርባለን፦ 1. የፕሪቶሪያን ስምምነት ስለማፍረስ እና ስለመሻር ደብዳቤው የኢትዮጵያ መንግሥት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ጥሷል ሲል ይከሳል። ነገር ግን እውነታው ፍጹም ተቃራኒ ነው። ትህነግ የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመሰረዝ በትግራይ ክልል የነበረውን ጊዜያዊ አስተዳደር በኃይል እና በሕገ-ወጥ መንገድ አስወግዷል። ትህነግ በራሱ ፍላጎት የሰላም … [Read more...] about ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው
በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ
ትብብር ለአንድነት ኢትዮጵያን በመወከል በየካ ክፍለ ከተማ ምርጫ የተወዳደሩት አቶ ጌትነት ወርቁ በአርሲ የተከሰተውን አስመልክቶ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ግልፅ ደብዳቤ በፌስቡክ ገጻቸው ከሦስት ቀን በፊት አጋርተው ነበር። አቶ ጌትነት ወርቁ እና መሰል የትብብር ፓርቲ አባላት ለምርጫ ለመወዳደር የገቡት በዓላማ እንደሆነ በተደጋጋሚ ሲነገር የቆየ ሲሆን ምርጫው ከተጠናቀቀ በኋላ የተለያዩ ምሥጢሮቻቸው ይፋ እየሆኑ መጥተዋል። በተለይ በምርጫው ክርክር ወቅት ከራሱ የትብብር ሰዎች፤ አቶ ጌትነትንም ጨምሮ፤ በምርጫው የሚወዳደሩት መንግሥት ለመመሥረት እንዳልሆነ ሲናገሩ መሰንበታቸው የሚረሳ አይደለም። እንዲያውም የፈለገውን ያህል ወንበር ብናገኝ መንግሥት ለመመሥረት አንችልም ብለው በሚዲያ መናገራቸው ትብብር ለምን ይሆን ወደ ምርጫ የገባው የሚል ጥያቄ ሲያስነሳ የቆየ ጉዳይ … [Read more...] about በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ
የጽምዶ ልክፍት
ትሕነግ (የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር - ህወሃት) ከ2010 ዓም ለውጥ በኋላ ሦስት መጠነ ሰፊ የተባሉ ወረራዎችን እንደፈጸም ይታወሳል። በእነዚህ ተዋጊዎችን እንደ ማዕበል (human wave) የማሰለፍ ስልት ከራሳቸው አንደበትና የጽሑፍ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት አንድ ሚሊዮን የሚደርሱ የትግራይ ተወላጆች ህይወት አልፏል። የፕሪቶሪያውን የሰላም አማራጭ ስምምነት ተከትሎ በትግራይ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች እና የሽግግር ወቅት ጊዜያዊ አስተዳደሩ በጦርነቱ ወቅት ተሳታፊ ለመሆን ዕድል የተመቻቸለት ሻዕቢያ በትግራይ እህቶች፣ እናቶችና ተወላጆች ላይ የፈጸመው ግፍም የሚዘነጋ አይደለም። ትሕነግ ለውጡን ተከትሎ ወደ ትግራይ ካፈገፈገ በኋላ “የፌዴራሊስት ኃይሎች” ብሎ የፈረሰውን ኢህአዴግ የሚተካ ሌላ አደረጃጀት ፈጥሮ ወደ አራት ኪሎ ለመመለስ የሚያግደው ምንም ኃይል እንደሌለ “ጦርነት … [Read more...] about የጽምዶ ልክፍት
ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው?
ራሱን የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) በማለት የሚጠራው ሕገወጥ የወንበዴዎች ቡድን ተክሎብን እና ጥሎብን የኼደው መርዝ እስካኹን አልፋታ ብሎን የመከራ ዘመናችንን አርዝሞታል። ሀገርን በዘር ከፋፍሎ፤ ሕዝብን እንደ ከብት በክልል ወስኖ፤ ኢትዮጵያዊነትን በሰፈርና በወንዝ ወስኖ፤ ለዘመናት አብሮ የኖረን ሕዝብ በጠላትነት እንዲተያይ አድርጓል። እንዳሰበው ባይሳካለትም ሀገራችን ከመፍረስ ድና አኹን ያለችበት ቁመና ላይ ትገኛለች። ትህነግ ግን ነጻ አወጣዋለኹ ብሎ ሲነግድበት የነበረውን ሕዝብ የምድር ሲዖል ውስጥ ጨምሮ እያሰቃየው ይገኛል። ወደ ጉዳያችን ስንመለስ፤ ትህነግ መርዙን ተፍቶብን ወደ ትግራይ ኼዶ ቢመሽግም አሁንም ግን ግድያ፣ ደም ማፍሰስ፣ ማፈናቀል፣ አልቆመም። በሀገሪቱ ላይ የሚፈጽመው ዕልቂት የገፊና ጎታች ሤራ እንደሆነ በተደጋጋሚ ያነሳነው ጉዳይ ነው። ጎልጉል በዚህ … [Read more...] about ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው?
የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ ተከትሎ “ትብብር” የተሰኘው ቡድን ያወጣው መግለጫ በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጠመው። የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ) እና የእናት ፓርቲ አመራሮች “ትብብር” የተባለውን ስብስብ ወክለው ኢኤምኤስ ለተባለው ዩትዩብ የተናገሩት በሀገር ውስጥና በዲያስፖራው ሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ አስነሳ። ሚስጥረሥላሴ ከኢህአፓና ጌትነት ከእናት ፓርቲ ሆነው “ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ ያልሆነ የጨረባ ምርጫ ነው” በማለት ውድቅ ለማድረግ ቢሞክሩም፣ ሕዝቡ ግን “ቀድሞውኑ ለገዢው ፓርቲ አጃቢና ድራማ አድማቂ ለመሆን የገባችሁ የፖለቲካ ድንኮችና ሆዳሞች ናችሁ” በማለት በብርቱ እያወገዛቸው ይገኛል። የፖለቲካ ተንታኞችና የውስጥ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት፣ የኢህአፓ እና የ“ትብብር” ጥምረት መሪዎች ቀድሞ የነደፉት … [Read more...] about የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ
ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ
የፌዴራል ፖሊስ በሪፖርተር ላይ ያወጣው መግለጫ የሪፖርተርንና የባለቤቱን ማንነት እንዲሁም ስሑት ሥራውን ያጋለጠ ነው። እንደ ፌዴራል ፖሊስ መግለጫ ሪፖርተር “ስውር ተልዕኮ የተንፀባረቀበት ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ፈፅሟል”። የመግለጫው ሙሉ ቃል ከዚህ በታች ይገኛል። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሪፖርተር ጋዜጣ “ከፍተኛ ባለስልጣናትና ታዋቂ አርቲስቶች ከ98 ቢሊየን ብር በላይ መዝረፋቸው በኦዲት ምርመራ መረጋገጡ ተነገረ" በሚል የዘገበው መረጃ የተዛባ መሆኑን አስታወቀ ሪፖርተር ጋዜጣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የዘጠኝ ወር የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ለተከበረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና የፍትህ ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ሪፖርቱን ለማስረዳት በማስታወሻነት የተጠቀመበትን ጥቅል መረጃ መነሻ በማድረግ፣ ጠቅላላ ይዘቱን በአግባቡ … [Read more...] about ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ
የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ
* ዳያስፖራው ራሱን ከትግሉ እያገለለ ነው ከሚያዚያ 6 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ በተደረገ ተከታታይ ስምሪት የፋኖ ኃይል እጅግ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ተገለጸ። በተለይ በራያ ቆቦ ወረዳ የተደረገው ሥምሪት ባካባቢው በሚገኘው የፋኖ ኃይል የደረሰው ጉዳት መጠነ ሰፊ እንደሆነ ተመልክቷል። በፋኖ ተስፋ የቆረጠው ዳያስፖራ ከሚኖርበት ሀገር የገጠመው ችግር ተጨምሮ ለፋኖ የሚሰጠውን ድጋፍ እየቀነሰ ነው። እስከ ዛሬ ድረስ በራያ ቆቦ ወረዳ በአማያ፣ በባይባዋ፣ በፀበለት እና አካባቢው በተደረገው ተከታታይ ስምሪት የመከላከያ ሠራዊት በፋኖ ላይ ባደረሰው ከፍተኛ ምት ንብረቱን፣ ትጥቁን እና ተተኳሹን በመተው ከአካባቢው ሲለቅቅ የሰሜን ምስራቅ ዕዝ 802ኛ ኮር አካል የሆነው 48ኛ ክፍለ ጦር በተጠቀሱት ቦታዎች እና ልዩ ሥፍራው "አካምባ" በሚባል ቦታ ፈጥኖ በመድረስ የፋኖው ኃይል ጥሎት … [Read more...] about የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ
የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ
የውጭ የደህንነት ተቋማት በአንድ ሀገር ውስጥ ወደፊት ስልጣን ወይም ተፅዕኖ ሊኖራቸው የሚችሉ ወጣቶችን ገና በለጋ እድሜያቸው የመመልመልና የራሳቸውን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ግብ በሚያሳካ መልኩ ኮትኩቶ የማሳደግ ስልትን በስፋት ይተገብራሉ። ይህ ተግባር በዘርፉ "የልሂቃን ቀረጻ" (Elite Capture or Cultivation) ተብሎ የሚጠራ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም የተመረጡ ወጣቶችን የዓለም እይታ (Worldview) ከሀገራዊ ጥቅም ይልቅ የውጭ ሃገር ፍላጎትና ጥቅምን በሚያሳካ መልኩ አድርጎ መቅረጽ ነው። እነዚህ ተቋማት የአንድን ወጣት የወደፊት የመሪነት ዝንባሌ ቀድመው በመረዳት፣ በትምህርት እና በተለያዩ ስልጠናዎች ስም ከሀገሩ በማውጣት የአስተሳሰብ አድማሱን በእነሱ የፍላጎት ልክ ይቀርፁታል። ይህ "Formative age" ወይም የማንነት ቀረጻ ምቹ እድሜ የአንድ ሰው ስብዕና እና … [Read more...] about የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ










