የውጭ የደህንነት ተቋማት በአንድ ሀገር ውስጥ ወደፊት ስልጣን ወይም ተፅዕኖ ሊኖራቸው የሚችሉ ወጣቶችን ገና በለጋ እድሜያቸው የመመልመልና የራሳቸውን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ግብ በሚያሳካ መልኩ ኮትኩቶ የማሳደግ ስልትን በስፋት ይተገብራሉ። ይህ ተግባር በዘርፉ "የልሂቃን ቀረጻ" (Elite Capture or Cultivation) ተብሎ የሚጠራ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም የተመረጡ ወጣቶችን የዓለም እይታ (Worldview) ከሀገራዊ ጥቅም ይልቅ የውጭ ሃገር ፍላጎትና ጥቅምን በሚያሳካ መልኩ አድርጎ መቅረጽ ነው። እነዚህ ተቋማት የአንድን ወጣት የወደፊት የመሪነት ዝንባሌ ቀድመው በመረዳት፣ በትምህርት እና በተለያዩ ስልጠናዎች ስም ከሀገሩ በማውጣት የአስተሳሰብ አድማሱን በእነሱ የፍላጎት ልክ ይቀርፁታል። ይህ "Formative age" ወይም የማንነት ቀረጻ ምቹ እድሜ የአንድ ሰው ስብዕና እና … [Read more...] about የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ
Jawar Mohammad
በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ
አሁን ላይ ጃዋር የፖለቲካ ምሕዋሩን ስቶ የሚሄድበትን መንገድ የማያውቅ ሆኗል። በዚህ ኪሣራ ውስጥ ተስፋ ሰጪ ሆኖ ያገኘው የሥራ ማቆም አድማ መጥራት ነው። እስካሁን ያልተሳኩ የሥራ ማቆም አድማዎችን ጠርቷል፤ በሌሎችም ባልተጋበዘባቸው ጥሪዎችም ድንኳን ሰብሮ በመግባት ደጋሾቹን ድግሱን አምክኖባቸዋል። ግን አላረፈም፤ አሁንም ሌላ ጥሪ አድርጓል፤ ይኼኛውን ግን እሱ የሌለበት ለማስመሰል ምሥጢራዊ ለማድረግ እየሞከረ ነው። ልደቱ አያሌው የሽግግር መንግሥት የዘርፉ ባለሙያ በመሆን የክብር ዶክትሬት እንዲሰጠው ተግቶ እየሠራ እንዳለው ጃዋርም በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ብቸኛው የዘርፉ ባለሙያ እየሆነ መጥቷል። አዲስ ሪፖርተር፤ ጃዋር [“ከመምህራን ማሕበር ጋር በታህሳስ ወር አመጽ ለማስነሳት ተስማምተናል” ማለቱን ማሕበሩ ነቀፈ፤] በሚል ርዕስ ያወጣው የዜና ዘገባ ይህንኑ የሚጠቁም ነው። … [Read more...] about በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ
የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ
* ይግባኝ ለማለት ወደ ፖለቲካው መመለስ የግድ ሆኖበታል በአሜሪካ የጥገኝነት ማመልከቻ ያስገባው አቶ በቀለ ገርባ የስደት ፈቃድ ማመልከቻው ውድቅ ተደረገ። በድጋሚ እንዲታይለት ይግባኝ መጠየቁም ታውቋል። ዳግም ወደ ፖለቲካ ተሳትፎ የተመለሰውም በዚህ ሳቢያ እንደሆነ ተመልክቷል። ከእስር ከተፈታ በኋላ ምስጋና ለማቅረብ ወደ አሜሪካ ከጃዋር ጋር ያመራው አቶ በቀለ በምስጋና ጉዞው ወቅት ከአቶ ጃዋር ሲራጅ መሐመድ ጋር ባለመግባባት መለያየቱና ይህ አለመግባባት አዲስ አበባ እያሉ የተጀመረ እንደነበር ጉዳዩን የሚያውቁ ማስታወቃቸው አይዘነጋም። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ በግል እና በፓርቲ ደረጃ ተሳታፊ የነበረው አቶ በቀለ ገርባ ከፓርቲው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) በመልቀቅ በአሜሪካ ጥገኝነት መጠየቁን ይፋ ያደረው ራሱ በቢቢሲ በኩል ነበር። ወደ አሜሪካ ከመጣ … [Read more...] about የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ



