አሁን ላይ ጃዋር የፖለቲካ ምሕዋሩን ስቶ የሚሄድበትን መንገድ የማያውቅ ሆኗል። በዚህ ኪሣራ ውስጥ ተስፋ ሰጪ ሆኖ ያገኘው የሥራ ማቆም አድማ መጥራት ነው። እስካሁን ያልተሳኩ የሥራ ማቆም አድማዎችን ጠርቷል፤ በሌሎችም ባልተጋበዘባቸው ጥሪዎችም ድንኳን ሰብሮ በመግባት ደጋሾቹን ድግሱን አምክኖባቸዋል። ግን አላረፈም፤ አሁንም ሌላ ጥሪ አድርጓል፤ ይኼኛውን ግን እሱ የሌለበት ለማስመሰል ምሥጢራዊ ለማድረግ እየሞከረ ነው። ልደቱ አያሌው የሽግግር መንግሥት የዘርፉ ባለሙያ በመሆን የክብር ዶክትሬት እንዲሰጠው ተግቶ እየሠራ እንዳለው ጃዋርም በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ብቸኛው የዘርፉ ባለሙያ እየሆነ መጥቷል። አዲስ ሪፖርተር፤ ጃዋር [“ከመምህራን ማሕበር ጋር በታህሳስ ወር አመጽ ለማስነሳት ተስማምተናል” ማለቱን ማሕበሩ ነቀፈ፤] በሚል ርዕስ ያወጣው የዜና ዘገባ ይህንኑ የሚጠቁም ነው። … [Read more...] about በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ
jawar massacre
“ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ)
ልደቱ አያሌው ከቴዎድሮስ ጸጋዬ ጋር ያስተባበረው “አየር አንቀጥቅጥ” ትዕይንት ቅዳሜ ቀን ተካሂዷል። ልደቱ በስተመጨረሻ እንዳለው ከታሰበው በላይ የተሳካው የአየር ትዕይንት 15 ሰዎች ተናግረዋል፤ ሕዝብ በሳተላይት እና በተገኘው መንገድ ሁሉ ሰምቷል ብሏል። አገዛዙ ፈርቶ ኢንተርኔት አፍኗል፤ ዳታ ታቅቧል፤ ዩትዩብ እንዳይሠራ ተደርጓል ብለው ልደቱም፣ ቴዎድሮስም እየደጋገሙ ሲናገሩ ተሰምተዋል። ይህ የአየር ላይ ትዕይንት “ስልቴዎች” ማለትም ስብሃት፣ ልደቱ፣ ቴዎድሮስ በልዩ ሁኔታ የቀመሩትና ትህነግን በመታደግ ለሻዕቢያ የተሠራ ልዩ የስልቴዎች ስልት ነው። ንግግር ያደረጉት ሰዎች ጥቂቶቹን ስንቃኝ፤ … የድግሱ መሪ ቴዎድሮስ መደረጉ በራሱ ብዙ የሚለው ነገር አለ። ቴዎድሮስ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ወገኖቼን (የትግራይ ተወላጆችን በተለይም ወያኔዎችን) የፈጀች ኢትዮጵያ ጥንቅር … [Read more...] about “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ)
ደም ጠጥቶ “አልጸጸትም” – የጃዋር አዲስ መጽሐፍ
ራሱን ከሚገባው በላይ መካብ የማይበቃው ጃዋር ሲራጅ መሐመድ የ21ኛው ክፍለ ዘመን አህመድ ግራኝ ነኝ፤ ተጽዕኖ ፈጣሪ ነኝ፤ “የአማራ ብሔርተኝነት ማነሳሳታችን ትልቁ ስኬታችን ነው”፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለሥልጣን ያበቃሁት እኔ ነኝ፤ የምርጫውን ቀመር (ካልኩሌሽን ሠርቼዋለሁ)፣ ቁርአን ይዤ ዐቢይን ጅማ ላይ እንዳይመረጥ አደርገዋለሁ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ሁለት መንግሥት ነው ያለው - የዐቢይ እና የቄሮ መንግሥት፣ እኔ ከታሰርሁ ኦሮሚያ ድብልቅልቁ ነው የሚወጣው፣ የፖለቲካ ሳይንቲስት ነኝ፣ ብዙ ዕውቀት አለኝ፤ ብዙ ችሎታ አለኝ፤ ወዘተ በማለት ያለማቋረጥ ከመትፋት አልፎ “ተከበብኩኝ፤ ልገደል ነው” የሚል የሃሰት መረጃ በማውጣት፤ ከህወሓት ጋር በመመሳጠር ለመተግበር የሞከረውን ዕቅድ እንደፈለገ የሚነዳውንና ማሰብ የተሳነውን የቄሮ ኃይል በመጠቀም ለማስፈጸም ባደረገው ሙከራ እጅግ በርካቶች በግፍ … [Read more...] about ደም ጠጥቶ “አልጸጸትም” – የጃዋር አዲስ መጽሐፍ
ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት
ጃዋር የኦነግን ባንዲራ መጠቀሙ ሕገወጥ ነው ሲል የዳውድ ኦነግ ከሰሰ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው አንዱ ኦነግ ጃዋር መሐመድ ገለቶማ በሚለው የአውሮጳና የአሜሪካ ስብሰባ ላይ የኦነግን ባንዲራ መጠቀሙን ኮነነ። ከእንግዲህ ወዲህ እንዳይጠቀም ትዕዛዝ አዘል ደብዳቤ ለኦፌኮ ጻፈ። በዳውድ ኢብሳ የሚመራውና በምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ተብሎ የተመዘገው ፓርቲ ባንዲራዬን ጃዋር መሐመድ በሕገወጥ መንገድ እየተጠቀመ ነው ሲል መረራ ጉዲና ለሚመራው ኦፌኮ ቅሬታውን አሰምቷል። ከሁለት ቀናት በፊት በተጻፈውና በዳውድ ኢብሳ በተፈረመው ደብዳቤ ጉዳዩ በሚለው ርዕስ ሥር በሕጋዊ መልኩ በምርጫ ቦርድ የተመዘገበውን የኦነግን ባንዲራ የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር ጃዋር መሐመድ በሕገወጥ መልኩ መጠቀሙን ስለማስቆም የሚል ነው። ደብዳቤው ሲያጠናቅቅም ከረር ያለ ማስጠንቀቂያ … [Read more...] about ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት
እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ?
ሕግ በረጅም ገመድ ያሰረው ጃዋር! ቅድሚያ “ኢትዮጵያዊ ፣ አባ ሜንጫ፣ አክቲቪስት፣ ተንታኝ፣ ፖለቲከኛ፣ አሁን ደግሞ “ሐጂ” ሆንኩ ያለው ጃዋር ማነው ነው? የሚለው ድብልቅልቅ ጉዳይ መመልከት ያሻል። ወይም የተለያዩ ማንነት ያለበት ጥያቄ መመለስ ግድ ነው። ጃዋር ወደ ፖለቲካ ሲመጣ በዳያስፖራ ያሉትን አገር ወዳዶች ለማማለል ፍጹም ኢትዮጵያዊ ሆኖ፣ በንግግሩ ሁሉን አስደምሞ ነበር ብቅ ያለው። ነገሮች መስመር ሲይዙለትና ደጋፊ ሲያገኝ እነዚህኑ ወደ ላይ የሰቀሉትን መሳደብና ኢትዮጵያን ማበሻቀጥ ጀመረ። በወቅቱ ተው ብለው አዛውንቱ የዳያስፖራ ምሁራን መከሩት። ወደላይ እየወጣ ስለነበር ይልቅ እኔን ብትሰሙ ይሻላል አላቸውና አልፏቸው ተስፈነጠረ። በቀጣይ ለኦሮሞን ትግል “አዲስ ትንፋሽ ነኝ” በማለት ራሱን መሪ አድርጎ ሾመ። የቀድሞ የኦሮሞ ታጋዮችን በተለይም ዕንቅፋት ይሆኑብኛል … [Read more...] about እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ?
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ክስ የተቋረጠባቸው ሶስት የክስ መዝገቦች ላይ መግለጫ ሰጠ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ክስ የተቋረጠባቸው ሶስት የክስ መዝገቦች የስነ-ስርዓት ሂደቶች ላይ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፡- ባለፈው ሶስት ዓመት ተኩል የፌደራል ፍርድ ቤቶች በሕገ መንግስቱ የተሰጣቸውን ሃላፊነት በተገቢው ደረጃ ለማከናወን በርካታ የለውጥ ተግባራትን ሲያከናውኑ ቆይተዋል፡፡ እነዚህ የለውጥ እርምጃዎች ትኩረት ያደረጉት በተቋማዊ እና በግለሰብ ዳኞች ደረጃ የፍርድ ቤቱን ነጻነት እና ገለልተኝነት ማስከበር ነው፡፡ በተጓዳኝም ለተጠያቂነት ተቋማዊ ስርዓቶች ተዘርግተዋል፡፡ በፍ/ቤቱ አመራሮች እና ዳኞች በኩል ሲደረግ የነበረው ጥረት ዋናው ግብ የሚሰጠው የዳኝነት ዘርፍ ቀልጣፋ፣ ተገማች እና ተደራሽ በማድረግ በፍርድ ቤቱ አገልግሎት ላይ የሕዝብ አመኔታ እንዲጨምር ነው፡፡ በዚህ ወር መጨረሻ በሚዘጋጀው “የፍርድ … [Read more...] about የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ክስ የተቋረጠባቸው ሶስት የክስ መዝገቦች ላይ መግለጫ ሰጠ
የኬሪያና የጃዋር ድብቁ ግንኙነትና አዲሱ የቤት ውስጥ እስር
የቀድሞ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የነበሩት ወ/ሮ ኬሪያ በዋስ መፈታታቸው ተሰምቷል። ፖሊስ ለችሎት እንዳስረዳው ወይዘሮዋ የተፈቱት ቀዳሚ ምርመራ እስኪሰማ ድረስ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀጽ 28 መሰረት ነው። ፋና ችሎቱን ጠቅሶ እንደዘገበው ወይዘሮ ኬሪያ ቀዳሚ ምርመራ እስከሚሰማ ድረስ የሚቆዩት በሰርቪስ ማረፊያ ነው። የህግ ማስከበሩ ሲጀመር ሌሎች ሲሸሹ መቀሌ ሆነው እጃቸውን የሰጡት የቀድሞ አፈ ጉባኤ፤ እጃቸውን ከሰጡ በኋላ ክስ ሳይመሰረትባቸው መቆየቱ ይታወሳል። ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም እንዴት ወደ መቀሌ ሄዱ? አፈጉባዔዋ ወደ መቀሌ የሄዱት ከአዲስ አበባ ተገፍተው መሆኑንን ጉዳይን በወጉ ሲከታተሉ የነበሩ ይናገራሉ። ኬሪያ ሃላፊነታቸውን በገዛ ፈቃዳቸው መልቀቃቸውን ከማስታወቃቸው በፊት ከአቶ ጃዋር ጋር ጥብቅ ግንኙነት እንዲመሠርቱ … [Read more...] about የኬሪያና የጃዋር ድብቁ ግንኙነትና አዲሱ የቤት ውስጥ እስር
ጃዋር “የአንድነት ኃይሎች ከዱኝ”
በቅርቡ ጃዋር መሐመድን ማረሚያ ቤት ድረስ ሄደው ከጎበኙ መካከል አንደኛው ከጃዋር አንደበት የሰሙትን ማመን እንዳቃታቸው ይገልጻሉ። ጃዋር ያለፈበትን መንገድ እያሰላ በጸጸት ውስጥ ያለ ይመስላል። በአጭር ጉብኝታቸው “የአንድነት ኃይሎች ከዱኝ” በማለት ቅዝዝ ብሎ የነገራቸው ጠያቂው እሱን ከተሰናበቱ በኋላ ነበር ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ሁኔታውን ያጫወቱት። ለተለያዩ ሚዲያዎችና በጃዋር ዙሪያ ለነበሩ እንቅስቃሴዎች እንግዳ ያልሆኑት እኚሁ ሰው ለጎልጉል ዘጋቢ መነሻ ሃሳብ ከሰጡ በኋላ ዘጋቢያችን በርካታ መረጃዎችን አሰባስቦ የሚከተለውን ሪፖርት አዘጋጅቷል። በሪፖርቱ አስቀድሞ የተሰባሰቡና ጊዜ ሲጠብቁ የነበሩ መረጃዎች ተካተዋል። ሪፖርቱ አንባቢያን የራሳቸውን ስሌት እንዲያሰሉና አቅም ያላቸው ይበልጥ ጉዳዩን እንዲያጠኑት የሚያነሳሳ ይሆናል። ጃዋርና “የአንድነት ኃይሎች” የት፣ … [Read more...] about ጃዋር “የአንድነት ኃይሎች ከዱኝ”
ተከሳሾቹ እነጃዋር “መንግሥት የለም” ብለው የመንግሥት አካል ነጻ እንዲያወጣቸው ተማጸኑ
በወንጀል ተከስሰው በእስር ቤት የሚገኙት ጃዋር ሲራጅ መሐመድ፣ በቀለ ገርባ ዳኮ፣ ሐምዛ አዳነ ታዬ እና ሸምሰዲን ጠሃ መሐመድ ከሰኞ መስከረም 25 ቀን ጀምሮ በሚመሠረተው የአደራ መንግሥት ለመሳተፍ ከእስር እንለቀቅ ብለው ተማጽንዖ አቅርበዋል። ተከሳሾቹ እነ ጃዋር ልቅም ባለ አማርኛ ከሽነው በጻፉት ደብዳቤ መንግሥታዊ አካል ለሆነው “የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች” ጥያቄያቸውን ሲያቀርቡ በግልባጭ “ለፌዴራል ዐቃቤ ሕግ” እና “ለፌዴራል ወንጀል ምርመራ” ጥያቄያቸውን ልከዋል። ተከሳሾቹ መቀሌ ከመሸገው የበረኻ ወንበዴዎች ቡድብ ህወሓት እና ከሌሎች ራሳቸውን ተቃዋሚ ፓርቲ ብለው ከሚጠሩ ጋር በመሆን ከመስከረም 25 ጀምሮ የአደራ መንግሥት እንመሠርታለን ብለው በተደጋጋሚ ሲናገሩና ሲሠሩ እንደነበር ይታወቃል። ተከሳሾቹ ያቀረቡት ደብዳቤ ከዚህ በታች ይገኛል፤ ጎልጉል የድረገጽ … [Read more...] about ተከሳሾቹ እነጃዋር “መንግሥት የለም” ብለው የመንግሥት አካል ነጻ እንዲያወጣቸው ተማጸኑ
የተረሳው የኢሬቻ ግፍና ከህወሓት ጋር የተዘለቀው ፍቅር እሽሩሩ
የዛሬ አራት ዓመት የኢሬቻን በዓል ለማክበር በወጣው ሕዝብ ላይ ያኔ ምኒልክ ቤተመንግሥት የነበረው አሁን መቀሌ ሆቴል የመሸገው ሕወሓት የተሰኘው የበረኻ ወንበዴዎች ቡድን ያደረሰው እጅግ ሰቅጣጭ ግፍ ፈጽሞ የሚዘነጋ አይደለም። ዓመት ባለፈ ቁጥር ይህንን የግፍ ናዳ ስናስብ ተመሳሳይ ዕልቂት በአገራችን እንዲፈጸም የሚሹ የዚህ ዓመቱን ኢሬቻ ክብረበዓል በሰላም መጠናቀቁን በፍጹም የፈለጉት አልነበረም። ሆኖም ፍጹም ሰላም በሰፈነበት መልኩ በዓሉ ተጠናቅቋ። ዓመታት አልፈው ያኔ የደረሰውን ግፍ ዘንግተው፤ ለኦሮሞ እንታገላለን የሚሉ ከህወሓት ጋር “ፍቅር እሹሩሩ” ማለታቸው ሕዝብን መናቅና መስደብ ብቻ ሳይሆን በቁሙ መግደልም ነው። ከሁሉ በላይ ለኦሮሞ ሕዝብ እታገላለሁ የሚለው በቀለ ገርባ ህወሓት ያደረሰበት ግፍና ስቅየት (ቶርቸር) ረስቶ መቀሌ በመሄድ ከህወሓት ሹሞች ጋር ስብሰባ … [Read more...] about የተረሳው የኢሬቻ ግፍና ከህወሓት ጋር የተዘለቀው ፍቅር እሽሩሩ










