• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት

June 8, 2022 12:59 pm by Editor 2 Comments

ጃዋር የኦነግን ባንዲራ መጠቀሙ ሕገወጥ ነው ሲል የዳውድ ኦነግ ከሰሰ

ዳውድ ኢብሳ የሚመራው አንዱ ኦነግ ጃዋር መሐመድ ገለቶማ በሚለው የአውሮጳና የአሜሪካ ስብሰባ ላይ የኦነግን ባንዲራ መጠቀሙን ኮነነ። ከእንግዲህ ወዲህ እንዳይጠቀም ትዕዛዝ አዘል ደብዳቤ ለኦፌኮ ጻፈ።

በዳውድ ኢብሳ የሚመራውና በምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ተብሎ የተመዘገው ፓርቲ ባንዲራዬን  ጃዋር መሐመድ በሕገወጥ መንገድ እየተጠቀመ ነው ሲል መረራ ጉዲና ለሚመራው ኦፌኮ ቅሬታውን አሰምቷል።

ከሁለት ቀናት በፊት በተጻፈውና በዳውድ ኢብሳ በተፈረመው ደብዳቤ ጉዳዩ በሚለው ርዕስ ሥር በሕጋዊ መልኩ በምርጫ ቦርድ የተመዘገበውን የኦነግን ባንዲራ የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር ጃዋር መሐመድ በሕገወጥ መልኩ መጠቀሙን ስለማስቆም የሚል ነው።

ደብዳቤው ሲያጠናቅቅም ከረር ያለ ማስጠንቀቂያ ይሰጣል፤ ይህ ደብዳቤ ከደረሳችሁ ቀን ጀምሮ አቶ ጃዋር የኦነግን ባንዲራ ከመጠቀም እንደምታስቆሙት፣ ጥያቄያችንን በተግባር ፈጽማችሁ እንደምታስታውቁን እናምናለን፤ ተስፋም እናደርጋለን ይላል።

የሸኔን አሸባሪ ተግባር ከውጭ በገንዘብም ሆነ በማስተባበርና በፕሮፓጋንዳ የሚረዱት እነ ጸጋዬ አራርሳ ከጃዋር ጋር ሆድና ጀርባ መሆናቸውን ተከትሎ ይህ ደብዳቤ መውጣቱ አነጋጋሪ ሆኗል።

የጃዋር የምስጋና ገለቶማ ጉዞ ገና ከመጀመሩ ይህ ዕንቅፋት መደንቀሩ ጉዞውንና ስብሰባዎቹን ወዴት አቅጣጫ እንደሚወስዳቸው በቀናት ውስጥ የሚታይ ነው። ሆኖም ግን ይህ የኦነግ ማስጠንቀቂያ ጃዋር በክፍሉ ውስጥ የሰቀለውን የሚጠቀልል መሆን አለመሆኑን ባይጠቁምም የዳውድ ኦነግ ግን ከእንግዲህ ባንዲራውን ማንም በምንም መልኩ እንዳይጠቀም ማስደረግ አለበት የሚሉ ኃይሎች ደብዳቤውን ደግፈው አስተያየት ሲሰጡ ተሰምተዋል።

ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ኦፌኮ ለደብዳቤው ምላሽ አልሰጠም።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: daud ibssa, jawar, jawar massacre, olf, olf shanee

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    June 8, 2022 02:03 pm at 2:03 pm

    ለካስ ጀዋር ሆሮሞ አይደለም በኦነጉ መሪ? ታዲያ ኦሮሞ ነፃ ኣውጭ ብሎ እራሱን የሰየመው የሆሮሞ ነፃ ኣውጪ መሪ በኦነግ ባንዲራ ሰበብ ጀዋርን መኮነኑ ኦነግ ለሆሮሞ ሕዝብ የቆመ ሳይሆን ለባንዲራው ነው ማለት ነው። ጀዋር የሆሮሞ ተወላጅና ኦሮሞ ከሆነ ባንዲራው የሆሮሞን ሕዝብ ይወክላል ካለ የኦፌኮ መሪ ባንዲራውን ቢይዘውና ስብሰባ ቢያደርግ ሆሮሞው ጀዋርን ስብሰባ ቢጠራው ዳውድ ኢብሳ የፈሩት ባንዲራውን ጀዋር ይቀይራል ብለው ነው ወይስ የኦነግ ባንዲራ የንጉስ ዳውድ ኢብሳ የንግስና ኣርማቸው ነውና ከኔ በቀር ማንም በዚህ ባንዲራ ስር አይሰብሰብ የተባለ ይመስላል። ለማንኛውም 90%የሆሮሞ ሕዝብ ኦነግ ምን እንደደረገለት ቢጠየቅ ኣለ እንዴ? ከማለት ይልቅ የተሰራ ነገር ለሕዝቡ ኣለመኖሩን የሆሮሞ ሕዝብ ያውቀዋል። የዳውድ ኢብሳ ፍራቻ ያለችን ሁሉ ይቀሙኛል ብሎ ፈርቶ ከሆነ ከድጡ ወደ ማጡ መግባታቸውና የመጨረሻው የውድቀት ደረጃ ላይ መሆናቸውን ያሳያል።

    Reply
  2. Somer Hamera says

    June 10, 2022 02:30 am at 2:30 am

    ባንድራ መያዝ ማለት በራሱ ትርጉሙ ምንድን ታውቃላችሁ? እውቅና ሰጪው ምርጫ ቦርድስ ምን እያደረገ እንዳለ ያውቃል ወይ? እኔን የሚያሳስበኝ ይሄ ነው? የትጥቅ ትግልን ባንዲራ ሕጋዊነት ማረጋገጥ የለየለት የሀገር ክህደት ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule