• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት

June 8, 2022 12:59 pm by Editor 2 Comments

ጃዋር የኦነግን ባንዲራ መጠቀሙ ሕገወጥ ነው ሲል የዳውድ ኦነግ ከሰሰ

ዳውድ ኢብሳ የሚመራው አንዱ ኦነግ ጃዋር መሐመድ ገለቶማ በሚለው የአውሮጳና የአሜሪካ ስብሰባ ላይ የኦነግን ባንዲራ መጠቀሙን ኮነነ። ከእንግዲህ ወዲህ እንዳይጠቀም ትዕዛዝ አዘል ደብዳቤ ለኦፌኮ ጻፈ።

በዳውድ ኢብሳ የሚመራውና በምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ተብሎ የተመዘገው ፓርቲ ባንዲራዬን  ጃዋር መሐመድ በሕገወጥ መንገድ እየተጠቀመ ነው ሲል መረራ ጉዲና ለሚመራው ኦፌኮ ቅሬታውን አሰምቷል።

ከሁለት ቀናት በፊት በተጻፈውና በዳውድ ኢብሳ በተፈረመው ደብዳቤ ጉዳዩ በሚለው ርዕስ ሥር በሕጋዊ መልኩ በምርጫ ቦርድ የተመዘገበውን የኦነግን ባንዲራ የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር ጃዋር መሐመድ በሕገወጥ መልኩ መጠቀሙን ስለማስቆም የሚል ነው።

ደብዳቤው ሲያጠናቅቅም ከረር ያለ ማስጠንቀቂያ ይሰጣል፤ ይህ ደብዳቤ ከደረሳችሁ ቀን ጀምሮ አቶ ጃዋር የኦነግን ባንዲራ ከመጠቀም እንደምታስቆሙት፣ ጥያቄያችንን በተግባር ፈጽማችሁ እንደምታስታውቁን እናምናለን፤ ተስፋም እናደርጋለን ይላል።

የሸኔን አሸባሪ ተግባር ከውጭ በገንዘብም ሆነ በማስተባበርና በፕሮፓጋንዳ የሚረዱት እነ ጸጋዬ አራርሳ ከጃዋር ጋር ሆድና ጀርባ መሆናቸውን ተከትሎ ይህ ደብዳቤ መውጣቱ አነጋጋሪ ሆኗል።

የጃዋር የምስጋና ገለቶማ ጉዞ ገና ከመጀመሩ ይህ ዕንቅፋት መደንቀሩ ጉዞውንና ስብሰባዎቹን ወዴት አቅጣጫ እንደሚወስዳቸው በቀናት ውስጥ የሚታይ ነው። ሆኖም ግን ይህ የኦነግ ማስጠንቀቂያ ጃዋር በክፍሉ ውስጥ የሰቀለውን የሚጠቀልል መሆን አለመሆኑን ባይጠቁምም የዳውድ ኦነግ ግን ከእንግዲህ ባንዲራውን ማንም በምንም መልኩ እንዳይጠቀም ማስደረግ አለበት የሚሉ ኃይሎች ደብዳቤውን ደግፈው አስተያየት ሲሰጡ ተሰምተዋል።

ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ኦፌኮ ለደብዳቤው ምላሽ አልሰጠም።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: daud ibssa, jawar, jawar massacre, olf, olf shanee

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    June 8, 2022 02:03 pm at 2:03 pm

    ለካስ ጀዋር ሆሮሞ አይደለም በኦነጉ መሪ? ታዲያ ኦሮሞ ነፃ ኣውጭ ብሎ እራሱን የሰየመው የሆሮሞ ነፃ ኣውጪ መሪ በኦነግ ባንዲራ ሰበብ ጀዋርን መኮነኑ ኦነግ ለሆሮሞ ሕዝብ የቆመ ሳይሆን ለባንዲራው ነው ማለት ነው። ጀዋር የሆሮሞ ተወላጅና ኦሮሞ ከሆነ ባንዲራው የሆሮሞን ሕዝብ ይወክላል ካለ የኦፌኮ መሪ ባንዲራውን ቢይዘውና ስብሰባ ቢያደርግ ሆሮሞው ጀዋርን ስብሰባ ቢጠራው ዳውድ ኢብሳ የፈሩት ባንዲራውን ጀዋር ይቀይራል ብለው ነው ወይስ የኦነግ ባንዲራ የንጉስ ዳውድ ኢብሳ የንግስና ኣርማቸው ነውና ከኔ በቀር ማንም በዚህ ባንዲራ ስር አይሰብሰብ የተባለ ይመስላል። ለማንኛውም 90%የሆሮሞ ሕዝብ ኦነግ ምን እንደደረገለት ቢጠየቅ ኣለ እንዴ? ከማለት ይልቅ የተሰራ ነገር ለሕዝቡ ኣለመኖሩን የሆሮሞ ሕዝብ ያውቀዋል። የዳውድ ኢብሳ ፍራቻ ያለችን ሁሉ ይቀሙኛል ብሎ ፈርቶ ከሆነ ከድጡ ወደ ማጡ መግባታቸውና የመጨረሻው የውድቀት ደረጃ ላይ መሆናቸውን ያሳያል።

    Reply
  2. Somer Hamera says

    June 10, 2022 02:30 am at 2:30 am

    ባንድራ መያዝ ማለት በራሱ ትርጉሙ ምንድን ታውቃላችሁ? እውቅና ሰጪው ምርጫ ቦርድስ ምን እያደረገ እንዳለ ያውቃል ወይ? እኔን የሚያሳስበኝ ይሄ ነው? የትጥቅ ትግልን ባንዲራ ሕጋዊነት ማረጋገጥ የለየለት የሀገር ክህደት ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule