• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት

June 8, 2022 12:59 pm by Editor 2 Comments

ጃዋር የኦነግን ባንዲራ መጠቀሙ ሕገወጥ ነው ሲል የዳውድ ኦነግ ከሰሰ

ዳውድ ኢብሳ የሚመራው አንዱ ኦነግ ጃዋር መሐመድ ገለቶማ በሚለው የአውሮጳና የአሜሪካ ስብሰባ ላይ የኦነግን ባንዲራ መጠቀሙን ኮነነ። ከእንግዲህ ወዲህ እንዳይጠቀም ትዕዛዝ አዘል ደብዳቤ ለኦፌኮ ጻፈ።

በዳውድ ኢብሳ የሚመራውና በምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ተብሎ የተመዘገው ፓርቲ ባንዲራዬን  ጃዋር መሐመድ በሕገወጥ መንገድ እየተጠቀመ ነው ሲል መረራ ጉዲና ለሚመራው ኦፌኮ ቅሬታውን አሰምቷል።

ከሁለት ቀናት በፊት በተጻፈውና በዳውድ ኢብሳ በተፈረመው ደብዳቤ ጉዳዩ በሚለው ርዕስ ሥር በሕጋዊ መልኩ በምርጫ ቦርድ የተመዘገበውን የኦነግን ባንዲራ የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር ጃዋር መሐመድ በሕገወጥ መልኩ መጠቀሙን ስለማስቆም የሚል ነው።

ደብዳቤው ሲያጠናቅቅም ከረር ያለ ማስጠንቀቂያ ይሰጣል፤ ይህ ደብዳቤ ከደረሳችሁ ቀን ጀምሮ አቶ ጃዋር የኦነግን ባንዲራ ከመጠቀም እንደምታስቆሙት፣ ጥያቄያችንን በተግባር ፈጽማችሁ እንደምታስታውቁን እናምናለን፤ ተስፋም እናደርጋለን ይላል።

የሸኔን አሸባሪ ተግባር ከውጭ በገንዘብም ሆነ በማስተባበርና በፕሮፓጋንዳ የሚረዱት እነ ጸጋዬ አራርሳ ከጃዋር ጋር ሆድና ጀርባ መሆናቸውን ተከትሎ ይህ ደብዳቤ መውጣቱ አነጋጋሪ ሆኗል።

የጃዋር የምስጋና ገለቶማ ጉዞ ገና ከመጀመሩ ይህ ዕንቅፋት መደንቀሩ ጉዞውንና ስብሰባዎቹን ወዴት አቅጣጫ እንደሚወስዳቸው በቀናት ውስጥ የሚታይ ነው። ሆኖም ግን ይህ የኦነግ ማስጠንቀቂያ ጃዋር በክፍሉ ውስጥ የሰቀለውን የሚጠቀልል መሆን አለመሆኑን ባይጠቁምም የዳውድ ኦነግ ግን ከእንግዲህ ባንዲራውን ማንም በምንም መልኩ እንዳይጠቀም ማስደረግ አለበት የሚሉ ኃይሎች ደብዳቤውን ደግፈው አስተያየት ሲሰጡ ተሰምተዋል።

ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ኦፌኮ ለደብዳቤው ምላሽ አልሰጠም።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: daud ibssa, jawar, jawar massacre, olf, olf shanee

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    June 8, 2022 02:03 pm at 2:03 pm

    ለካስ ጀዋር ሆሮሞ አይደለም በኦነጉ መሪ? ታዲያ ኦሮሞ ነፃ ኣውጭ ብሎ እራሱን የሰየመው የሆሮሞ ነፃ ኣውጪ መሪ በኦነግ ባንዲራ ሰበብ ጀዋርን መኮነኑ ኦነግ ለሆሮሞ ሕዝብ የቆመ ሳይሆን ለባንዲራው ነው ማለት ነው። ጀዋር የሆሮሞ ተወላጅና ኦሮሞ ከሆነ ባንዲራው የሆሮሞን ሕዝብ ይወክላል ካለ የኦፌኮ መሪ ባንዲራውን ቢይዘውና ስብሰባ ቢያደርግ ሆሮሞው ጀዋርን ስብሰባ ቢጠራው ዳውድ ኢብሳ የፈሩት ባንዲራውን ጀዋር ይቀይራል ብለው ነው ወይስ የኦነግ ባንዲራ የንጉስ ዳውድ ኢብሳ የንግስና ኣርማቸው ነውና ከኔ በቀር ማንም በዚህ ባንዲራ ስር አይሰብሰብ የተባለ ይመስላል። ለማንኛውም 90%የሆሮሞ ሕዝብ ኦነግ ምን እንደደረገለት ቢጠየቅ ኣለ እንዴ? ከማለት ይልቅ የተሰራ ነገር ለሕዝቡ ኣለመኖሩን የሆሮሞ ሕዝብ ያውቀዋል። የዳውድ ኢብሳ ፍራቻ ያለችን ሁሉ ይቀሙኛል ብሎ ፈርቶ ከሆነ ከድጡ ወደ ማጡ መግባታቸውና የመጨረሻው የውድቀት ደረጃ ላይ መሆናቸውን ያሳያል።

    Reply
  2. Somer Hamera says

    June 10, 2022 02:30 am at 2:30 am

    ባንድራ መያዝ ማለት በራሱ ትርጉሙ ምንድን ታውቃላችሁ? እውቅና ሰጪው ምርጫ ቦርድስ ምን እያደረገ እንዳለ ያውቃል ወይ? እኔን የሚያሳስበኝ ይሄ ነው? የትጥቅ ትግልን ባንዲራ ሕጋዊነት ማረጋገጥ የለየለት የሀገር ክህደት ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule