• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት

June 8, 2022 12:59 pm by Editor 2 Comments

ጃዋር የኦነግን ባንዲራ መጠቀሙ ሕገወጥ ነው ሲል የዳውድ ኦነግ ከሰሰ

ዳውድ ኢብሳ የሚመራው አንዱ ኦነግ ጃዋር መሐመድ ገለቶማ በሚለው የአውሮጳና የአሜሪካ ስብሰባ ላይ የኦነግን ባንዲራ መጠቀሙን ኮነነ። ከእንግዲህ ወዲህ እንዳይጠቀም ትዕዛዝ አዘል ደብዳቤ ለኦፌኮ ጻፈ።

በዳውድ ኢብሳ የሚመራውና በምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ተብሎ የተመዘገው ፓርቲ ባንዲራዬን  ጃዋር መሐመድ በሕገወጥ መንገድ እየተጠቀመ ነው ሲል መረራ ጉዲና ለሚመራው ኦፌኮ ቅሬታውን አሰምቷል።

ከሁለት ቀናት በፊት በተጻፈውና በዳውድ ኢብሳ በተፈረመው ደብዳቤ ጉዳዩ በሚለው ርዕስ ሥር በሕጋዊ መልኩ በምርጫ ቦርድ የተመዘገበውን የኦነግን ባንዲራ የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር ጃዋር መሐመድ በሕገወጥ መልኩ መጠቀሙን ስለማስቆም የሚል ነው።

ደብዳቤው ሲያጠናቅቅም ከረር ያለ ማስጠንቀቂያ ይሰጣል፤ ይህ ደብዳቤ ከደረሳችሁ ቀን ጀምሮ አቶ ጃዋር የኦነግን ባንዲራ ከመጠቀም እንደምታስቆሙት፣ ጥያቄያችንን በተግባር ፈጽማችሁ እንደምታስታውቁን እናምናለን፤ ተስፋም እናደርጋለን ይላል።

የሸኔን አሸባሪ ተግባር ከውጭ በገንዘብም ሆነ በማስተባበርና በፕሮፓጋንዳ የሚረዱት እነ ጸጋዬ አራርሳ ከጃዋር ጋር ሆድና ጀርባ መሆናቸውን ተከትሎ ይህ ደብዳቤ መውጣቱ አነጋጋሪ ሆኗል።

የጃዋር የምስጋና ገለቶማ ጉዞ ገና ከመጀመሩ ይህ ዕንቅፋት መደንቀሩ ጉዞውንና ስብሰባዎቹን ወዴት አቅጣጫ እንደሚወስዳቸው በቀናት ውስጥ የሚታይ ነው። ሆኖም ግን ይህ የኦነግ ማስጠንቀቂያ ጃዋር በክፍሉ ውስጥ የሰቀለውን የሚጠቀልል መሆን አለመሆኑን ባይጠቁምም የዳውድ ኦነግ ግን ከእንግዲህ ባንዲራውን ማንም በምንም መልኩ እንዳይጠቀም ማስደረግ አለበት የሚሉ ኃይሎች ደብዳቤውን ደግፈው አስተያየት ሲሰጡ ተሰምተዋል።

ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ኦፌኮ ለደብዳቤው ምላሽ አልሰጠም።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: daud ibssa, jawar, jawar massacre, olf, olf shanee

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    June 8, 2022 02:03 pm at 2:03 pm

    ለካስ ጀዋር ሆሮሞ አይደለም በኦነጉ መሪ? ታዲያ ኦሮሞ ነፃ ኣውጭ ብሎ እራሱን የሰየመው የሆሮሞ ነፃ ኣውጪ መሪ በኦነግ ባንዲራ ሰበብ ጀዋርን መኮነኑ ኦነግ ለሆሮሞ ሕዝብ የቆመ ሳይሆን ለባንዲራው ነው ማለት ነው። ጀዋር የሆሮሞ ተወላጅና ኦሮሞ ከሆነ ባንዲራው የሆሮሞን ሕዝብ ይወክላል ካለ የኦፌኮ መሪ ባንዲራውን ቢይዘውና ስብሰባ ቢያደርግ ሆሮሞው ጀዋርን ስብሰባ ቢጠራው ዳውድ ኢብሳ የፈሩት ባንዲራውን ጀዋር ይቀይራል ብለው ነው ወይስ የኦነግ ባንዲራ የንጉስ ዳውድ ኢብሳ የንግስና ኣርማቸው ነውና ከኔ በቀር ማንም በዚህ ባንዲራ ስር አይሰብሰብ የተባለ ይመስላል። ለማንኛውም 90%የሆሮሞ ሕዝብ ኦነግ ምን እንደደረገለት ቢጠየቅ ኣለ እንዴ? ከማለት ይልቅ የተሰራ ነገር ለሕዝቡ ኣለመኖሩን የሆሮሞ ሕዝብ ያውቀዋል። የዳውድ ኢብሳ ፍራቻ ያለችን ሁሉ ይቀሙኛል ብሎ ፈርቶ ከሆነ ከድጡ ወደ ማጡ መግባታቸውና የመጨረሻው የውድቀት ደረጃ ላይ መሆናቸውን ያሳያል።

    Reply
  2. Somer Hamera says

    June 10, 2022 02:30 am at 2:30 am

    ባንድራ መያዝ ማለት በራሱ ትርጉሙ ምንድን ታውቃላችሁ? እውቅና ሰጪው ምርጫ ቦርድስ ምን እያደረገ እንዳለ ያውቃል ወይ? እኔን የሚያሳስበኝ ይሄ ነው? የትጥቅ ትግልን ባንዲራ ሕጋዊነት ማረጋገጥ የለየለት የሀገር ክህደት ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule