ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲና የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) በሀገሪቱ ፍትህና ዴሞክራሲ እንዲሰፍን በጥምረት ለመስራት ያስችላል ያሉትን የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። ትብብሩ በቀጣይ በአገሪቱ እንዲፈጠርና እንዲጎለብት የሚፈለገው የአገራዊ በጎ ሀይሎች ጥምረት መሰረት እንዲሆን ያለመ መሆኑም ተገልጿል። በመጪው አገራዊ ምርጫ የመራጮች የጋራ ፍላጎትና ራዕይ ለማሳካት ፓርቲዎቹ በጋራ ለመስራት በማሰብ የተመሰረ የፖለቲካ ትብብር መሆኑንም ነው ፓርቲዎቹ የገለፁት። በአገሪቱም ሆነ በዜጎች ላይ የተጋረጡ ፈተናዎች እንዳሉ የገለጹት ፓርቲዎቹ፣ ይህንን ከመቼውም ጊዜ በላይ በትብብር ለመታገል በቁርጠኝነት እንደሚሰሩና ትብብሩ ከምርጫው በኋላም እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። (ኢቢሲ) የባልደራስ መሪና በአሁኑ ጊዜ በእሥር ላይ የሚገኙት አቶ እስክንድር ነጋ ከአማራ ድርጅቶች በተለይ … [Read more...] about ባልደራስና የአብን የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ
balderas
የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ወቅታዊ መግለጫ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ መስከረም 15/2013 ዓ.ም ባካሄደው ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባው፣ በከተማዋ የተጀመረውን ትምህርት ተሞክሮ እና አገልግሎቶች በአካታች ልማት (inclusive development) መርህ መሰረት አዲስ አበባ ዙሪያ ልዩ ዞን ወይም የኦሮሞ ብልጽግና “የፊንፊኔ ልዩ ዞን” በሚል መጠሪያ ባካተታቸው አካባቢዎች በሚገኙ 346 ትምህርት ቤቶች ውስጥ ለሚማሩ አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ(152,000) ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ፣ የተማሪ ደንብ ልብስ፣ጫማ እና የትምህርት ቤት ምገባ አገልግሎት ለማቅረብ የሚያስችል 669,210,780 (ስድስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ሚልዮን ሁለት መቶ አስር ሽህ ሰባት መቶ ሰማንያ ብር) በጀት በመመደብ ለእርዳታ አገልግሎቱ እንዲውል በልዩ ሁኔታ ውሳኔ አሳልፏል። ፓርቲያችን ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ በአዲስ አበባ ከተማ ዙሪያ … [Read more...] about የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ወቅታዊ መግለጫ
አዲስ አበባ በክልልነት እንድትደራጅ ባልደራስ የፓርቲዎችን ድጋፍ ጠየቀ
አዲስ አበባ በራሷ ግዛተ-መሬት ላይ የፌዴራል አድያምነት /ክልልነት/ መደራጀት በተመለከተ ባልደራስ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በትብብር ለመስራት ለፓርቲዎች ጥያቄ አቅርቧል። ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ትላንት ባወጣው ደብዳቤ እንደጠየቀው የአዲስ አበባን ህልውና ለማስጠበቅ በሚደረገው ታሪካዊ ጉዞ እንዲሳተፉ ለ10 ፓርቲዎች ጥሪውን አቅርቧል። ይህ ባልደራስ ለብልጽግና፤ ለመኢአድ፤ ለኢዜማ፤ ለአብን፤ ለመድረክ፤ ለአረና፤ ለትዴፓ፤ ለኦብነግ እና ሌሎች ፓርቲዎች ባቀረበው ጥሪ ፓርቲዎቹ መስከረም 20፤ ከ4 ሰዓት ጀምሮ ለሚደረገው ውይይት ፓርቲያቸውን የሚወክሉ 3 አመራሮችን እንዲልኩ ጥሪ አድርጓል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about አዲስ አበባ በክልልነት እንድትደራጅ ባልደራስ የፓርቲዎችን ድጋፍ ጠየቀ