• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ

July 1, 2022 09:23 am by Editor Leave a Comment

አዲስ አበባ ላይ ታላቅ ለውጥ ያመጣል ተብሎ በብዙዎች ተስፋ የተጣለበት ባልደራስ ባለፈው በተካሄደው ምርጫ የአዲስ አበባ ሕዝብ ድምጽ ነፍጎት አንድም ወንበር በአዲስ አበባ ምክር ቤትም ይሁን በተወካዮች ምክርቤት ሳያገኝ መቅረቱ ደጋፊዎቹን ተስፋ ያስቆረጠና አንገት ያስደፋ ክስተት ነበር።

ከሁሉ በላይ በአድናቂዎቹ “ታላቁ እስክንድር“ እየተባለ የሚጠራውና በትንሹ ለ10 ጊዜ ያህል በዘመነ ትህነግ እየተከሰሰ እስርቤት ሲንገላታ የኖረው እስክንድር ነጋ እስርቤት እያለ ምርጫውን እንዲወዳደር ቢደረግም በብልፅግና ተወዳዳሪ ተሸንፎ ሳይመረጥ መቅረቱ ብዙዎችን ያነጋገረ ጉዳይ ሆኖ አልፏል።

በኢትዮጵያ ሕግ በፓርቲነት ተመዝግቦ ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ አደርጋለሁ የሚለው ባልደራስ ከፓርቲ ፖለቲካ ወጣ ባለ መልኩ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጹ ላይ የጠላትን ሃሳብ የሚደግፍና የሚያበረታታ፣ የወገንን ሞራል፣ ቅስም የሚሰብርና የአገርን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ የሚጥል ዜና ትላንት ለጥፎ ነበር። የተለጠፈው ዜና ይህንን ይመስላል፤

በዚህ ልጥፍ ያዘኑና ለሕዝብና አገር ኅልውና ቀን ተሌት የሚለፉ ወገኖች ባልደራስን ተው፣ ከመንግሥት ጋር ቁርሾ ቢኖርህም እንዲህ የወረደ ተግባር አታድርግ ብለው ገስጸውታል።

ሌሎች ጎልጉል በግል ያነጋገራቸው ደጋፊዎቹ ደግሞ በድርጊቱ ማፈራቸውን የገለፁ ሲሆን ባልደራስ ከተነሳበት ዓላማ ወጥቶ የበረከት ስምዖንን ልጅ ኤርሚያስ ለገሠን ምክትል ኃላፊ አድርጎ የሾመ ጊዜ ራሳቸውን ከድርጅቱ ማግለላቸውን ጠቅሰው ባልደራስ የአገርን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ፣ ከተቻለም ሊከሰስ ይገባዋል ብለዋል::

ሲቀጥሉም ይህንን የመሰለ ተግባር የሚፈጽሙት፣ ከነእስክንድር ጋር ሆነው የሚሠሩትና ለግብፅ ሎሌ የሆኑት እነ ኤርሚያስ ናቸው፤ እስክንድርን በዚህ የክህደት ሥራ ውስጥ ማየታችን አንገታችንን አስደፍቶናል ብለዋል።

የባልደራስን ልጥፍ በተመለከተ ጌታቸው ሸፈራው ይህንን ብሏል፤

ባልደራሶች! በቀላሉ አትገመቱ! ዜናውን ለሚዲያ ተውት!

ባልደራስ መአት ነገር በፌስቡክ ገፁ ይለጥፋል። በአዲስ አበባ ጉዳይ ብዙ ነገር ይሰራል የተባለው ፓርቲ የሚያስገምቱትን የተራ አክቲቪስት መልዕክቶች ሲያጋራ ይውላል። ባልደራሶች ይህን ብታስተካክሉ ጥሩ ነው።

ለምሳሌ ከስር ያለውን ዜና መመልከት ይቻላል። የዜናው ምንጭ ከሱዳን ነው። የሱዳን መገናኛ ብዙሃን አገራቸው ውስጥ የተፈጠረውን ውጥረት ለማርገብ ጥረት እያደረጉ ነው። ለዚህም በቅርቡ ከባድ መሳርያዎችን እየተኮሰ ያለው የሱዳን ሰራዊት የኢትዮጵያን ሰራዊት ቦታ እንዳስለቀቀ አድርገው የሚዘግቡት ነው። እነሱ የሉአላዊነት ጉዳይ አንስተው አቅጣጫ ማስቀየር ፈልገዋል። ሮይተርስም ከእነሱ ነው የወሰደው።

ባልደራስ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ያለው። ለመታየት ሲል ሲያገኛቸው የከረመውን ፋኖዎች ሱዳን ድንበር ነው ያሉት። ለእነሱ ደውሎ ማረጋገጥ ይችል ነበር። ለእነሱም ባይደውል ከሱዳን ጎንደር ያለ መአት ምንጭ ይቀርበው ነበር። ማረጋገጥ ይችል ነበር።

ብስለት ቢታከልበት ደግሞ መሰል ዜና ትርጉም የለውም። የሱዳኖች ቅኝት ነው። ይህን ተርጉሞ መዘገብ ብስለት ማጣት ነው። ስራቸውም አይደለም።

ባልደራስ የሆነ ያልሆነውን እያጋራ በደጋፊዎቹም ጭምር ከሚገመት ሌላ ስራ ቢሰራ ይሻለዋል። ለምሳሌ በዚህ ዜና ጉዳይ መንግስትን ምን እየሆነ ነው ብሎ ቢጠይቅ፣ የአገር ሉአላዊነት የሚያስከብር መንግስት አይደለም ብሎ ቢተች ወዘተ የተገባ ነው። እንዲህ ያለ ዜና ግን ባልደራስን መዘባበቻ ያደርገዋል።

የግድ ዜና ካልሰራን ካላችሁ ደግሞ የወገን ዜና እንዲህ አይሰራም። ሱዳን ተጨማሪ የኢትዮጵያን መሬት ከያዘች ወረራ ነው የሚሆነው። ወረራ ነው የሚባለው።


ባልደራስ የሚባለውን ፓርቲ በአዲስአበባ ጉዳይ ብዙ ነገር ይሰራል የሚል ግምት ነበረኝ ይላል በቴሌግራም ገጹ ላይ ምልከታውን የጻፈው ታደለ ጥበቡ።  ተራ አክቲቪስት እንኳን ይጽፈዋል ተብሎ የማይመገት እንደዚህ ያለ የውሸት መረጃ ማሰራጨቱ ምናልባትም ድርጅቱ ራሱን ቆም ብሎ ማሰብ ያለበት ጊዜ ይመስለኛል። ፓርቲው ላይ የሚና መደበላለቅ እያየሁ ነው። እንዲያውም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባልደራስ እንደ ፓርቲ ሳይሆን “ባልደራስ ብዙሃን መገናኛ” እየመሰለኝ ነው። ዛሬ ደግሞ የዘገበውን መረጃ ለማረጋገጥ እዛው ድንበር አካባቢ ያሉ ፋኖዎችን ጠይቄ አንዱ “እዛው እኮ ነኝ” ብሎ በቁጣ ነበር የመለሰልኝ።

ባልደራስ የዜና ምንጭ አድርጎ የወሰደው ሮይተርስን ነው። የሮይተርስ የዜና ምንጭ ደግሞ ከሱዳን ነው። ከትናንት ጀምሮ በሱዳን የተነሳውን ተቃውሞ ለማርገብ ከሱዳን በኩል የሱዳን ሠራዊት፣ የኢትዮጵያን መከላከያ ሠራዊት ማስለቀቅ እንደቻለ ዘገባዎች ሊወጡ ይችላሉ። ደግሞም የሚጠበቅ ነው።ተደጋጋሚ የውሸት ዜናዎችም ተሰራጭተዋል።

ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ባልደራስ ድንበር አካባቢ ያሉ ፋኖዎችን እንኳን ጠይቆ እውነቱን ማረጋገጥ ሲገባው ከጠላት በኩል የወጣን መረጃ ተርጉሞ ማሰራጨቱ ከማስገረምም በላይ ሀላፊነት የጎደለው ዘገባ ነው።በነገራችን ላይ ሥራውም አይደለም። ምናልባት የተባለው መረጃ ትክክለኛ ቢሆን እንኳን ባልደራስ እንደ ፓርቲ መጠየቅ ያለበት የአገሪቱ ሉዓላዊነት የማስከበር ግዴታ ያለበት መንግሥት እርምጃ ባለመወሰዱ መጠየቅና መተቸት ነበር።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: balderas, bereket simon, Egypt, ermias legesse, eskinder, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule