• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ

July 1, 2022 09:23 am by Editor Leave a Comment

አዲስ አበባ ላይ ታላቅ ለውጥ ያመጣል ተብሎ በብዙዎች ተስፋ የተጣለበት ባልደራስ ባለፈው በተካሄደው ምርጫ የአዲስ አበባ ሕዝብ ድምጽ ነፍጎት አንድም ወንበር በአዲስ አበባ ምክር ቤትም ይሁን በተወካዮች ምክርቤት ሳያገኝ መቅረቱ ደጋፊዎቹን ተስፋ ያስቆረጠና አንገት ያስደፋ ክስተት ነበር።

ከሁሉ በላይ በአድናቂዎቹ “ታላቁ እስክንድር“ እየተባለ የሚጠራውና በትንሹ ለ10 ጊዜ ያህል በዘመነ ትህነግ እየተከሰሰ እስርቤት ሲንገላታ የኖረው እስክንድር ነጋ እስርቤት እያለ ምርጫውን እንዲወዳደር ቢደረግም በብልፅግና ተወዳዳሪ ተሸንፎ ሳይመረጥ መቅረቱ ብዙዎችን ያነጋገረ ጉዳይ ሆኖ አልፏል።

በኢትዮጵያ ሕግ በፓርቲነት ተመዝግቦ ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ አደርጋለሁ የሚለው ባልደራስ ከፓርቲ ፖለቲካ ወጣ ባለ መልኩ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጹ ላይ የጠላትን ሃሳብ የሚደግፍና የሚያበረታታ፣ የወገንን ሞራል፣ ቅስም የሚሰብርና የአገርን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ የሚጥል ዜና ትላንት ለጥፎ ነበር። የተለጠፈው ዜና ይህንን ይመስላል፤

በዚህ ልጥፍ ያዘኑና ለሕዝብና አገር ኅልውና ቀን ተሌት የሚለፉ ወገኖች ባልደራስን ተው፣ ከመንግሥት ጋር ቁርሾ ቢኖርህም እንዲህ የወረደ ተግባር አታድርግ ብለው ገስጸውታል።

ሌሎች ጎልጉል በግል ያነጋገራቸው ደጋፊዎቹ ደግሞ በድርጊቱ ማፈራቸውን የገለፁ ሲሆን ባልደራስ ከተነሳበት ዓላማ ወጥቶ የበረከት ስምዖንን ልጅ ኤርሚያስ ለገሠን ምክትል ኃላፊ አድርጎ የሾመ ጊዜ ራሳቸውን ከድርጅቱ ማግለላቸውን ጠቅሰው ባልደራስ የአገርን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ፣ ከተቻለም ሊከሰስ ይገባዋል ብለዋል::

ሲቀጥሉም ይህንን የመሰለ ተግባር የሚፈጽሙት፣ ከነእስክንድር ጋር ሆነው የሚሠሩትና ለግብፅ ሎሌ የሆኑት እነ ኤርሚያስ ናቸው፤ እስክንድርን በዚህ የክህደት ሥራ ውስጥ ማየታችን አንገታችንን አስደፍቶናል ብለዋል።

የባልደራስን ልጥፍ በተመለከተ ጌታቸው ሸፈራው ይህንን ብሏል፤

ባልደራሶች! በቀላሉ አትገመቱ! ዜናውን ለሚዲያ ተውት!

ባልደራስ መአት ነገር በፌስቡክ ገፁ ይለጥፋል። በአዲስ አበባ ጉዳይ ብዙ ነገር ይሰራል የተባለው ፓርቲ የሚያስገምቱትን የተራ አክቲቪስት መልዕክቶች ሲያጋራ ይውላል። ባልደራሶች ይህን ብታስተካክሉ ጥሩ ነው።

ለምሳሌ ከስር ያለውን ዜና መመልከት ይቻላል። የዜናው ምንጭ ከሱዳን ነው። የሱዳን መገናኛ ብዙሃን አገራቸው ውስጥ የተፈጠረውን ውጥረት ለማርገብ ጥረት እያደረጉ ነው። ለዚህም በቅርቡ ከባድ መሳርያዎችን እየተኮሰ ያለው የሱዳን ሰራዊት የኢትዮጵያን ሰራዊት ቦታ እንዳስለቀቀ አድርገው የሚዘግቡት ነው። እነሱ የሉአላዊነት ጉዳይ አንስተው አቅጣጫ ማስቀየር ፈልገዋል። ሮይተርስም ከእነሱ ነው የወሰደው።

ባልደራስ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ያለው። ለመታየት ሲል ሲያገኛቸው የከረመውን ፋኖዎች ሱዳን ድንበር ነው ያሉት። ለእነሱ ደውሎ ማረጋገጥ ይችል ነበር። ለእነሱም ባይደውል ከሱዳን ጎንደር ያለ መአት ምንጭ ይቀርበው ነበር። ማረጋገጥ ይችል ነበር።

ብስለት ቢታከልበት ደግሞ መሰል ዜና ትርጉም የለውም። የሱዳኖች ቅኝት ነው። ይህን ተርጉሞ መዘገብ ብስለት ማጣት ነው። ስራቸውም አይደለም።

ባልደራስ የሆነ ያልሆነውን እያጋራ በደጋፊዎቹም ጭምር ከሚገመት ሌላ ስራ ቢሰራ ይሻለዋል። ለምሳሌ በዚህ ዜና ጉዳይ መንግስትን ምን እየሆነ ነው ብሎ ቢጠይቅ፣ የአገር ሉአላዊነት የሚያስከብር መንግስት አይደለም ብሎ ቢተች ወዘተ የተገባ ነው። እንዲህ ያለ ዜና ግን ባልደራስን መዘባበቻ ያደርገዋል።

የግድ ዜና ካልሰራን ካላችሁ ደግሞ የወገን ዜና እንዲህ አይሰራም። ሱዳን ተጨማሪ የኢትዮጵያን መሬት ከያዘች ወረራ ነው የሚሆነው። ወረራ ነው የሚባለው።


ባልደራስ የሚባለውን ፓርቲ በአዲስአበባ ጉዳይ ብዙ ነገር ይሰራል የሚል ግምት ነበረኝ ይላል በቴሌግራም ገጹ ላይ ምልከታውን የጻፈው ታደለ ጥበቡ።  ተራ አክቲቪስት እንኳን ይጽፈዋል ተብሎ የማይመገት እንደዚህ ያለ የውሸት መረጃ ማሰራጨቱ ምናልባትም ድርጅቱ ራሱን ቆም ብሎ ማሰብ ያለበት ጊዜ ይመስለኛል። ፓርቲው ላይ የሚና መደበላለቅ እያየሁ ነው። እንዲያውም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባልደራስ እንደ ፓርቲ ሳይሆን “ባልደራስ ብዙሃን መገናኛ” እየመሰለኝ ነው። ዛሬ ደግሞ የዘገበውን መረጃ ለማረጋገጥ እዛው ድንበር አካባቢ ያሉ ፋኖዎችን ጠይቄ አንዱ “እዛው እኮ ነኝ” ብሎ በቁጣ ነበር የመለሰልኝ።

ባልደራስ የዜና ምንጭ አድርጎ የወሰደው ሮይተርስን ነው። የሮይተርስ የዜና ምንጭ ደግሞ ከሱዳን ነው። ከትናንት ጀምሮ በሱዳን የተነሳውን ተቃውሞ ለማርገብ ከሱዳን በኩል የሱዳን ሠራዊት፣ የኢትዮጵያን መከላከያ ሠራዊት ማስለቀቅ እንደቻለ ዘገባዎች ሊወጡ ይችላሉ። ደግሞም የሚጠበቅ ነው።ተደጋጋሚ የውሸት ዜናዎችም ተሰራጭተዋል።

ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ባልደራስ ድንበር አካባቢ ያሉ ፋኖዎችን እንኳን ጠይቆ እውነቱን ማረጋገጥ ሲገባው ከጠላት በኩል የወጣን መረጃ ተርጉሞ ማሰራጨቱ ከማስገረምም በላይ ሀላፊነት የጎደለው ዘገባ ነው።በነገራችን ላይ ሥራውም አይደለም። ምናልባት የተባለው መረጃ ትክክለኛ ቢሆን እንኳን ባልደራስ እንደ ፓርቲ መጠየቅ ያለበት የአገሪቱ ሉዓላዊነት የማስከበር ግዴታ ያለበት መንግሥት እርምጃ ባለመወሰዱ መጠየቅና መተቸት ነበር።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: balderas, bereket simon, Egypt, ermias legesse, eskinder, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule