
መነሻውን አማራ ክልል በማድረግ ወደ አዲስ አበባ ገብቶ ለሽብር ዓላማ ሊውል የነበረ ሕገ ወጥ ጠመንጃና ጥይቶች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።
መነሻውን ከአማራ ክልል ያደረገ ኮድ 3 አ.አ ታርጋ ቁጥር 05299 የሆነ ተሽከርካሪ ሕግ ወጥ 08 ክላሽ፣ 151 የክላሽ ጥይት፣ 17 የብሬን ጥይት እና 07 የክላሽ ካዝና ጭኖ በድብቅ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ለማሳለፍ ሲሞክር ለገጣፎ ኬላ ላይ ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደረገው ጠንካራ ፍተሻ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።
በተመሳሳይ መነሻውን አማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ ያደረገ ኮድ 3 ኢት የታርጋ ቁጥሩ 55426 የሆነ ተሽከርካሪ በእንቁላል ካርቶን ውስጥ 988 የክላሽ ጥይት ደብቆ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ለማሳለፍ ሲሞክር በሱልልታ ኬላ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደረገው ጠንካራ ፍተሻ በቁጥጥር ሥር መዋሉ ታውቋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና ሁሉ የተሰጠውን ግዳጅ በታማኝነትና በቁርጣኝነት በመወጣት የሀገርን ሰላምና ደኅንነት እያስከበረ የሕገ-ወጦች እኩይ ዓላማ ከግብ እንዳይደርስ የበኩሉን ድርሻ በጀግንነት እየተወጣ እንደሆነ ገልጾዋል።
በውጭ ሀገር የሚገኙና ለሻዕቢያ ደፋ ቀና እያሉ የሚሠሩ ባንዳዎች ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ሀገሪቱን መበጥበጥ አለብን በሚል መመሪያ መቀበላቸው በስፋት እየተሰማ ነው። በነአምን ዘለቀ አስተባባሪነት ልደቱ አያሌውና መሰሎቹ የሚሳተፉበት የትርምስ ኮሚቴ ተመሥርቶ አንድ ደረጃ ላይ ለመድረስ እየታተረ ነው። አካሄዱ እንዲህ ነው፤…
በሰላማዊ ትግል ሽፋን ከውጪ በሰልፍና በፕሮፓጋንዳ ለመሥራት፤ ከውስጥ ደግሞ ከፋኖም፣ ከሸኔም ጋር በመሆን ነውጥ መፍጠርና ለምርጫው ምቹና አስቻይ ሁኔታ አልተፈጠረም በሚል ፓርቲዎቹ ከምርጫ ራሳቸውን እንዲያገልሉ፤ በመጨረሻም ምርጫው ያለ ሕዝብ ውክልና የሚካሄድ ነው በሚል ቅቡልነትና ሕጋዊ እንዳይኖረው የማድረግ ዘመቻ ነው። ለዚህም እንዲያግዝ የሸኔው ተወካይ በስብሰባቸው መገኘቱን በጥምረት መሥራት መጀመራቸውን ጎልጉል ዘግቦ ነበር።
ሻዕቢያ የሰጠው መመሪያ ምርጫውን ሕገወጥ አድርጉት የሚል ነው። ይህንንም ዘመቻ ለማስፈጸም በዳያስፖራ ያሉት ሥፍር ቁጥር የሌላቸው ቡድኖች፣ ድርጅቶች፣ ስብስቦች፣ የቤተሰብ ዕድሮችና ዕቁቦች የሚመስሉ ሁሉ እንዲሳተፉ እነ ነዓምን ከጀርባ ሆነው እየተጉ ነው። በሰብዓዊ መብት ስም ድርጅት የሚመራው ያሬድ ኃይለማርያምም ስብሰባዎችን በመምራትና የነዓምንን ትዕዛዝ በማስፈጸም ላይ ይገኛል። ልደቱም ወደኛ ቀረብ በል ተብሎ ከሚኖርበት አትላንታ ወደ ዲሲ አካባቢ እንዲመጣ በነዓምን ተደርጓል።
በሀገር ውስጥ ግድያዎችን ማካሄድ፤ ንጹሐንን በግፍ መረሸን፤ የሃይማኖት የሚመስል ግጭት መፍጠር፤ ወዘተ የዕቅዱ አንዱና ዋነኛ አካል ነው። ለዚህም ሥራ በፋኖ ስም የሚንቀሳቀሰው አሸባሪ (ደረጃ ሦስት) ፋኖ እና አራጁ ሸኔ የገፊና ጎታች ነውጡን ለማፋፋም ተጋብዘዋል። ከአማራ ክልል ተነስቶ ወደ አዲስ አበባ የተላከው መሣሪያና ጥይት የዚሁ ዘመቻ አንዱ አካል ሆኖ ሊታይ የሚገባው ነው።
አንዳንድ ተጣምረናል፤ ምርጫ እንሳተፋለን ያሉ ፓርቲዎች አስቻይ ሁኔታዎች የሉም፤ በዚሁ ከቀጠለ ከምርጫው ለመውጣ እንገደዳለን ሲሉ ሰሞኑን የተደመጡት ከግብፅ በሻዕቢያ አድርጎ ከዳያስፖራ የተላከላቸውን መመሪያ በትዕዛዙ መሠረት ሲያስፈጽሙ ነው። ይህ ሁሉ ከዚህ በፊት ጎልጉል በስፋት እንደዘገበው የገፊና ጎታች ፕሮፓጋንዳ አካሄድ ስልት ነው።
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ














Leave a Reply