• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ”

March 27, 2026 09:14 am by Editor Leave a Comment

መነሻውን አማራ ክልል በማድረግ ወደ አዲስ አበባ ገብቶ ለሽብር ዓላማ ሊውል የነበረ ሕገ ወጥ ጠመንጃና ጥይቶች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።

መነሻውን ከአማራ ክልል ያደረገ ኮድ 3 አ.አ ታርጋ ቁጥር 05299 የሆነ ተሽከርካሪ ሕግ ወጥ 08 ክላሽ፣ 151 የክላሽ ጥይት፣ 17 የብሬን ጥይት እና 07 የክላሽ ካዝና ጭኖ በድብቅ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ለማሳለፍ ሲሞክር ለገጣፎ ኬላ ላይ ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደረገው ጠንካራ ፍተሻ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።

በተመሳሳይ መነሻውን አማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ ያደረገ ኮድ 3 ኢት የታርጋ ቁጥሩ 55426 የሆነ ተሽከርካሪ በእንቁላል ካርቶን ውስጥ 988 የክላሽ ጥይት ደብቆ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ለማሳለፍ ሲሞክር በሱልልታ ኬላ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደረገው ጠንካራ ፍተሻ በቁጥጥር ሥር መዋሉ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና ሁሉ የተሰጠውን ግዳጅ በታማኝነትና በቁርጣኝነት በመወጣት የሀገርን ሰላምና ደኅንነት እያስከበረ የሕገ-ወጦች እኩይ ዓላማ ከግብ እንዳይደርስ የበኩሉን ድርሻ በጀግንነት እየተወጣ እንደሆነ ገልጾዋል።

በውጭ ሀገር የሚገኙና ለሻዕቢያ ደፋ ቀና እያሉ የሚሠሩ ባንዳዎች ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ሀገሪቱን መበጥበጥ አለብን በሚል መመሪያ መቀበላቸው በስፋት እየተሰማ ነው። በነአምን ዘለቀ አስተባባሪነት ልደቱ አያሌውና መሰሎቹ የሚሳተፉበት የትርምስ ኮሚቴ ተመሥርቶ አንድ ደረጃ ላይ ለመድረስ እየታተረ ነው። አካሄዱ እንዲህ ነው፤…

በሰላማዊ ትግል ሽፋን ከውጪ በሰልፍና በፕሮፓጋንዳ ለመሥራት፤ ከውስጥ ደግሞ ከፋኖም፣ ከሸኔም ጋር በመሆን ነውጥ መፍጠርና ለምርጫው ምቹና አስቻይ ሁኔታ አልተፈጠረም በሚል ፓርቲዎቹ ከምርጫ ራሳቸውን እንዲያገልሉ፤ በመጨረሻም ምርጫው ያለ ሕዝብ ውክልና የሚካሄድ ነው በሚል ቅቡልነትና ሕጋዊ እንዳይኖረው የማድረግ ዘመቻ ነው። ለዚህም እንዲያግዝ የሸኔው ተወካይ በስብሰባቸው መገኘቱን በጥምረት መሥራት መጀመራቸውን ጎልጉል ዘግቦ ነበር።

ሻዕቢያ የሰጠው መመሪያ ምርጫውን ሕገወጥ አድርጉት የሚል ነው። ይህንንም ዘመቻ ለማስፈጸም በዳያስፖራ ያሉት ሥፍር ቁጥር የሌላቸው ቡድኖች፣ ድርጅቶች፣ ስብስቦች፣ የቤተሰብ ዕድሮችና ዕቁቦች የሚመስሉ ሁሉ እንዲሳተፉ እነ ነዓምን ከጀርባ ሆነው እየተጉ ነው። በሰብዓዊ መብት ስም ድርጅት የሚመራው ያሬድ ኃይለማርያምም ስብሰባዎችን በመምራትና የነዓምንን ትዕዛዝ በማስፈጸም ላይ ይገኛል። ልደቱም ወደኛ ቀረብ በል ተብሎ ከሚኖርበት አትላንታ ወደ ዲሲ አካባቢ እንዲመጣ በነዓምን ተደርጓል።

በሀገር ውስጥ ግድያዎችን ማካሄድ፤ ንጹሐንን በግፍ መረሸን፤ የሃይማኖት የሚመስል ግጭት መፍጠር፤ ወዘተ የዕቅዱ አንዱና ዋነኛ አካል ነው። ለዚህም ሥራ በፋኖ ስም የሚንቀሳቀሰው አሸባሪ (ደረጃ ሦስት) ፋኖ እና አራጁ ሸኔ የገፊና ጎታች ነውጡን ለማፋፋም ተጋብዘዋል። ከአማራ ክልል ተነስቶ ወደ አዲስ አበባ የተላከው መሣሪያና ጥይት የዚሁ ዘመቻ አንዱ አካል ሆኖ ሊታይ የሚገባው ነው።

አንዳንድ ተጣምረናል፤ ምርጫ እንሳተፋለን ያሉ ፓርቲዎች አስቻይ ሁኔታዎች የሉም፤ በዚሁ ከቀጠለ ከምርጫው ለመውጣ እንገደዳለን ሲሉ ሰሞኑን የተደመጡት ከግብፅ በሻዕቢያ አድርጎ ከዳያስፖራ የተላከላቸውን መመሪያ በትዕዛዙ መሠረት ሲያስፈጽሙ ነው። ይህ ሁሉ ከዚህ በፊት ጎልጉል በስፋት እንደዘገበው የገፊና ጎታች ፕሮፓጋንዳ አካሄድ ስልት ነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Literature, News Tagged With: ethiopian terrorists, lidetu ayalew, Neamin, operation dismantle tplf, Pull and Push Conspiracy

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule