ካለፉት አራት ወይም አምስት ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ የሚታየው የፖለቲካ መካረርና ጡዘት የሁለትዮሽ የተናበበ የገፊና ጎታች ሤራ (Pull and Push Conspiracy) ነው ለማለት የሚያስችሉ በርካታ ጠቋሚዎች አሉ። የዚህ ሤራ ዓላማ ሕዝብን መስዋዕት በማድረግ መስዋዕትነቱ በሚፈጥረው ቁጭትና ሐዘን ሕዝብን ስሜት ውስጥ በማስገባት ሥርዓት አፍርሶ ሥልጣን ባቋራጭ ለመጨበጥ ያለመ ነው። ለነገሩ ይህ ዓይነት የፖለቲካ አካሄድ አመጽ በተቀላቀለበት መልኩ ሁልጊዜ ባይታይም ሠለጠነ በሚባለው ዓለም የተለመደ አካሄድ ነው። ፓርቲዎች ጎራ ለይተው ይናቆራሉ፣ ይሰዳደባሉ፤ ሚዲያው ጉዳዩን የተካረረ ፖለቲካ ያደርገዋል፤ ደጋፊዎች በስሜት በመነዳት ብዙ ርቀው ይሄዳሉ፤ አታጋይ የተባሉት ፖለቲከኞች ግን አብረው ሲበሉ፣ ሲጠጡ፣ ሲሳሳቁ ይገኛሉ። “የሠለጠነ ፖለቲካ” በማለት ይህንን ድራማ ሚዲያው ሌላ ቅኝት … [Read more...] about በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት
Ethiopia
የህወሓት የሽብር ሰነድ ሲገለጥ…
አሸባሪው ህወሓት ሀገርን የሚያፈርስበትና የኢትዮጵያን ህዝብ በመበቀል ለመከራ የሚዳርግበት አዲስ ሰነድ አዘጋጅቶ ወደ ተግባር ገብቷል። አሁን እያካሄደ ያለው ውጊያም የዚሁ አካል ነው። ፅሁፉ ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ በማሳጠርና መታየት ያለባቸው ነጥቦች ብቻ ቀርቧል። ከሰነዱ የተወሰዱ ዋና ወና ሃሳቦች: ስለ ሰላም አማራጮች ያላቸው አቋም:- • የሰላም አማራጭ በሚል ስትራቴጂው፣ በአንድ በኩል ጊዜ ወስዶ ለአጠቃላይ ዘመቻ ለመዘጋጀት በሌላ በኩል ደግሞ ህወሓት ሰላም ፈላጊ አይደለም ብሎ ለዓለም ማህበረሰብ ጥላቻ ለማሰተጋባት እንዲያግዘው በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የጀመረው አካሄድ በፍፁም የማያዋጣና የትግራይ ህዝብን ጥቅም የማያስከብር መሆኑን ያስቀምጣል። • የውስጥ ትግላችን በማገዝ የሚንቀሳቀሱ እንደ ኦነግ የመሳሰሉ አጋሮቻችን እንዲሁም በተለያዬ የዓለም … [Read more...] about የህወሓት የሽብር ሰነድ ሲገለጥ…
“ውረሩ፣ ያገኛችሁትን ግደሉ እየተባልን ነው የምንመጣው” እጃቸውን የሠጡ የትህነግ ታጣቂዎች
በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን ላይ የተነሳው የሽብር ቡድን በሕዝብ ላይ አያሌ በደሎችን አድርሷል። ከእኩይ ቡድን አቅራቢያ የሚገኙ የአማራና የአፋር ክልል ነዋሪዎች ደግሞ የሽብር ቡድኑ ግፍና ወረራ ገፈት ቀማሾች ናቸው። ለሦስተኛ ጊዜ ጦርነት ያነሳው የትህነግ የሽብር ቡድን የትግራይ ተወላጆችን ከሕፃናት እስከ አዛውንት ድረስ እየመለመለ ለጦርነት እየላካቸው ነው። የሽብር ቡድኑ በአማራና አፋር ክልል በወረራ በያዛቸው አካባቢዎች ንፁሐንን በጅምላ ረሽኗል፣ ሃብትና ንብፈታቸውን ዘረፏል አውድሟል። የሽብር ቡድኑ የሚልካቸው ታጣቂዎች ሀገሩን እየተከላከለ በሚገኘው ጥምር ጦር እየተመቱ ብዙዎች ይረግፋሉ። እድል የቀናቸው እጃቸውን ሰጥተው ሕይወታቸውን ያተርፋሉ። የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች በወልቃት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ለሚገኘው ጀግናው የሀገር መከላከያ በርካቶች እጃቸውን እየሰጡ … [Read more...] about “ውረሩ፣ ያገኛችሁትን ግደሉ እየተባልን ነው የምንመጣው” እጃቸውን የሠጡ የትህነግ ታጣቂዎች
ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ
አርሶ አደር ዳንኤል ሾጦጦ ይባላሉ፤ በጌዴኦ ዞን በዲላ ዙሪያ ወረዳ የሺጋዶ ቀበሌ ነዋሪ ናቸዉ። ባላቸው አነስተኛ መሬት ላይ ቋሚና ጊዜያዊ ሰብሎችን በማምረት ይተዳደራሉ።አርሶ አደሩ ማሳቸውን አቋርጣ የሚታልፍ አነስተኛ ወንዝ በመጥለፍ ባዘጋጁዋቸዉ ገንዳዎች ዓሣ የማልማት ሀሳብ ይዘዉ ወደ ተግባር ገቡ፤ በእነዚህ የዉኃ ገንዳዎች 6 ሺህ የዓሳ ጫጩቶችን ወደማርባት ተሸጋገሩ።በአሁኑ ወቅት የሚያረቡትን የዓሣ ጫጬት ብዛት እስከ 80 ሺህ ማድረስ ችለዋል። የገንዳዎቹንም ቁጥር ወደ 3 አሳድገዋል። (ቲክቫህ) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ
በእንግሊዝ ሮያል ሚሊታሪ አካዳሚ የወርቅ ጎራዴ ተሸላሚው ም/መቶ አለቃ ለገሰ
ምክትል መቶ አለቃ ለገሰ መብራት ፥ ለአንድ ዓመት ከስምንት ወር ትምህርታቸውን በመከታተል አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል፡፡ በሮያል ሚሊታሪ አካዳሚ ከ38 የአፍሪካ እና የአውሮፓ ሃገራት የተውጣጡ 250 ተማሪዎች መካከል የአንደኝነት ደረጃን በመያዝ የጥንታዊያን የምስራቅ አገሮች የወርቅ ጎራዴ እና ሜዳሊያ ተሸላሚ ለመሆን መብቃታቸውን እና ሜዲያሊያውንም መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡ ለሽልማቱ በመስፈርትነት የተቀመጡትን በአካዳሚክ፣ በሚሊታሪ እና የተግባር ትምህርት ካሉት ተማሪዎች ውስጥ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ለሽልማቱ መብቃታቸውን ነው ያስረዱት፡፡ ምክትል መቶ አለቃ ለገሰ መብራት ከኤታማዦር ሹሙ በተጨማሪ ከከፍተኛ ጄነራሎች ጋር ቆይታ ማድረጋቸው ተገልጿል፡፡ ጄነራሎችም በውጤቱ … [Read more...] about በእንግሊዝ ሮያል ሚሊታሪ አካዳሚ የወርቅ ጎራዴ ተሸላሚው ም/መቶ አለቃ ለገሰ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ክስ የተቋረጠባቸው ሶስት የክስ መዝገቦች ላይ መግለጫ ሰጠ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ክስ የተቋረጠባቸው ሶስት የክስ መዝገቦች የስነ-ስርዓት ሂደቶች ላይ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፡- ባለፈው ሶስት ዓመት ተኩል የፌደራል ፍርድ ቤቶች በሕገ መንግስቱ የተሰጣቸውን ሃላፊነት በተገቢው ደረጃ ለማከናወን በርካታ የለውጥ ተግባራትን ሲያከናውኑ ቆይተዋል፡፡ እነዚህ የለውጥ እርምጃዎች ትኩረት ያደረጉት በተቋማዊ እና በግለሰብ ዳኞች ደረጃ የፍርድ ቤቱን ነጻነት እና ገለልተኝነት ማስከበር ነው፡፡ በተጓዳኝም ለተጠያቂነት ተቋማዊ ስርዓቶች ተዘርግተዋል፡፡ በፍ/ቤቱ አመራሮች እና ዳኞች በኩል ሲደረግ የነበረው ጥረት ዋናው ግብ የሚሰጠው የዳኝነት ዘርፍ ቀልጣፋ፣ ተገማች እና ተደራሽ በማድረግ በፍርድ ቤቱ አገልግሎት ላይ የሕዝብ አመኔታ እንዲጨምር ነው፡፡ በዚህ ወር መጨረሻ በሚዘጋጀው “የፍርድ … [Read more...] about የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ክስ የተቋረጠባቸው ሶስት የክስ መዝገቦች ላይ መግለጫ ሰጠ
5 ሚሊዮን “የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት” ዘመቻ ተጀመረ
ኢትዮጵያ የያዘችውን እውነታ ለዓለም የማስረዳትና የአሸባሪውን ህወሃት የጥፋት ድርጊት ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ማሳየትን አላማ ያደረገው "የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት" ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል። ዘመቻው ይፋ ሲደረግ ሚኒስትሮች፣ የተለያዩ ታዋቂ ግለሰቦችና በርካታ ወጣቶች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል። "የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት" ዘመቻ ከዛሬ ጀምሮ አስከ መስከረም 15 ቀን 2014 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑ ታውቋል። “በኢትዮጵያ ላይ በተሳሳተ መልኩ የሚነዛው አሉባልታ ከእውነት የራቀ መሆኑን ለዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ለማሳየት በዘመቻው ይሰራል” ተብሏል። በዚሁ ንቅናቄ ኢትዮጵያ የያዘችውን እውነታ ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እንዲደርስ ይሰራል ተብሏል። በዚህ ዘመቻ ከ5 ሚሊዮን በላይ ወጣቶች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል። በሌላ በኩል … [Read more...] about 5 ሚሊዮን “የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት” ዘመቻ ተጀመረ
“የማንነታችን መገለጫዎች ማሰሪያው ኢትዮጵያዊነት ነው”- ዶ/ር ዲማ ነገዎ
ዛሬ (ሰኞ) በሸራተን አዲስ እየተከበረ በሚገኘው የኢትዮጵያዊነት ቀን የመወያያ ጽሑፍ ያቀረቡት ዶ/ር ዲማ ነገዎ የማንነታችን መገለጫዎች ማሰሪያው ኢትዮጵያዊነት ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ የህዝቦች የተለያዩ የማንነት መገለጫዎች መኖራቸውን የገለጹት ዶ/ር ዲማ እነዚህን ሁሉ አጠቃሎ አንድ ዓይነት አገራዊ ማንነት የሚሰጠን ኢትዮጵያዊነታችን ማንነት ነው ብለዋል፡፡ አሁን ያለው ኢትዮጵያዊ ማንነት አንድነትን በብዝሀነት አጣምሮ ሁሉንም ህዝብ በእኩልነት የሚያስተናግድ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ አገሪቷ አሁን ያለችበትን ውስብስብ ፈተና እንድትሻር ለማስቻል በህግ ማስከበር እና በሌሎች በሚወሰዱ እርምጃዎች የአገርን አንድነት እና ኢትዮጵያዊነትን እንዳይሸረሽር ጥንቃቄ መደረግ አለበት ብለዋል፡፡ (ኢብኮ) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ማስታወሻ፤ የኦሮሞ መብት አቀንቃኝ ነን ለሚሉትና … [Read more...] about “የማንነታችን መገለጫዎች ማሰሪያው ኢትዮጵያዊነት ነው”- ዶ/ር ዲማ ነገዎ
የዓለም ባንክ የ907 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለኢትዮጵያ አደረገ
የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ለሚተገበሩት ሶስት ፕሮጀክትች የሚውል የ907 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ዛሬ ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር ስምምነት ተፈራርሟል። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እና ዓለም ባንክ ግሩፕ ምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ሚ/ር ዲዮን ነው የተፈራረሙት። የገንዘብ ድጋፉ በኢትዮጵያ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ፤ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎትን አሰጣጥንና ተደራሽነትን ለማሳደግ እንዲሁም የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ የሚውል ነው ተብሏል። የመጀመሪያው የ200 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት በኢትዮጵያ ውስጥ በአነስተኛ እና ጥቃቅን ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የሚውል ነው። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ክፉኛ የተጎዱ እንተርፕራይይች አዋጭ በሆነ መንግድ እንዲቀጥሉና በንግድ ውስጥ እንዲቆዩ ለማድረግ … [Read more...] about የዓለም ባንክ የ907 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለኢትዮጵያ አደረገ
ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው
የኢትጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖኖሊጂ ኢንስቲትዩት ድሮኖችን ለማምረት ከኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንዲሁም ከሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመሆን ወደ ስራ ለመግባት ስምምነት ላይ መደረሱም ተነግሯል፡፡የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር የሽሩን አለማየሁ ከኢትዮ ኤፍ ኤም ጋር በነበራቸው ቆይታ አገሪቱ በራሷ አቅም ድሮኖችን ማምረት የሚያስችል ስራዎች ተጀምረዋል ነዉ ያሉት፡፡ (ምንጭ Tikvah) … [Read more...] about ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው