የዛሬ አምስት ዓመት ግድም ነው። የሚያምሩ ሁለት ሸበቶ እናቶችን ጨምሮ ተገልጋዮች ይበላሉ። ይጠጣሉ። ያነሳቸውን ይጠይቃሉ። የወቅቱ የኢሳት ባልደረቦችም በአንድ ኮርነር ክብ ሰርተው የሚበላወንም የሚጠጣውንም በዓይነት ሤራ እያዋለዱ ይጠዘጥዛሉ። ቨርጂኒያ ዳማ ሆቴል!! በድንገት ሁለቱ ሸበቶ ሴቶች ይነሱና እንደ ብራቅ ይጮሃሉ። ክብ ሰርተው የሚመገቡትን የኢሳት የማታ ማታ ኮማንዶዎች እያመለከቱ እሳት ጎርሰው “አፈር ብሉ፣ እምዬ ማሪያም አፈር ታብላችሁ፤ ሕዝብ እያጫረሳችሁ እናንተ እዚህ ሥጋ ትቆርጣላችሁ። ደም ብሉ …. ” እናቶቹ ስሜታቸውን መቆጣጠር አቅቷቸው “ያዙኝ ልቀቁኝ” አሉ። ወርውረው ለመማታት ገላጋዮችን ታገሉ። ተለምነው። ተገዝተው …. የገባቸው እናቶች። እንደ እኔ ያልደነዘዙ። “ሦስትን ወደ አራት” አስገራሚ ትርክት፣ አስገራሚ ሤራ ነው። ሤራው በርካቶችን የሰለበ … [Read more...] about ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት”
Dr Ambachew
ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል
የገፊና ጎታች ሴራ፣ የአማራ ሕዝብ መከራ ክልሉ የፖለቲካ ቧልት እየበላው ነው የአማራ ክልል የራሱን መሪዎች በመብላት ሤራ ከሁሉም የአገሪቱ ክልሎች በተለየ መታወቂያው ነው። የአማራ ክልል አሁን ላይ በፖለቲካ አመለካከት ሳቢያ ሰዎች የሚገደሉበት ክልል ሆኗል። አማራ ክልል ላይ በተደጋጋሚ የሚስተዋለው መጠፋፋትና ይህንኑ በማወደስ የሚያራግቡት ክልሉን "ለፖለቲካ ቧልት" ዳርገውታል እየተባለ ነው። "የገፊና ጎታች ፖለቲካ መሃል ሜዳ" የሚባለው የአማራ ክልል መሪዎቹ እንዲገደሉ የሚያቅዱ፣ ግድያውን የሚያቀነባብሩ፣ ግድያውን የሚፈጽሙ፣ ግድያው ሲፈጸም ወደ ሌላ በመጠቆም ሕዝብ እንዲቆጣ የሚያደርጉ ተዋንያኖች የሚተራመሱበት እንደሆነ በርካታ መረጃ በማንሳት የሚናገሩ ጥቂት አይደሉም። ከሁሉም በላይ በፍረጃና ማጠልሸት ላይ አተኩረው የሚሠሩት ሚዲያዎች "የገፊና ጎታች" ፖለቲካው ፊት … [Read more...] about ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል


