“ህወሓት ወደ አገር በሚገቡ መንገደኞች ገንዘብ ለማስገባት እየጣረ ነው” በሚል ርዕስ አንድ ዘገባ ካወጣን በኋላ ዛጎል “በአሜሪካ “ገንዘብ – ውሰዱልን” የቅርብ ወዳጆችን ግንኙነት በጠሰ” በሚል ርዕስ የሚከተለውን ዘገባ ለንባብ አብቅቷል። አሁንም የኢትዮጵያን መንግሥት ለማሳሰብ የምንፈልገው ይህንን የተቀናጀ ሥራ እያከናወኑ ያሉት ህወሓቶች መሆናቸውን ነው። ከዚህ ሌላ በተለያዩ የኢትዮጵያ ድንበር ኬላዎች ከጎረቤት አገር ወደ ኢትዮጵያ ገንዘብ ይገባል ከሚለው እሳቤ በተጨማሪ በቦሌ በኩልም እየገባ እንደሆነ ሊታወቅ ይገባዋል። ስለዚህ በቦሌ ዓለምአቀፍ አውሮጵላን ማረፊያ በተጓዦች በተለይም በበረራ ሠራተኞች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ሊደረግ ይገባል እንላለን። በአሜሪካ “ገንዘብ – ውሰዱልን” የቅርብ ወዳጆችን ግንኙነት በጠሰ “እንዴት ብትንቁን ነው” ሲል ባለቤት ቁጣ የተሞላ ምላሽ … [Read more...] about በቦሌ በኩል አሮጌው ብር እየገባ ነው፤ በበረራ ሠራተኞችና መንገደኞች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ ተጠየቀ
Ethiopia
ህወሓት ወደ አገር በሚገቡ መንገደኞች ገንዘብ ለማስገባት እየጣረ ነው
በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገውን የገንዘብ ኖት ለውጥ ተከትሎ መደናገጥ ውስጥ የሚገኘው ህወሓት ከውጭ አገራት ወደ ኢትዮጵያ የብር ኖቶችን እያስገባ እንደሆነ ተጠቆመ። ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ፤ ቦሌ ዓለምአቀፍ አውሮጵላን ማረፊያ ደግሞ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ ተጠየቀ። ጭንቅላቱ የደረቀውና ኪሱ ወደ በመድረቅ ጉዞ ላይ ያለው ህወሓት የገንዘብ ለውጡን ተከትሎ ከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ እንደገባ ጎልጉል ያጠናቀረውን መረጃ ለንባብ አብቅቶ ነበር። ከሁለት ዓመት ተኩል በፊት ከምኒልክ ቤተመንግሥት የተባረረው ህወሓት መቀሌ በየሆቴሉ መሽጎ በኢትዮጵያ የሽብር ተግባራትን ሲፈጽም ቆይቷል። ይህንንም ተግባሩን ለማስፈጸም እንዲረዳው በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር፤ ሐሰተኛ የብር ኖቶች በማተም ተግባር፤ በኮንትሮባንድ ንግድ፤ ገንዘብ ከአገር በማሸሽ፤ ወዘተ ሕገወጥ ተግባራት … [Read more...] about ህወሓት ወደ አገር በሚገቡ መንገደኞች ገንዘብ ለማስገባት እየጣረ ነው
አማርኛ ቋንቋ በቻይና መሰጠት ተጀመረ፤ የመጀመሪያው የሕግ መዝገበቃላት በአማርኛ ሊዘጋጅ ነው
ቻይና አማርኛ ቋንቋን በመጀመሪያ ዲግሪ ልታስተምር እንደሆነ በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ። ትምህርቱ መሰጠት የጀመረበትን ይፋዊ የመክፈቻ ሥነ ስርዓት የተመለከተ መረጃን በማኅበራዊ ገጹ ያጋራው ኤምባሲው ትምህርቱ በቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ (BFSU) መሰጠት እንደጀመረ ገልጿል። በሥነ ስርዓቱ የኤምባሲው የሚኒስትር አማካሪ አቶ ሳሙዔል ፍጹም ብርሃን እና የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ጂያን ውንጂን ንግግር አድርገዋል። (አል አይን) ከዚሁ ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የሕግ መዝገበ ቃላት ለማዘጋጀት የሚያስችል ሥምምነት መፈረሙን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። ሥምምነቱን የተፈራረሙት የፌዴራል የፍትሕና የሕግ ምርምርና ሥልጠና ኢንስቲትዩት፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ጀስቲስ ፎር ኦል የተባለው ግብረ ሠናይ ድርጅት ናቸው።መዝገበ … [Read more...] about አማርኛ ቋንቋ በቻይና መሰጠት ተጀመረ፤ የመጀመሪያው የሕግ መዝገበቃላት በአማርኛ ሊዘጋጅ ነው
ሕገወጥ መሣሪያዎችና ተሠርቀው የተከማቹ የመኪና ዕቃዎች ተያዙ
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረጃርሶ ወረዳ 53 ሕገወጥ ሽጉጦችና 3860 የሽጉጥ ጥይቶች ባለፈው እሁድ በቁጥጥር ሥር ውለዋል። ሕገወጥ የጦር መሳሪያዎቹ የተያዙት ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ በመጓጓዝ ላይ እያሉ በጎሃ ቀሬ ከተማ ኬላ ላይ መያዛቸውን የወረጃርሶ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ኮማንደር አበባየሁ ገረመው በተለይ ለኢቲቪ ተናግረዋል፡፡ ሕገወጥ የጦር መሳሪያዎቹን ሲያጓጉዙ የነበሩት ግለሰቦችና ሹፌር ያመለጡ በመሆናቸው እነሱን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ክትትል እየተደረገ መሆኑን ኮማንደር አበባየሁ ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል በአዲስ አበባ በልደታ ክ/ከተማ ተሠርቀው የተከማቹ በርካታ የመኪና እቃዎችን ከ3 ተጠርጣሪዎች ጋር መያዙን የአብነት አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ገለፀ፡፡ የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የመኪና ዕቃ ስርቆት ወንጀልን ለመከላከል የክትትልና … [Read more...] about ሕገወጥ መሣሪያዎችና ተሠርቀው የተከማቹ የመኪና ዕቃዎች ተያዙ
“የሤራ ፅንሰ ሃሳብ በኢትዮጵያ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ አሁን ገዝፎ ወጥቷል” ዶ/ር ደመቀ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህር እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውጭ ግንኙነት ትብብር እና ኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ዳይሬክተር ዶክተር ደመቀ አጭሶ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳመለከቱት፣ በኢትዮጵያ የፈለገ ጥሩ ሃሳብ፣ ጥሩ አመለካከት ይዘህ ብትመጣ አንተን ለመቃረን ብቻ ሌላ ኃይል ተደራጅቶ ይጠብቅሃል። ይህ ማደም፤ ሴራ ነው። ይህ የሴራ ፅንሰ ሃሳብ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ከምንጊዜውም በላይ አሁን ገዝፎ ወጥቷል። “የፈለገ ጥሩ ሃሳብ፣ ጥሩ አመለካከት ይዘህ ብትመጣ አንተን ለመቃረን ብቻ ሌላ ኃይል ተደራጅቶ ይጠብቅሃል”። ይህ የሴራ ፅንሰ ሃሳብ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ከምንጊዜውም በላይ አሁን ገዝፎ መውጣቱን ዶክተር ደመቀ … [Read more...] about “የሤራ ፅንሰ ሃሳብ በኢትዮጵያ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ አሁን ገዝፎ ወጥቷል” ዶ/ር ደመቀ
አራት መቶ ሺህ ዶላር የሚያወጣ ኮኬይን ቦሌ በቁጥጥር ሥር ዋለ
ወደ ታይላንድ ዋና ከተማ ባንኮክ ሊጓጓዝ የነበረ 400 ሺህ ዶላር የሚያወጣ 4 ኪሎግራም ኮኬይን በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ። አገልግሎቱ ለኢቲቪ በላከው መረጃ እንደገለጸው በዛሬው ዕለት ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ አንድ ኢትዮጵያዊ 4 ኪሎ ግራም ኮኬይን የተባለ አደንዛዥ ዕጽ በማይሰራ ላፕቶፕ ቦርሳ ውስጥ ደብቆ ለማሳለፍ ሲሞክር በቀጥጥር ሥር ውሏል። ተጠርጣሪው ከአዲስ አበባ ወደ ባንኮክ በላፕቶፕ ቦርሳ ለማሳለፍ የሞከረው አራት ኪሎ ግራም ኮኬይን በኤክስሬይ ፍተሻ አማካኝነት የተያዘ ሲሆን፤ በወንጀል ድርጊቱ ተባባሪ እንደሆኑ የተጠረጠሩ ሌሎች ሶሰት ግለሰቦችም እጅ ከፍንጅ መያዛቸው ተገልጿል። በወንጀል ድርጊቱ የተሳተፉት አራት ተጠርጣሪዎችና አደንዛዥ ዕፁ ለተጨማሪ ምርመራ ለፌደራል ፖሊስ … [Read more...] about አራት መቶ ሺህ ዶላር የሚያወጣ ኮኬይን ቦሌ በቁጥጥር ሥር ዋለ
ህወሃት “የመጨረሻ” ያለው ሤራ መክሸፉን መቀበል አቅቶታል
መንግሥት ህወሃትን ቀስ በቀስ ሥሩን እየቆራረጠ ቢቆይም አብዛኞች ባለመረዳትና በተገዙ ኃይሎች ውዥንብር ዕድሜው ሊራዘም እንደቻለ ለህወሃት ቅርበት ያላቸው እየገለጹ ነው። በተቀነባበረ ዕቅድ ሃጫሉ እንዲገደል ተደርጎ መንግሥትን ለመገልበጥ የታቀደውና የመጨረሻ የተባለው ሤራ መክሸፉ ህወሃት መንደር ግራ መጋባት መፍጠሩ ተስምቷል። የዐቢይ አስተዳደር እንደሚባለው ደካማ እንዳልሆነም አንዳንዶቹ በይፋ ሲናገሩ ተደምጧል። ለውጡን ተክትሎ ከህወሃት አሰልቺ የስብሰባና የግምገማ (ምይይጥ) ባህል በተቃራኒው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በፍጥነት መጓዛቸውና ለህወሃቶች ከጅምሩ የማሰቢያ ጊዜ የከለከለ ነበር። የጎልጉል ታማኝ የመረጃ ምንጭ እንደሚሉት፤ የህወሃት ከፍተኛ አመራሮች ሲነጋ ልክ እንደማንኛውም ተራ ዜጋ ከፍተኛና አዳዲስ ውሳኔዎችን ይሰማሉ። በዚህም እነርሱ ለአንዱ ጉዳይ አንድ ወር ሲሰበሰቡና … [Read more...] about ህወሃት “የመጨረሻ” ያለው ሤራ መክሸፉን መቀበል አቅቶታል
በወታደራዊ መረጃ ምጡቅ እርምጃ
ዛሬ ታኅሣሥ 10፤2012ዓም ኢትዮጵያ በታሪኳ መጀመሪ የሆነውን ሳተላይት አምጥቃለች። ሳተላይቷ መረጃ አገልግሎት የምትሰጥ ነች የተባለ ሲሆን ይህም ባብዛኛው የመልከዓ ምድር ጥናትና የመሳሰሉትን ለማድግ የምትጠቅም መሆኗ ተነግሯል። ለወታደራዊ ግልጋሎት አትውልም የሚል ቢባም ሳተላቷ መረጃ ስትሰበስብ ይህ ቀረሽ እንደማትባል፤ “ከግዙፍ ክንውኖች እስከ ጥቃቅን እንቅስቃሴዎች” እንደምትመዘግብና እንደምታስተላልፍ ባለሙያዎቹ ይናገራሉ። በዓለማችን ወታደራዊ የበላይነት የተጎናጸፉ አገራት በርካታ ሳተላይቶች በኅዋው ላይ አላቸው። ከምስራቅ አፍሪካ እንኳን በኬኒያና በሱዳን ተቀድመናል። ከተለያየ አቅጣጫ የውጭ ጠላት ያላት አገራችን አንድ ብቻ አይደለም በርካታ ሳተላይቶች ያስፈልጓታል። በተለይ ደግሞ አገር ውስጥ ያሉ አፍራሾች የሚደርጉትን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር፣ ማባሪያ ያጣውን የወሰን … [Read more...] about በወታደራዊ መረጃ ምጡቅ እርምጃ
ጃዋር፤ ለኦሮሚያ የተጠመደ ፈንጂ!
“… ስሙን መጥቀስ ባያስፈልግም አንድ ጎረምሳ ልንለው እንችላለን። ጃዋር ዜግነቱ አሜሪካዊ በመሆኑ የጃዋር ሚዲያ የተመዘገበው በዚህ ጎረምሳ ስም ነው። ከየአቅጣጫው የሚሰበሰበው ገንዘብ የሚቀመጠው በዚሁ ልጅ ስም ነው። መኪኖችና አንዳንድ ንብረቶች የሚገዙትም በዚሁ ስም ነው። ይህ ጎረምሳ አዲስ አበባ እጅግ መንዛሪና በከፍተኛ ቅንጦት እንደሚኖር የሚያውቁት ነገረውኛል። የቄሮ አካልም አልነበረም። ቄሮ ከድል በኋላ ቤቱ ሲመለስ የጠበቀው ማሳውና መደቡ ሲሆን እነ ጃዋርና ስማቸውን የሚጠቀሙባቸው ጎረምሶች በሚሊዮኖች እየረጩ ዘመናዊ ተሽከርካሪ ይሸምታሉ፤ ንብረት ያከማቻሉ፤ ሰዎች ሰላም ሰፍኖ በተረጋጋ መልኩ እንዳያስቡ ቀውስ ይመረትላቸዋል። ልክ ከዚህ በፊት ተደርጎ እንደማይታወቅ በዓሉንም፣ ልደቱንም፣ በሚዲያ እያስጮሁ ያሳብዱታል። ይህ ወጣት የሰከነ ዕለት ለጃዋር የሚቀርብለት ጥያቄ ስለሚታወቅ … [Read more...] about ጃዋር፤ ለኦሮሚያ የተጠመደ ፈንጂ!
መንግሥትና ኦዲፒ የጃዋርን የድጎማ በጀት ጥያቄ ውድቅ አደረጉ
የኦሮሞ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ሥራ አስኪያጅና ባለቤት ጃዋር መሃመድ ለድርጅቱ በጀት እንዲመደብና በቋሚነት እንዲረዳ ለመንግሥት ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ መደረጉ ታወቀ። የጎልጉል የኦዲፒ የመረጃ ምንጮች እንዳሉት የድጎማ ጥያቄው ውድቅ መደረጉ ጃዋር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይና በኦዲፒ ላይ የጥላቻ ሪፖርት ተጠናክሮ እንደሚሠራ መናገራቸውን አመልክተዋል። በተያያዘ ጃዋር የሚመራው ኦ.ኤም.ኤን. ለሸዋ ተወላጅ ኦሮሞዎች መድረክ እንደማይሰጥና ኦነግ በንጹሃን ላይ እየፈጸመ ያለውን ግድያም ሽፋን እንዲሰጥ እንደማይፈቅድ ተገልጿል። እንደ መረጃ አቀባዮቹ ከሆነ ጃዋር ለሚመራው “የትግል ሚዲያ” ከፍተኛ በጀት የጠየቀው ሚዲያው ለተገኘው ለውጥ ትልቁን ሚና ተጫውቷል በሚል ነው። ኦ.ኤም.ኤን. በትግሉ ወቅት የአንበሳውን ድርሻ በመጫወቱ የኦሮሚያ ክልልም ሆነ መንግሥት ሊደጉመው እንደሚገባ በተደጋጋሚ … [Read more...] about መንግሥትና ኦዲፒ የጃዋርን የድጎማ በጀት ጥያቄ ውድቅ አደረጉ