• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በቦሌ በኩል አሮጌው ብር እየገባ ነው፤ በበረራ ሠራተኞችና መንገደኞች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ ተጠየቀ

September 23, 2020 11:59 pm by Editor Leave a Comment

“ህወሓት ወደ አገር በሚገቡ መንገደኞች ገንዘብ ለማስገባት እየጣረ ነው” በሚል ርዕስ አንድ ዘገባ ካወጣን በኋላ ዛጎል “በአሜሪካ “ገንዘብ – ውሰዱልን” የቅርብ ወዳጆችን ግንኙነት በጠሰ” በሚል ርዕስ የሚከተለውን ዘገባ ለንባብ አብቅቷል። አሁንም የኢትዮጵያን መንግሥት ለማሳሰብ የምንፈልገው ይህንን የተቀናጀ ሥራ እያከናወኑ ያሉት ህወሓቶች መሆናቸውን ነው።

ከዚህ ሌላ በተለያዩ የኢትዮጵያ ድንበር ኬላዎች ከጎረቤት አገር ወደ ኢትዮጵያ ገንዘብ ይገባል ከሚለው እሳቤ በተጨማሪ በቦሌ በኩልም እየገባ እንደሆነ ሊታወቅ ይገባዋል። ስለዚህ በቦሌ ዓለምአቀፍ አውሮጵላን ማረፊያ በተጓዦች በተለይም በበረራ ሠራተኞች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ሊደረግ ይገባል እንላለን።

በአሜሪካ “ገንዘብ – ውሰዱልን” የቅርብ ወዳጆችን ግንኙነት በጠሰ

“እንዴት ብትንቁን ነው” ሲል ባለቤት ቁጣ የተሞላ ምላሽ ሰጠ። ባልና ሚስት የቆየ ወዳጆቻቸው ቤት ሄደው እንደ ሃበሻ ወግ ከተጋበዙ በኋላ “ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ ውሰዱልን” ብለው ሲጠይቃሉ። እንግዶቻቸውን እየጋበዙ ያሉት ቤተሰቦች ምን ያህል እንደሆነ ይጠይቃሉ። እንግዶች “ሁለት መቶ ሺህ” ሲሉ ይመልሳሉ።

ጥያቄው የቀረበላቸው ሰዎች በመደነቅና በተደበላለቀ ስሜት “ሁለት መቶ ሺህ ዶላር?” ሲሉ በመገረም ማብራሪያ እንደሚፈልጉ ይገልጻሉ። “አይደለም የኢትዮጵያ ብር” ሲሉ እንግዶች ይመልሳሉ። ከዚያም አንድ ሁለት ይባባሉና ይካረራሉ። ጥያቄው የቀረበላቸው ቤተሰቦች በተለይም ባል “እንዴት ብትንቁን ነው” ሲል ቅሬታውን በቁጣ ያሰማል። በዚያው የቃላት ልውውጡ በርትቶ በሚስት ሸምጋይነት እንግዶች ቤቱን ለቀው የሄዳሉ። ነገሩ እንዲህ ነው።

ለረዥም ዓመታት አሜሪካን አገር የኖሩ እናት ከእርጅና ጋር በተያያዘ ስለተዳከሙና ስለታመሙ “ለአገሬ አፈር አብቁኝ” በማለት ልጃቸውን ወትውተው ወደ አዲስ አበባ ለማምራት ከሁለት ቀን በፊት ጉዞ ነበራቸው። በጣም ስለተዳከሙ ቤተሰቦቻቸው አዲስ አበባ በሰላም እንዲደርሱ ለእሳቸው ድጋፍ ስለማድረግና ስለ ጉዞው ከማሰብና ከመጨነቅ ውጪ ሌላ ሃሳብ አልነበራቸውም። ጉዞው ረዥምና የስንበትም ዓይነት በመሆኑ!

በዚህ መሃል ነበር የቀድሞ ወዳጆቻቸው ልጅ እናቱን ይዞ ወደ አገር ቤት እንደሚያመራ በመስማታቸው ለጉብኝት የሄዱት። ይሁን እንጂ ጉብኝቱ ሁለት ዓላማ ያለው ነበረው። መሰናበትና ብር መላክ። ለዚህም ውለታ ክፍያ መስጠት።

ድርጊቱን በስልክ የተከታተለች ለዛጎል እንደነገረችው ሁለት መቶ ሺህ የኢትዮጵያ አሮጌ ብር ወደ አገር ቤት ለመላክ የቀረበው ጥያቄ መጨረሻው የበርካታ ዓመታት ወዳጅ ቤተሰቦችን አለያይቷል። ወዳጅነታቸው ተበጥሷል። በደከሙ እናት ሻንጣ ውስጥ በመደበቅ ገንዘቡን ወደ ኢትዮጵያ እንዲሄድላቸው የጠየቁት ሰዎች ሌላም ብር እንዳላቸው፣ ብሩንም በተለያዩ ጊዜያት ወደ አሜሪካ ንብረት ሸጠው እንዳመጡት አስረድተዋል።

ታሪኩን ያስረዳችው “ተደፈርን” ያሉት ቤተሰቦች ዘመድ ስትሆን ይህንን መረጃ ከሰማች በኋላ ፊንላንድና ሎንደን ከባልደረቦቿ ጋር በዚሁ አስገራሚ ጉዳይ ስትወያይ እነሱ አካባቢም በተመሳሳይ መልኩ ጥያቄው እንደሚቀርብ ጠቅሰው ይህንን ጉዳይ የኤርፖርት ሃላፊዎች እንዲሰሙ ቢደረግ መልካም እንደሆነ እንደነገሯትና ለዛጎል ለመግለጽ እንዳነሳሳት ገልጻለች።

“ማሰብ የተሳነን ይመላል። እናት የደከመባቸውን ቤተሰቦች በህገወጥ ገንዘብ ውሰዱልን። ወሮታ እንከፍላለን ማለት ፍጹም ሰዋዊ አይደለም። ሰው ራሱ ህገወጥ መሆኑ ሳያንሰው ሌሎችን ህገወጥ ለማድረግ መድፈሩ ያስገርማል” ብሎ እናቷ የደከሙባት ዘመዷ ባለቤት መናገሩንና እልህ መጋባቱን የገለጸችው ሴት፣ ከድንበር ጥበቃ ባልተናነሰ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጓዦች፣ እንዲሁም የበረራ ሰራተኞች ላይ ጠንካራ ፍተሻና ቁጥጥር ሊደረግ እንደሚገባ መክራለች።

ከሁሉም በላይ ግን በአሜሪካና በአውሮፓ የኢትዮጵያ ብር በግለሰቦች እጅ እንዳለ ማረጋገጧ አንዳስገረማት፣ ይህም ገንዘብ በአየር መንገድ በኩል ስለመውጣቱ ጥርጥር እንደሌለውና ማምከን የሚቻለውም የወጣበትን ቀዳዳ በመድፈን እንደሆነ አመልክታለች። ሕዝብ ገንዘብ መቀየር የተፈለገበት ምክንያት ግልጽ ከሆነለት በተመሳሳይ የሚቀርቡለትን ጥያቄዎች ወደ ጎን በማለት ወደ ህግ በማቅረብና ጥቆማ በመስጠት ሊተባበር እንደሚገባም አመልክታለች። ለወደፊቱም በተመሳሳይ መረጃ ከመስጠት ወደ ኋላ እንደማትል አስታውቃለች።

ጥቆማ ሰጪዋ የሰዎቹን ስምና የመኖሪያ ከተማ የገለጸች ቢሆንም ከማተም ተቆጥበናል። መንግስት የብር ኖት እንደሚቀየር ይፋ ካደርረገ በኋላና በፊት ከፍተኛ መጠን ያለው የአገር ውስጥና የተለያዩ አገራት የብር ኖቶች በፍተሻ ኬላዎች ላይ መያዛቸው ሪፖርት ሲደረግ መሰንበቱ ይታወቃል።

በኢትዮጵያ ከ113 ቢሊዮን ብር በላይ ከመንግሥት ባንክ ቁጥጥር ወይም ስርዓት ውጪ እንደሚንቀሳቀስ፣ ከፍተኛ መጠን ያለው ህገወጥ የብር ኖት ገበያው ላይ መሰራጨቱ አንድ ላይ ተዳምሮ የአገሪቱን የግሽበት መጠን እንዳናረው ባለሙያዎች ሲናገሩ፣ መንግሥትም ይህንኑ አውቆ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱ ይታወሳል።

የብር ኖት ለውጡ ይፋ ከሆነ በኋላ ውሳኔውን እጅግ አክርረው የሚቃወሙ ወገኖች መሰማታቸው ጉዳዩን አስገራሚ እንዳደረገው ከተለያዩ ባለሙያዎች እየተደመጠ ነው። ማንም ተቃዋሚም ሆነ የመንግሥት አካል ህገወጥ ገንዘብ የአገሪቱን ኢኮኖሚ እያሽመደመደና ለሽብር ተግባር እየዋለ ባለበት ወቅት የመንግሥትን ውሳኔ መቃወሙ “ሕገወጥ ገንዘብና ህገወጥነት ይሻለኛል በማለት አገሪቱ ላይ ማፊያ እንዲፈነጭ መፈቀድ ነው” በሚል ክፉኛ ተተችቷል። (@ዛጎል፥ ፎቶው በርግጥ ቦሌ የተከሰተ ሳይሆን ለማሳያነት የቀረበ ነው)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Ethiopia, new birr notes, new currency, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule