• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በቦሌ በኩል አሮጌው ብር እየገባ ነው፤ በበረራ ሠራተኞችና መንገደኞች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ ተጠየቀ

September 23, 2020 11:59 pm by Editor Leave a Comment

“ህወሓት ወደ አገር በሚገቡ መንገደኞች ገንዘብ ለማስገባት እየጣረ ነው” በሚል ርዕስ አንድ ዘገባ ካወጣን በኋላ ዛጎል “በአሜሪካ “ገንዘብ – ውሰዱልን” የቅርብ ወዳጆችን ግንኙነት በጠሰ” በሚል ርዕስ የሚከተለውን ዘገባ ለንባብ አብቅቷል። አሁንም የኢትዮጵያን መንግሥት ለማሳሰብ የምንፈልገው ይህንን የተቀናጀ ሥራ እያከናወኑ ያሉት ህወሓቶች መሆናቸውን ነው።

ከዚህ ሌላ በተለያዩ የኢትዮጵያ ድንበር ኬላዎች ከጎረቤት አገር ወደ ኢትዮጵያ ገንዘብ ይገባል ከሚለው እሳቤ በተጨማሪ በቦሌ በኩልም እየገባ እንደሆነ ሊታወቅ ይገባዋል። ስለዚህ በቦሌ ዓለምአቀፍ አውሮጵላን ማረፊያ በተጓዦች በተለይም በበረራ ሠራተኞች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ሊደረግ ይገባል እንላለን።

በአሜሪካ “ገንዘብ – ውሰዱልን” የቅርብ ወዳጆችን ግንኙነት በጠሰ

“እንዴት ብትንቁን ነው” ሲል ባለቤት ቁጣ የተሞላ ምላሽ ሰጠ። ባልና ሚስት የቆየ ወዳጆቻቸው ቤት ሄደው እንደ ሃበሻ ወግ ከተጋበዙ በኋላ “ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ ውሰዱልን” ብለው ሲጠይቃሉ። እንግዶቻቸውን እየጋበዙ ያሉት ቤተሰቦች ምን ያህል እንደሆነ ይጠይቃሉ። እንግዶች “ሁለት መቶ ሺህ” ሲሉ ይመልሳሉ።

ጥያቄው የቀረበላቸው ሰዎች በመደነቅና በተደበላለቀ ስሜት “ሁለት መቶ ሺህ ዶላር?” ሲሉ በመገረም ማብራሪያ እንደሚፈልጉ ይገልጻሉ። “አይደለም የኢትዮጵያ ብር” ሲሉ እንግዶች ይመልሳሉ። ከዚያም አንድ ሁለት ይባባሉና ይካረራሉ። ጥያቄው የቀረበላቸው ቤተሰቦች በተለይም ባል “እንዴት ብትንቁን ነው” ሲል ቅሬታውን በቁጣ ያሰማል። በዚያው የቃላት ልውውጡ በርትቶ በሚስት ሸምጋይነት እንግዶች ቤቱን ለቀው የሄዳሉ። ነገሩ እንዲህ ነው።

ለረዥም ዓመታት አሜሪካን አገር የኖሩ እናት ከእርጅና ጋር በተያያዘ ስለተዳከሙና ስለታመሙ “ለአገሬ አፈር አብቁኝ” በማለት ልጃቸውን ወትውተው ወደ አዲስ አበባ ለማምራት ከሁለት ቀን በፊት ጉዞ ነበራቸው። በጣም ስለተዳከሙ ቤተሰቦቻቸው አዲስ አበባ በሰላም እንዲደርሱ ለእሳቸው ድጋፍ ስለማድረግና ስለ ጉዞው ከማሰብና ከመጨነቅ ውጪ ሌላ ሃሳብ አልነበራቸውም። ጉዞው ረዥምና የስንበትም ዓይነት በመሆኑ!

በዚህ መሃል ነበር የቀድሞ ወዳጆቻቸው ልጅ እናቱን ይዞ ወደ አገር ቤት እንደሚያመራ በመስማታቸው ለጉብኝት የሄዱት። ይሁን እንጂ ጉብኝቱ ሁለት ዓላማ ያለው ነበረው። መሰናበትና ብር መላክ። ለዚህም ውለታ ክፍያ መስጠት።

ድርጊቱን በስልክ የተከታተለች ለዛጎል እንደነገረችው ሁለት መቶ ሺህ የኢትዮጵያ አሮጌ ብር ወደ አገር ቤት ለመላክ የቀረበው ጥያቄ መጨረሻው የበርካታ ዓመታት ወዳጅ ቤተሰቦችን አለያይቷል። ወዳጅነታቸው ተበጥሷል። በደከሙ እናት ሻንጣ ውስጥ በመደበቅ ገንዘቡን ወደ ኢትዮጵያ እንዲሄድላቸው የጠየቁት ሰዎች ሌላም ብር እንዳላቸው፣ ብሩንም በተለያዩ ጊዜያት ወደ አሜሪካ ንብረት ሸጠው እንዳመጡት አስረድተዋል።

ታሪኩን ያስረዳችው “ተደፈርን” ያሉት ቤተሰቦች ዘመድ ስትሆን ይህንን መረጃ ከሰማች በኋላ ፊንላንድና ሎንደን ከባልደረቦቿ ጋር በዚሁ አስገራሚ ጉዳይ ስትወያይ እነሱ አካባቢም በተመሳሳይ መልኩ ጥያቄው እንደሚቀርብ ጠቅሰው ይህንን ጉዳይ የኤርፖርት ሃላፊዎች እንዲሰሙ ቢደረግ መልካም እንደሆነ እንደነገሯትና ለዛጎል ለመግለጽ እንዳነሳሳት ገልጻለች።

“ማሰብ የተሳነን ይመላል። እናት የደከመባቸውን ቤተሰቦች በህገወጥ ገንዘብ ውሰዱልን። ወሮታ እንከፍላለን ማለት ፍጹም ሰዋዊ አይደለም። ሰው ራሱ ህገወጥ መሆኑ ሳያንሰው ሌሎችን ህገወጥ ለማድረግ መድፈሩ ያስገርማል” ብሎ እናቷ የደከሙባት ዘመዷ ባለቤት መናገሩንና እልህ መጋባቱን የገለጸችው ሴት፣ ከድንበር ጥበቃ ባልተናነሰ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጓዦች፣ እንዲሁም የበረራ ሰራተኞች ላይ ጠንካራ ፍተሻና ቁጥጥር ሊደረግ እንደሚገባ መክራለች።

ከሁሉም በላይ ግን በአሜሪካና በአውሮፓ የኢትዮጵያ ብር በግለሰቦች እጅ እንዳለ ማረጋገጧ አንዳስገረማት፣ ይህም ገንዘብ በአየር መንገድ በኩል ስለመውጣቱ ጥርጥር እንደሌለውና ማምከን የሚቻለውም የወጣበትን ቀዳዳ በመድፈን እንደሆነ አመልክታለች። ሕዝብ ገንዘብ መቀየር የተፈለገበት ምክንያት ግልጽ ከሆነለት በተመሳሳይ የሚቀርቡለትን ጥያቄዎች ወደ ጎን በማለት ወደ ህግ በማቅረብና ጥቆማ በመስጠት ሊተባበር እንደሚገባም አመልክታለች። ለወደፊቱም በተመሳሳይ መረጃ ከመስጠት ወደ ኋላ እንደማትል አስታውቃለች።

ጥቆማ ሰጪዋ የሰዎቹን ስምና የመኖሪያ ከተማ የገለጸች ቢሆንም ከማተም ተቆጥበናል። መንግስት የብር ኖት እንደሚቀየር ይፋ ካደርረገ በኋላና በፊት ከፍተኛ መጠን ያለው የአገር ውስጥና የተለያዩ አገራት የብር ኖቶች በፍተሻ ኬላዎች ላይ መያዛቸው ሪፖርት ሲደረግ መሰንበቱ ይታወቃል።

በኢትዮጵያ ከ113 ቢሊዮን ብር በላይ ከመንግሥት ባንክ ቁጥጥር ወይም ስርዓት ውጪ እንደሚንቀሳቀስ፣ ከፍተኛ መጠን ያለው ህገወጥ የብር ኖት ገበያው ላይ መሰራጨቱ አንድ ላይ ተዳምሮ የአገሪቱን የግሽበት መጠን እንዳናረው ባለሙያዎች ሲናገሩ፣ መንግሥትም ይህንኑ አውቆ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱ ይታወሳል።

የብር ኖት ለውጡ ይፋ ከሆነ በኋላ ውሳኔውን እጅግ አክርረው የሚቃወሙ ወገኖች መሰማታቸው ጉዳዩን አስገራሚ እንዳደረገው ከተለያዩ ባለሙያዎች እየተደመጠ ነው። ማንም ተቃዋሚም ሆነ የመንግሥት አካል ህገወጥ ገንዘብ የአገሪቱን ኢኮኖሚ እያሽመደመደና ለሽብር ተግባር እየዋለ ባለበት ወቅት የመንግሥትን ውሳኔ መቃወሙ “ሕገወጥ ገንዘብና ህገወጥነት ይሻለኛል በማለት አገሪቱ ላይ ማፊያ እንዲፈነጭ መፈቀድ ነው” በሚል ክፉኛ ተተችቷል። (@ዛጎል፥ ፎቶው በርግጥ ቦሌ የተከሰተ ሳይሆን ለማሳያነት የቀረበ ነው)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Ethiopia, new birr notes, new currency, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule