• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት ወደ አገር በሚገቡ መንገደኞች ገንዘብ ለማስገባት እየጣረ ነው

September 23, 2020 02:00 am by Editor 6 Comments

በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገውን የገንዘብ ኖት ለውጥ ተከትሎ መደናገጥ ውስጥ የሚገኘው ህወሓት ከውጭ አገራት ወደ ኢትዮጵያ የብር ኖቶችን እያስገባ እንደሆነ ተጠቆመ። ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ፤ ቦሌ ዓለምአቀፍ አውሮጵላን ማረፊያ ደግሞ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ ተጠየቀ።

ጭንቅላቱ የደረቀውና ኪሱ ወደ በመድረቅ ጉዞ ላይ ያለው ህወሓት የገንዘብ ለውጡን ተከትሎ ከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ እንደገባ ጎልጉል ያጠናቀረውን መረጃ ለንባብ አብቅቶ ነበር።

ከሁለት ዓመት ተኩል በፊት ከምኒልክ ቤተመንግሥት የተባረረው ህወሓት መቀሌ በየሆቴሉ መሽጎ በኢትዮጵያ የሽብር ተግባራትን ሲፈጽም ቆይቷል። ይህንንም ተግባሩን ለማስፈጸም እንዲረዳው በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር፤ ሐሰተኛ የብር ኖቶች በማተም ተግባር፤ በኮንትሮባንድ ንግድ፤ ገንዘብ ከአገር በማሸሽ፤ ወዘተ ሕገወጥ ተግባራት ተሰማርቶ አገር የማፍረስ ሥራውን በትጋት ሲሠራ ቆይቷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ጎልጉል የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ህወሓት እጅግ በርካታ የብር ኖቶችን ከአገር በማውጣት በአሜሪካና በአውሮጳ በሚገኙ አባልና ተላላኪዎቹ እጅ አስቀምጧል። ይህንን መጠኑ እጅግ በርካታ የሆነ ብር ከገንዘብ ምንዛሪ ጀምሮ ለተለያዩ አገር የማፍረስ ተግባራት ወደ አገር በመላክ ሲጠቀምበት እንደነበር መረጃው ይጠቁማል።

የብር ኖቶች መለወጣቸውን ተከትሎ በተሰጠው መግለጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይና የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ይናገር ደሴ እንደተናገሩት እጅግ በርካታ ገንዘብ በውጭ አገራት በተለይም በጎረቤት አገራት እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ጎልጉል ያገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በህወሓት እጅ በአውሮጳና አሜሪካ የሚገኘው ብር በየጊዜው ለተለያዩ የኮንትሮባንድና የሽብር ሥራ በጎረቤት አገራት በኩል ሲገባ እንደነበር ነው። ሆኖም የገንዘብ ኖት በመቀየሩ ይህ በምዕራቡ ዓለም የተከማቸውን ብር ለመቀየር የህወሓት ሰዎች ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ መንገደኞችን እያግባቡ እንደሆነ ጥያቄው የቀረበላቸው ለጎልጉል ተናግረዋል።

ከአሜሪካ ደለስ ኤርፖርት ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ የሚያደርጉ ሰዎችን በመምረጥና ቀረብ ብሎ በማናገር ይህንን ያህል መቶ ሺህ ብር ይዛችሁልን ሂዱ ይህንን ያህል ዶላር እከፍላለን በማለት የማግባባት ጥያቄ እንደቀረበላቸው መረጃ አቀባያችን ተናግረዋል።

ተመሳሳይ ተግባር ከአውሮጳ ለሚነሱ መንገደኞች እየቀረበላቸው እንደሆነ ከዚሁ ጋር ተያይዞ የተገኙት መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ጉዳዩ ያሳሰባቸው ወገኖች መንግሥት በድንበር በኩል ብቻ ይገባል ብሎ የሚጠብቀው ብር ባልተጠበቀ ሁኔታ በቦሌ በኩል በሻንጣ እየተሞላ እየገባ የመሆኑን ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል።

ይህንን በርካታ የገንዘብ መጠን ይዘው የሚገቡት ሰዎች በጥንቃቄ የተመረጡ የማይጠረጠሩ መንገደኞች፤ የዕድሜ ባለጸጋዎች፤ በተለይም ሴቶች እንደሆኑና በሁሉም መስክ ቦሌ ዓለምአቀፍ አውሮጵላን ማረፊያ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።

ያለፈው ሳምንት ከዋሽንግተን ደለስ ኤርፖርት ወደ አዲስ አበባ ሊጓዝ ከነበረ መንገደኛ የአሜሪካ ጉምሩክና ድንበር ተቆጣጣሪዎች የተያዘው ገንዘብ 98,762 ዶላር መያዛቸው ይታወሳል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ        

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Left Column, News Tagged With: dulles airport, Ethiopia, new birr notes, new currency, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tariku says

    September 24, 2020 01:56 am at 1:56 am

    በተለያየ አጋጣሚ ውጭም ይሁን ሃገር ውስጥ ያለ ገንዘብ ሲንቀሳቀስና ሲያዝም፡እየታየ ነው ገና ብዙ ነገር ልታይም ይችላል ከዝህ በኋላም በተለያየ አከባቢ የሚነሱ የሽብር ጥቃቶች በተወሰነ መልኩ ሊቆሙ ይችላሉ

    Reply
  2. Kibrey says

    September 24, 2020 09:53 am at 9:53 am

    Ere afh molteh wshet le hzbu stakerb berash mafer alebh yemr

    Reply
  3. TD says

    September 24, 2020 10:09 am at 10:09 am

    Too sad!
    Can’t lead a country by Tit-for-tat principals.

    Reply
  4. Samuel says

    September 24, 2020 09:11 pm at 9:11 pm

    ዶር አብይም እንደ ሕወሀት ሳይደነፋ በብልሀት ብቻ ገና ልክ ያስገባቼዋል እኝህ ሌባ የሌባ ዘር

    Reply
  5. shamsu suliman says

    September 25, 2020 03:39 am at 3:39 am

    ድቡን የአለ ዉሸት

    Reply
  6. A. Belayneh says

    September 25, 2020 06:48 pm at 6:48 pm

    TPLF has mastered the “art” of theft using all available tools. If Eritrea’s experience following separation from Ethiopia is any lesson, TPLF would sink in VERY DEEP hole, and can be expected to do anything and everything to come out of the shit hole. Economic strangulation is an obvious tool available to the federal government, and should use it starting immediately. Forget about the ‘common people’ because most of those are supporters and/or members of TPLF.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule