• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት ወደ አገር በሚገቡ መንገደኞች ገንዘብ ለማስገባት እየጣረ ነው

September 23, 2020 02:00 am by Editor 6 Comments

በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገውን የገንዘብ ኖት ለውጥ ተከትሎ መደናገጥ ውስጥ የሚገኘው ህወሓት ከውጭ አገራት ወደ ኢትዮጵያ የብር ኖቶችን እያስገባ እንደሆነ ተጠቆመ። ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ፤ ቦሌ ዓለምአቀፍ አውሮጵላን ማረፊያ ደግሞ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ ተጠየቀ።

ጭንቅላቱ የደረቀውና ኪሱ ወደ በመድረቅ ጉዞ ላይ ያለው ህወሓት የገንዘብ ለውጡን ተከትሎ ከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ እንደገባ ጎልጉል ያጠናቀረውን መረጃ ለንባብ አብቅቶ ነበር።

ከሁለት ዓመት ተኩል በፊት ከምኒልክ ቤተመንግሥት የተባረረው ህወሓት መቀሌ በየሆቴሉ መሽጎ በኢትዮጵያ የሽብር ተግባራትን ሲፈጽም ቆይቷል። ይህንንም ተግባሩን ለማስፈጸም እንዲረዳው በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር፤ ሐሰተኛ የብር ኖቶች በማተም ተግባር፤ በኮንትሮባንድ ንግድ፤ ገንዘብ ከአገር በማሸሽ፤ ወዘተ ሕገወጥ ተግባራት ተሰማርቶ አገር የማፍረስ ሥራውን በትጋት ሲሠራ ቆይቷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ጎልጉል የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ህወሓት እጅግ በርካታ የብር ኖቶችን ከአገር በማውጣት በአሜሪካና በአውሮጳ በሚገኙ አባልና ተላላኪዎቹ እጅ አስቀምጧል። ይህንን መጠኑ እጅግ በርካታ የሆነ ብር ከገንዘብ ምንዛሪ ጀምሮ ለተለያዩ አገር የማፍረስ ተግባራት ወደ አገር በመላክ ሲጠቀምበት እንደነበር መረጃው ይጠቁማል።

የብር ኖቶች መለወጣቸውን ተከትሎ በተሰጠው መግለጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይና የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ይናገር ደሴ እንደተናገሩት እጅግ በርካታ ገንዘብ በውጭ አገራት በተለይም በጎረቤት አገራት እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ጎልጉል ያገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በህወሓት እጅ በአውሮጳና አሜሪካ የሚገኘው ብር በየጊዜው ለተለያዩ የኮንትሮባንድና የሽብር ሥራ በጎረቤት አገራት በኩል ሲገባ እንደነበር ነው። ሆኖም የገንዘብ ኖት በመቀየሩ ይህ በምዕራቡ ዓለም የተከማቸውን ብር ለመቀየር የህወሓት ሰዎች ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ መንገደኞችን እያግባቡ እንደሆነ ጥያቄው የቀረበላቸው ለጎልጉል ተናግረዋል።

ከአሜሪካ ደለስ ኤርፖርት ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ የሚያደርጉ ሰዎችን በመምረጥና ቀረብ ብሎ በማናገር ይህንን ያህል መቶ ሺህ ብር ይዛችሁልን ሂዱ ይህንን ያህል ዶላር እከፍላለን በማለት የማግባባት ጥያቄ እንደቀረበላቸው መረጃ አቀባያችን ተናግረዋል።

ተመሳሳይ ተግባር ከአውሮጳ ለሚነሱ መንገደኞች እየቀረበላቸው እንደሆነ ከዚሁ ጋር ተያይዞ የተገኙት መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ጉዳዩ ያሳሰባቸው ወገኖች መንግሥት በድንበር በኩል ብቻ ይገባል ብሎ የሚጠብቀው ብር ባልተጠበቀ ሁኔታ በቦሌ በኩል በሻንጣ እየተሞላ እየገባ የመሆኑን ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል።

ይህንን በርካታ የገንዘብ መጠን ይዘው የሚገቡት ሰዎች በጥንቃቄ የተመረጡ የማይጠረጠሩ መንገደኞች፤ የዕድሜ ባለጸጋዎች፤ በተለይም ሴቶች እንደሆኑና በሁሉም መስክ ቦሌ ዓለምአቀፍ አውሮጵላን ማረፊያ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።

ያለፈው ሳምንት ከዋሽንግተን ደለስ ኤርፖርት ወደ አዲስ አበባ ሊጓዝ ከነበረ መንገደኛ የአሜሪካ ጉምሩክና ድንበር ተቆጣጣሪዎች የተያዘው ገንዘብ 98,762 ዶላር መያዛቸው ይታወሳል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ        

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: dulles airport, Ethiopia, new birr notes, new currency, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tariku says

    September 24, 2020 01:56 am at 1:56 am

    በተለያየ አጋጣሚ ውጭም ይሁን ሃገር ውስጥ ያለ ገንዘብ ሲንቀሳቀስና ሲያዝም፡እየታየ ነው ገና ብዙ ነገር ልታይም ይችላል ከዝህ በኋላም በተለያየ አከባቢ የሚነሱ የሽብር ጥቃቶች በተወሰነ መልኩ ሊቆሙ ይችላሉ

    Reply
  2. Kibrey says

    September 24, 2020 09:53 am at 9:53 am

    Ere afh molteh wshet le hzbu stakerb berash mafer alebh yemr

    Reply
  3. TD says

    September 24, 2020 10:09 am at 10:09 am

    Too sad!
    Can’t lead a country by Tit-for-tat principals.

    Reply
  4. Samuel says

    September 24, 2020 09:11 pm at 9:11 pm

    ዶር አብይም እንደ ሕወሀት ሳይደነፋ በብልሀት ብቻ ገና ልክ ያስገባቼዋል እኝህ ሌባ የሌባ ዘር

    Reply
  5. shamsu suliman says

    September 25, 2020 03:39 am at 3:39 am

    ድቡን የአለ ዉሸት

    Reply
  6. A. Belayneh says

    September 25, 2020 06:48 pm at 6:48 pm

    TPLF has mastered the “art” of theft using all available tools. If Eritrea’s experience following separation from Ethiopia is any lesson, TPLF would sink in VERY DEEP hole, and can be expected to do anything and everything to come out of the shit hole. Economic strangulation is an obvious tool available to the federal government, and should use it starting immediately. Forget about the ‘common people’ because most of those are supporters and/or members of TPLF.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule