• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጭንቅላቱ የደረቀው ህወሓት ኪሱም ሊደርቅ ነው

September 15, 2020 06:48 am by Editor 1 Comment

የብር ኖቶች መቀየር በህወሓት ሠፈር መደናገጥ ፈጥሯል

ኢትዮጵያ በአዳዲስ የብር ኖቶች እንደምትጠቀም ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ይፋ ካደረጉ በኋላ መቀሌ የመሸገው ህወሓት ችግር ውስጥ መግባቱ ተሰምቷል። አዳዲሶቹ ብሮች ሙስናን እና የኮንትሮባንድን ንግድ መቀልበስ ዓላማው ማድረጉ ተነግሯል።

ላለፉት ሁለት ዓመታት መቀሌ መሽጎ የሚገኘው ህወሓት የተባለው የበረኻ ወንበዴዎች ስብስብ ላለፉት እጅግ በርካታ ዓመታት ኢትዮጵያን ያለገደብ ሲዘርፍ የነበረ ቡድን መሆኑን ራሱም የሚመሰክረው ሐቅ ነው።

ከሁለት ዓመት ተኩል በፊት ከምኒልክ ቤተመንግሥት ከተባረረ ወዲህ መቀሌ በየሆቴሉ መሽጎ የሽብር ተግባራትን ሲፈጽም ቆይቷል። ይህንንም ተግባሩን ለማስፈጸም እንዲረዳው በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር፤ ሐሰተኛ የብር ኖቶች በማተም ተግባር፤ በኮንትሮባንድ ንግድ፤ ገንዘብ ከአገር በማሸሽ፤ ወዘተ ሕገወጥ ተግባራት ተሰማርቶ አገር የማፍረስ ሥራውን በትጋት ሲሠራ ቆይቷል። 

የኢትዮጵያ የገንዘብ ኖቶች ይቀየራሉ የሚለው መረጃ ሲነገር የቆየ ቢሆንም ጉዳዩ ለበርካታ ጊዜያት በምሥጢር ተይዞ ቆይቷል። ህወሓትም ባንድ በኩል የብር ኖቶችን ወደ ዶላርና ፓውንድ በመቀየሩ ተግባር በሥፋት ተሠማርቶበት የነበረ ቢሆንም ባልተጠበቀ ጊዜ ዜናው ይፋ መደረጉ በህወሓት ሠፈር መደናገጥ ፈጥሯል።  

የወንበዴዎቹ ቡድን ድርጎ የሚሠፍርላቸው ተላላኪዎች የብር ኖቶቹ መቀየራቸው ከተሰማበት ጊዜ ጀምሮ በህወሓት ሠፈር ሽብር መፈጠሩን የሚያመላክቱ መረጃዎችን ሲበትኑ ቆይተዋል። አንዳንዶቹ አስቀድመን ብሩን ወደ ውጭ ምንዛሪ ቀይረናል በማለት አልተሸነፍንም ለማለት የሞከሩ ሲሆን ሌሎቹ ደግሞ ሌሎች አጀንዳ የማስቀየሪያ መረጃዎችን በማሰራጨት ትኩረት ለመሳብ ሲሞክሩና በግልጽም ሲናገሩ ተስተውለዋል። 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ነባሮቹን የ10፣ የ50 እና የ100 ብር የገንዘብ ዓይነቶች ሙሉ ለሙሉ በመተካት ለግብይት የሚሆን አዲስ የገንዘብ ዓይነት በዛሬው ዕለት (ሰኞ) ይፋ አድርገዋል። ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያ የሁለት መቶ ብር ኖትን ወደ ሥራ ታስገባለች ብለዋል። በወጣው መረጃ መሠረት የ5 ብር ገንዘብ ባለበት ቀጥሎ፣ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ወደ ሣንቲም የሚለወጥ ይሆናል። 

የብር ኖቶቹ የመለወጥ ጉዳይ ይፋ ከሆነ በኋላ በትግራይ የህወሓት ሰዎች በተለያዩ ወጣቶች ብር በማስቀመጥ ለመለወጥ ሙከራ እያደረጉ እንደሆነ ተሰምቷል። ይህም በሕገወጥ መንገድ በህወሓት የተሰበሰበውን ብር ሕጋዊ ለማድረግ የታሰበው አካሄድ አስቀድሞ በፌዴራል መንግሥቱ የታሰበበት መሆኑን የሚያመለክት ሆኗል።

ጠቅላይ ሚ/ሩ እንደተናገሩት፤

  • ከ1.5 ሚሊዮን ብር በላይ ይዞ የሚመጣ ሰው ገንዘቡ ይወረሳል
  • በውክልና ገንዘብ መቀየር አይቻልም
  • ከኢትዮጵያ አጎራባች አገራት ወደ አገር ውስጥ የሚገባ ገንዘብ ይወረሳል
  • መከላከያ ወይም ፖሊስ ይህንን ወርሶ ተቋሙን ለማጠናከሪያ እንዲውል ይደረጋል
  • የሚቀየረው ገንዘብ ይዞ የመጣው ሰው ባለው ወይም በሚከፍተው የባንክ ሒሳብ የሚገባ ሲሆን ከሁለት መቶ ሺህ ብር በላይ መውሰድ አይቻልም
  • ሕገወጥ ገንዘብ በመለወጥ ሒደት ላይ የሚሳተፉ፤ በጎጥ፣ በዘር፣ በሃይማኖት፣ በወገንተኝነት፣ ወዘተ በመተባበር ሕገወጥ የሆነ ወይም ሃሰተኛ የብር ኖት በመቀየር የሚተባበሩ ባንኮች ወዲያውኑ ኅልውናቸውን ያጣሉ፤ ይዘጋሉ፡፡ እንደ ጠቅላይ ሚ/ሩ አነጋገር “በሚቀጥለው ቀን ባንክ መሆናቸው ያከትማል” ብለዋል፡፡

አዲሱ የብር ኖት 2.9 ቢሊዮን ታትሞ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ለስርጭት ዘግጁ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ አስታወቀ።

በዕለቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር ይናገር ደሴ አዲሱን የብር ኖት በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም፤

  • አዲሱን የብር ኖት ለማሳተም 3.7 ቢሊዮን ብር ውጭ መደረጉንም ገልጸው፤ በሁሉም ክልሎች በበቂ ሁኔታ ለማድረስ ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል።
  • የብር ቅያሬው በውክልና የማይከናወን በመሆኑ መታወቂያ በመያዝ ባለቤቱ ብቻ ማከናወን ይኖርበታል ብለዋል።
  • ከአጎራባች አገራት የሚገባን ህገ ወጥ ገንዘብ ለመቆጣጠር በድንበር አካባቢ ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግ መሆኑን ዶክተር ይናገር መግለፃቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የብር ኖቶቹን ለምን መቀየር አስፈለገ?

  • መደበኛ ባልሆነ መንገድ እንዲሁም ከፋይናንስ ተቋማት ውጪ የሚዘዋወረውን ገንዘብ ለመሰብሰብ፣
  • ሙስናን እና የኮንትሮባንድ ሥራዎችን ለመቀልበስ፣
  • ለሕገ ወጥ እንቅስቃሴዎች የሚደረግን ድጋፍ ለማስቀረት ፣

እርምጃው የፋይናንስ ተቋማት የገንዘብ እጥረትን ለመቋቋም እንዲችሉም እንደሚያግዝ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

አሁን በምን ደረጃ ላይ ይገኛል?

አብዛኛው የሕትመት ሥራ ተገባዶ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ግምጃ ቤት ይገኛል። የስርጭት ስርዓት እና ዕቅድ የተዘጋጀ ሲሆን፣ በሚመለከታቸው አካላት አማካኝነት ይተገበራል።

በገንዘብ ቅያሬው ሂደት ውስጥ የጸጥታ አስከባሪ አካላት ከፍተኛ ሚና የሚጫወቱ ሲሆን፣ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ከማኅበረሰቡ ጋር በመተባበር ጥንቃቄ በሞላበት መንገድ ያስፈጽማሉ ተብሏል።

ከብሔራዊ መከላከያ ሠራዊት፣ ከብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎትና ከፌደራል ፖሊስ የተውጣጣ ኮማንድ ፖስት ተቋቁሞ፣ ሂደቱን በበላይነት ያስተባብራል። የክልል መንግሥታት ተመሳሳይ ኮማንድ ፖስት አቋቁመው ሥራውን እንዲያከናውኑ ይጠበቃል።

  • አዲስ የታተሙት የብር ኖቶች ዓይነት፣ የደህንነት መጠበቂያ ምልክቶች እና ምስሎች

ተከታታይ ቁጥሮች

  • የገንዘቡ ቁጥሮች በሚያጎላ ማሽን ሲታዩ ከጥቁር ወደ አረንጓዴ ፍሎረሰንት ቀለም ይለወጣሉ።

ማየት ለተሳናቸው ዕውቅና ምልክት

  • የብሩን ዋጋ የሚገልፅ ማየት የተሳናቸው በእጅ ዳሰሳ ማወቅ የሚችሉበት የደህንነት መጠበቂያ ምልክት አለው።

ጎርባጣ መስመሮች

  • የባንክ ኖቱ ሲዳሰስ የመጎርበጥ ስሜት እንዲሁም የኖቱ ዋጋ ይታያል።

ደማቅ አንፀባራቂ ምልክት

  • ገንዘቡ ወደ ላይ ወይም ወደታች ሲዞር የሚንቀሳቀስ ደማቅ የቀለም ፍንጣቂ የደህንነት መጠበቂያ ምልክት።

የደህንነት መጠበቂያ ክር

  • የሚሽከረከር ደማቅ ቀለም ኮከብ አዲስ የደህንነት መጠበቂያ ክር፤ በክሩ ውስጥ NBE፣ ኢብባ እና የገንዘቦቹ አይነት ተፅፎ ይገኛል።

የውሃ ምልክት

  • ገንዘቡ ወደ ብርሃን አቅጣጫ ተደርጎ ሲታይ በላዩ ላይ ከሚገኘው ምስል ፊት ለፊት ተመሳሳይ ደብዛዛ የውሃ መልክ ያለው ምልክት ይታያል።

ትይዩ ምልክት

  • የብር ኖቶች ከብርሃን አቅጣጫ ሲታዩ ኳስ መሳይ ምልክት ከገንዘብ በስተኋላው ካለው ተመሳሳይ ጋር በፍፁም ትይዩ ሆነው በአንድ ቦታ ላይ ያርፋሉ።

ፈሎረሰንስ ምልክት

  • አንበሳው ምስል ራስ ላይ አልትራቫዮሌት ጨረር ሲበራበት ወደ ቢጫነት የሚለወጥ ፍሎረሰንት ምልክት።

አዲሱ የብር ኖቶች ከሚያመጡት በርካታ ጠቀሜታዎች በተጨማሪ በህወሓት ዘመን በሃሰት ሲሰራጩ የነበረውን የገንዘብ መጠን፤ አለአግባብ ወደ ኢኮኖሚ የተረጨውን የብር ኖት ለመሰብሰብ እና የዋጋ ግሽበትን ለመከላከል እንደሚጠቅም ተነግሯል፡፡

በኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ ከመደበኛው የባንክ ሥርዓት ውጪ ከ113 ቢሊዮን ብር በላይ ይንቀሳቀሳል። አዲሱ የብር ኖት ለውጥ ይህንን በኢኮኖሚው ውስጥ የተረጨ ገንዘብ በባንኮች ተቋማዊ አሠራር ውስጥ እንዲያልፍ ያደርጋል ተብሎ ተገምቶዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: new birr notes, new currency, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Rahel says

    September 15, 2020 02:39 pm at 2:39 pm

    በርታልኝ፡አቢቹ፡ጀግናዬ፡ያመንከው፡እየሱስ፡አሁንም፡ከፍ፡ያድርግህ፡ከፍ፡አድርገኽናል

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule