• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወደ ኢትዮጵያ ሊገባ የነበረ 99 ሺህ የሚጠጋ ዶላር ተያዘ

September 16, 2020 06:02 am by Editor Leave a Comment

የዛሬ ሳምንት ረቡዕ ወደ አዲስ አበባ ሊጓዝ ከነበረው መንገደኛ ላይ ዋሽንግተን በሚገኘው ደለስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአሜሪካ ጉምሩክና ድንበር ተቆጣጣሪዎች የተያዘው ገንዘብ 99 ሺህ ዶላር የሚጠጋ እንደሆነ ተነግሯል።

ቢቢሲ እንዳረጋገጠው ከግለሰቡ ላይ የተያዘው የገንዘብ መጠን 98,762 ዶላር ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ ብር ሲመነዘር ከ3.6 ሚሊዮን ብር በላይ ይሆናል።

የጉምሩክ መስሪያ ቤቱ የሕዝብ ግንኙነት ሠራተኛ ስቲቭ ሳፕ ለቢቢሲ በሰጡት የጽሁፍ ምላሽ ላይ እንዳመለከቱት፣ ግለሰቡ ይዞት የነበረው ዶላር የተያዘበት ተጓዦች የያዙትን የገንዘብ መጠን እንዲያሳውቁ የሚጠይቀውን የአገሪቱን ሕግ በመተለላፍ ነው።

በተጨ ማሪም ቢቢሲ ባገኘው መረጃ መሰረት ግለሰቡ በዚሁ ሳቢያ ያልታሰረ ሲሆን የወንጀል ክስ ስላልተመሰረተበትም ማንነቱ እንደማይገለጽ ለማወቅ ተችሏል።

እንዲህ ዓይነት የሕግ ጥሰቶች ሲያጋጥሙ ክስ መመስረትን በተመለከተ የአሜሪካ ዐቃቤ ሕግ ውሳኔ እንደሚሰጥ ያመለከቱት ስቲቭ ሳፕ፤ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ዐቃቤ ሕጉ የወንጀል ክስ ላለመመስረት በመወሰኑ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት እንዳልሄደ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ነገር ግን ግለሰቡ የአገሪቱን የገንዘብ ዝውውርና መጠን የማሳወቅ ግዴታን ባለመፈጸሙ 98,762 ዶላር ተይዞበታል።

ስቲቭ ሳፕ እንዳሉት ተጓዦች በተለያየ መንገድና በተደጋጋሚ የያዙትን የገንዘብ መጠን በትክክል እንዲያሳውቁ እንደሚጠየቁና በመጨረሻም ይህን በጽሁፍና በቃል ለጉምሩክ ተቆጣጣሪዎች ማሳውቅ ይጠበቅባቸዋል። ይህ ሳይሆን ከተገኘ የያዙት ገንዘብ እንደሚያዝ ተናግረዋል።

ባለስልጣናት እንዳሉት ኢትዮጵያዊው ግለሰብ በአሜሪካ ሕጋዊ ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ ያለው ሲሆን ወደ አዲስ አበባ በሚያደርገው ጉዞ ላይ ነበር ገንዘቡ ሊያዝ የቻለው።

በወቅቱ ግለሰቡ የያዘውን የጥሬ ገንዘብ መጠን በቃልና በጽሁፍ እንዲያሳውቅ መጠየቁንና 14,000 ሺህ ዶላር እንደያዘ ቢገልፅም ይዞት በነበረው ቦርሳ ውስጥ 19,112 ዶላር ተገኝቷል።

ይህንን ተከትሎ በጉምሩክና በድንበር ተቆጣጣሪዎች ተፈትሾ አልፎ በነበረ ሌላ ሻንጣ ላይ በተደረገ ብርበራ ተጨማሪ 79,650 ዶላር በጫማና በጂንስ ሱሪ ኪሶች ውስጥ አግኝተዋል። በአጠቃላይም የተገኘው የዶላር መጠን 98,762 ሆኗል።

ስቲቭ ሳፕ ጨምረውም ግለሰቡ ይህን ያህል መጠን ያለው ገንዘብ እንደያዘና ለምን አገልግሎት ሊያውለው እንደነበር ያልገለጸ ሲሆን፤ የገንዘቡ ምንጭ ከየት እንደሆነ የታወቀ ነገር የለም።

በምድር፣ በአየርና በባሕር የአሜሪካ ድንበርን የሚያቋርጡ ሰዎች በሚይዙት የገንዘብ መጠን ላይ በሕግ የተጣለ ገደብ ባይኖርም መንገደኞች ከ10 ሺህ ዶላር በላይ የሆነ ገንዘብ ወይም ሌላ የገንዘብ መገልገያዎችን ወደ አገሪቱ ሲያስገቡም ሆነ ሲያስወጡ ለጉምሩክ ሠራተኞች ማ ሳወቅ ይጠበቅባቸዋል።

ይህንን ሕግ ተላልፈው የያዙትን ገንዘብ በትክክል ሳያሳውቁ የተገኙ ተጓዦች ከተያዘባቸው ገንዘብ አብዛኛውን ወይም ሁሉም የሚወረስ ሲሆን በተጨማሪም የወንጀል ክስ ሊመሰረትባቸው ይችላል።

ገንዘቡ የተያዘበት ግለሰብ እንዲመለስለት የመጠየቅ መብት ያለው ቢሆንም የተወረሰው ገንዘብ ምንጭና ሊውል የታሰበበት ዓላማ ሕጋዊ መሆኑን ማረጋገጥ ይጠበቅበታል።

መንገደኞች ወደ አሜሪካ ሲገቡም ሆነ ሲወጡ በእጃቸው ላይ ያለን የትኛውንም ዓይነት ገንዘብ መጠኑን ማሳወቅ የሚጠበቅባቸው ሲሆን ይህንንም የአሜሪካ የጉምሩክና የድንበር ቁጥጥር መስሪያ ቤት ያስፈጽማል።

መስሪያ ቤቱ በተጨማሪም የአገሪቱን የምድር፣ የአየርና የባሕር ድንበሮችን ከመጠበቅ ባሻገር ሕጋዊ የንግድና የጉዞ እንቅስቃሴ እንዲሁም የገንዘብ ልውውጥ እንዲኖር የተለያዩ ሕጎችን ያስፈጽማል። © ቢቢሲ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: tplf, us dollar to ethiopia

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule