• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወደ ኢትዮጵያ ሊገባ የነበረ 99 ሺህ የሚጠጋ ዶላር ተያዘ

September 16, 2020 06:02 am by Editor Leave a Comment

የዛሬ ሳምንት ረቡዕ ወደ አዲስ አበባ ሊጓዝ ከነበረው መንገደኛ ላይ ዋሽንግተን በሚገኘው ደለስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአሜሪካ ጉምሩክና ድንበር ተቆጣጣሪዎች የተያዘው ገንዘብ 99 ሺህ ዶላር የሚጠጋ እንደሆነ ተነግሯል።

ቢቢሲ እንዳረጋገጠው ከግለሰቡ ላይ የተያዘው የገንዘብ መጠን 98,762 ዶላር ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ ብር ሲመነዘር ከ3.6 ሚሊዮን ብር በላይ ይሆናል።

የጉምሩክ መስሪያ ቤቱ የሕዝብ ግንኙነት ሠራተኛ ስቲቭ ሳፕ ለቢቢሲ በሰጡት የጽሁፍ ምላሽ ላይ እንዳመለከቱት፣ ግለሰቡ ይዞት የነበረው ዶላር የተያዘበት ተጓዦች የያዙትን የገንዘብ መጠን እንዲያሳውቁ የሚጠይቀውን የአገሪቱን ሕግ በመተለላፍ ነው።

በተጨ ማሪም ቢቢሲ ባገኘው መረጃ መሰረት ግለሰቡ በዚሁ ሳቢያ ያልታሰረ ሲሆን የወንጀል ክስ ስላልተመሰረተበትም ማንነቱ እንደማይገለጽ ለማወቅ ተችሏል።

እንዲህ ዓይነት የሕግ ጥሰቶች ሲያጋጥሙ ክስ መመስረትን በተመለከተ የአሜሪካ ዐቃቤ ሕግ ውሳኔ እንደሚሰጥ ያመለከቱት ስቲቭ ሳፕ፤ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ዐቃቤ ሕጉ የወንጀል ክስ ላለመመስረት በመወሰኑ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት እንዳልሄደ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ነገር ግን ግለሰቡ የአገሪቱን የገንዘብ ዝውውርና መጠን የማሳወቅ ግዴታን ባለመፈጸሙ 98,762 ዶላር ተይዞበታል።

ስቲቭ ሳፕ እንዳሉት ተጓዦች በተለያየ መንገድና በተደጋጋሚ የያዙትን የገንዘብ መጠን በትክክል እንዲያሳውቁ እንደሚጠየቁና በመጨረሻም ይህን በጽሁፍና በቃል ለጉምሩክ ተቆጣጣሪዎች ማሳውቅ ይጠበቅባቸዋል። ይህ ሳይሆን ከተገኘ የያዙት ገንዘብ እንደሚያዝ ተናግረዋል።

ባለስልጣናት እንዳሉት ኢትዮጵያዊው ግለሰብ በአሜሪካ ሕጋዊ ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ ያለው ሲሆን ወደ አዲስ አበባ በሚያደርገው ጉዞ ላይ ነበር ገንዘቡ ሊያዝ የቻለው።

በወቅቱ ግለሰቡ የያዘውን የጥሬ ገንዘብ መጠን በቃልና በጽሁፍ እንዲያሳውቅ መጠየቁንና 14,000 ሺህ ዶላር እንደያዘ ቢገልፅም ይዞት በነበረው ቦርሳ ውስጥ 19,112 ዶላር ተገኝቷል።

ይህንን ተከትሎ በጉምሩክና በድንበር ተቆጣጣሪዎች ተፈትሾ አልፎ በነበረ ሌላ ሻንጣ ላይ በተደረገ ብርበራ ተጨማሪ 79,650 ዶላር በጫማና በጂንስ ሱሪ ኪሶች ውስጥ አግኝተዋል። በአጠቃላይም የተገኘው የዶላር መጠን 98,762 ሆኗል።

ስቲቭ ሳፕ ጨምረውም ግለሰቡ ይህን ያህል መጠን ያለው ገንዘብ እንደያዘና ለምን አገልግሎት ሊያውለው እንደነበር ያልገለጸ ሲሆን፤ የገንዘቡ ምንጭ ከየት እንደሆነ የታወቀ ነገር የለም።

በምድር፣ በአየርና በባሕር የአሜሪካ ድንበርን የሚያቋርጡ ሰዎች በሚይዙት የገንዘብ መጠን ላይ በሕግ የተጣለ ገደብ ባይኖርም መንገደኞች ከ10 ሺህ ዶላር በላይ የሆነ ገንዘብ ወይም ሌላ የገንዘብ መገልገያዎችን ወደ አገሪቱ ሲያስገቡም ሆነ ሲያስወጡ ለጉምሩክ ሠራተኞች ማ ሳወቅ ይጠበቅባቸዋል።

ይህንን ሕግ ተላልፈው የያዙትን ገንዘብ በትክክል ሳያሳውቁ የተገኙ ተጓዦች ከተያዘባቸው ገንዘብ አብዛኛውን ወይም ሁሉም የሚወረስ ሲሆን በተጨማሪም የወንጀል ክስ ሊመሰረትባቸው ይችላል።

ገንዘቡ የተያዘበት ግለሰብ እንዲመለስለት የመጠየቅ መብት ያለው ቢሆንም የተወረሰው ገንዘብ ምንጭና ሊውል የታሰበበት ዓላማ ሕጋዊ መሆኑን ማረጋገጥ ይጠበቅበታል።

መንገደኞች ወደ አሜሪካ ሲገቡም ሆነ ሲወጡ በእጃቸው ላይ ያለን የትኛውንም ዓይነት ገንዘብ መጠኑን ማሳወቅ የሚጠበቅባቸው ሲሆን ይህንንም የአሜሪካ የጉምሩክና የድንበር ቁጥጥር መስሪያ ቤት ያስፈጽማል።

መስሪያ ቤቱ በተጨማሪም የአገሪቱን የምድር፣ የአየርና የባሕር ድንበሮችን ከመጠበቅ ባሻገር ሕጋዊ የንግድና የጉዞ እንቅስቃሴ እንዲሁም የገንዘብ ልውውጥ እንዲኖር የተለያዩ ሕጎችን ያስፈጽማል። © ቢቢሲ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: tplf, us dollar to ethiopia

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule