• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የሤራ ፅንሰ ሃሳብ በኢትዮጵያ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ አሁን ገዝፎ ወጥቷል” ዶ/ር ደመቀ

September 21, 2020 02:32 pm by Editor Leave a Comment

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህር እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውጭ ግንኙነት ትብብር እና ኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ዳይሬክተር ዶክተር ደመቀ አጭሶ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳመለከቱት፣ በኢትዮጵያ የፈለገ ጥሩ ሃሳብ፣ ጥሩ አመለካከት ይዘህ ብትመጣ አንተን ለመቃረን ብቻ ሌላ ኃይል ተደራጅቶ ይጠብቅሃል። ይህ ማደም፤ ሴራ ነው። ይህ የሴራ ፅንሰ ሃሳብ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ከምንጊዜውም በላይ አሁን ገዝፎ ወጥቷል።

“የፈለገ ጥሩ ሃሳብ፣ ጥሩ አመለካከት ይዘህ ብትመጣ አንተን ለመቃረን ብቻ ሌላ ኃይል ተደራጅቶ ይጠብቅሃል”። ይህ የሴራ ፅንሰ ሃሳብ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ከምንጊዜውም በላይ አሁን ገዝፎ መውጣቱን ዶክተር ደመቀ ይናገራሉ።

መልካም ነገር ይዘህ ስትመጣ የአንተን መልካም ነገር የሚያኮላሹ፣ ከግብ እና ከዓላማህ የሚያጨናግፉ በርካታ ሕጋዊም ሆነ ሕገ ወጥ አደረጃጀቶች በሀገሪቱ እንዳሉ ያመለከቱት ዶክተር ደመቀ፣ እነዚህ ነገሮች ሆን ተብለው የሚደረጉ ካልበላሁ ልድፋው ዓይነት የአስተሳሰብ መሰረት ያላቸው ናቸው ብለዋል። ካልበላሁ ልድፋው ለየትኛውም ችግር መፍትሔ አምጥቶ እንደማያውቅም አመልክተዋል።

መልካም አስተሳሰቦች ስር እንዲሰዱና ግባችንን ማሳካት እንድንችል የሁሉንም ሰው ቀና ትብብር እንደሚያስፈልግ አመልክተው፣ የሁሉም ሰው አስተሳሰብ የአመለካከት መገራትን እንደሚፈልግ አስታውቀዋል። የተለያዩ አመለካከቶች ይኑሩ፣ እንከራከር፣ እንወያይ፣ በጥሩ መንፈስ መከራከር መልካም ነው ብለዋል።

ክርክር ጥሩ የሚሆነው መልስ ለመሰጣጠት ብቻ ሳይሆን ራስን ለማነፅ፣ ክፍተቶችን ለመሙላት፤ የተከራካሪህንም ክፍተቶች ለመሙላት የምታደርገው ዴሞክራቲክ የሆነ እና የሰለጠነ ክርክር መሆን ሲችል እንደሆነ ጠቁመው፣ ይህን ዴሞክራሲያዊ የሆነ ለመገነባቢያ የሚረዳ የክርክር ባህል ማዳበር እንደሚገባ አመልክተዋል። በእኛ ሀገር ግን እየሆነ ያለው ክርክር ለማጥቃት እና ለመከላከል እንደሆነም ገልጸዋል።

በኛ ሀገር የፖለቲካ ባህል ሀገር ሊገነባ የሚችል ሃሳብ ይዘህ ብትመጣ ከአንተ በተቃራኒ በመቆም ምንም ሳያዳምጥህ መልስ የሚሰጥህ ወይም ስትናገር የሚያዳምጥህ አንተን ለማጥቃት ወይም የአንተን ሃሳብ ለማኮላሸት ነው የሚሉት ዶክተር ደመቀ፣ ይህ ወደአሰብነው ግብ እንዳንደርስ እንደሚያደርገን ጠቁመዋል። እከሌ በዚህ ጎራ ተሰልፏል።

ስለዚህ ከሱ ጋር ላለመሰለፍ በማለት ሆን ተብሎ ከሱ ጋር ላለመሆን የሆነ ስንጥር እየሰነጠረ በተቃራኒህ ይቆማል። አንድ ከምሆን ሞቼ እገኛለሁ ይልሃል፤ ይህ የፖለቲካ ባህል የትም እንደማያደርሰን አመልክተዋል።

ይህ ዓይነት አካሄድ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ አሁን እየበዛ እንደመጣ ያመለከቱት ዶክተር ደመቀ፣ ከዚህ የተነሳም ግባችን ላይ እንዳንደርስ ፅንፍ የረገጡ ኃይሎች የአንዱን መብት፣ የመኖር ህልውና፣ ባህል፣ ወግ፣ ዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶችን ከግንዛቤ ሳያስገቡ እኔ ብቻ በሚል አስተሳሰብ ከምንጊዜውም በላይ ጎልተው መምጣታቸውን አስታውቀዋል።

“ይህን በዓለም ታሪክ ስንቃኝ የቡድን አስተሳሰብ (the we group, the they group) የእኛ ቡድን የእነሱ ቡድን፤ ከእኛ ለእኛ ወገን የእኛ ቡድን የሚጠቀመውን ነገር የእነሱ ቡድን እንዳይጠቀመው እናድርግ። የእኛ ቡድን የማያሳካውን ግብ የእነሱ ቡድን እንዳያሳካ እናድርግ የሚባል ሴራ በዓለማችን ላይ ከባባድ እልቂቶችን አስከትሏል” የሚሉት ዶክተር ደመቀ፣ የአንደኛውም ሆነ የሁለተኛው የዓለም ጦርነቶች የዚህ ዓይነት አስተሳሰብ ውጤቶች መሆናቸውን አስታውቀዋል።

“ለብዙ የአይሁድ ማህበረሰቦች በአውሮፓ እንዲታረዱ ምክንያት ሆኗል። ጭፍን በሆነ ጥላቻ መሰላል (ደረጃ) አስቀምጦ እነዚህ፣ እነዚህ ሰዎች መወገድ አለባቸው ብሎ ማሰብ በደቡብ አፍሪካ አንዳንድ ቦታዎች ላይ አይተናል። በኢትዮጵያም ውስጥ አንዳንድ ቦታዎች ላይ አልገባም ማለት አይቻልም። አንዳንድ ቦታዎች ላይ ሰዎች በእሳት ሲቃጠሉ አይተናል። ይህ በጣም አጸያፊ ተግባር ነው። ጭፍን ጥላቻ በጣም አስቸጋሪ ነገር ነው። ወደ እልቂት እንዳያመራን ዋልታ እረገጥ አመለካከቶችን ማስቀረት፣ መቁረጥ፣ መከራከርም ይኖርብናል ብለዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Interviews, Middle Column Tagged With: conspiracy theory, Ethiopia

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule