• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የሤራ ፅንሰ ሃሳብ በኢትዮጵያ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ አሁን ገዝፎ ወጥቷል” ዶ/ር ደመቀ

September 21, 2020 02:32 pm by Editor Leave a Comment

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህር እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውጭ ግንኙነት ትብብር እና ኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ዳይሬክተር ዶክተር ደመቀ አጭሶ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳመለከቱት፣ በኢትዮጵያ የፈለገ ጥሩ ሃሳብ፣ ጥሩ አመለካከት ይዘህ ብትመጣ አንተን ለመቃረን ብቻ ሌላ ኃይል ተደራጅቶ ይጠብቅሃል። ይህ ማደም፤ ሴራ ነው። ይህ የሴራ ፅንሰ ሃሳብ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ከምንጊዜውም በላይ አሁን ገዝፎ ወጥቷል።

“የፈለገ ጥሩ ሃሳብ፣ ጥሩ አመለካከት ይዘህ ብትመጣ አንተን ለመቃረን ብቻ ሌላ ኃይል ተደራጅቶ ይጠብቅሃል”። ይህ የሴራ ፅንሰ ሃሳብ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ከምንጊዜውም በላይ አሁን ገዝፎ መውጣቱን ዶክተር ደመቀ ይናገራሉ።

መልካም ነገር ይዘህ ስትመጣ የአንተን መልካም ነገር የሚያኮላሹ፣ ከግብ እና ከዓላማህ የሚያጨናግፉ በርካታ ሕጋዊም ሆነ ሕገ ወጥ አደረጃጀቶች በሀገሪቱ እንዳሉ ያመለከቱት ዶክተር ደመቀ፣ እነዚህ ነገሮች ሆን ተብለው የሚደረጉ ካልበላሁ ልድፋው ዓይነት የአስተሳሰብ መሰረት ያላቸው ናቸው ብለዋል። ካልበላሁ ልድፋው ለየትኛውም ችግር መፍትሔ አምጥቶ እንደማያውቅም አመልክተዋል።

መልካም አስተሳሰቦች ስር እንዲሰዱና ግባችንን ማሳካት እንድንችል የሁሉንም ሰው ቀና ትብብር እንደሚያስፈልግ አመልክተው፣ የሁሉም ሰው አስተሳሰብ የአመለካከት መገራትን እንደሚፈልግ አስታውቀዋል። የተለያዩ አመለካከቶች ይኑሩ፣ እንከራከር፣ እንወያይ፣ በጥሩ መንፈስ መከራከር መልካም ነው ብለዋል።

ክርክር ጥሩ የሚሆነው መልስ ለመሰጣጠት ብቻ ሳይሆን ራስን ለማነፅ፣ ክፍተቶችን ለመሙላት፤ የተከራካሪህንም ክፍተቶች ለመሙላት የምታደርገው ዴሞክራቲክ የሆነ እና የሰለጠነ ክርክር መሆን ሲችል እንደሆነ ጠቁመው፣ ይህን ዴሞክራሲያዊ የሆነ ለመገነባቢያ የሚረዳ የክርክር ባህል ማዳበር እንደሚገባ አመልክተዋል። በእኛ ሀገር ግን እየሆነ ያለው ክርክር ለማጥቃት እና ለመከላከል እንደሆነም ገልጸዋል።

በኛ ሀገር የፖለቲካ ባህል ሀገር ሊገነባ የሚችል ሃሳብ ይዘህ ብትመጣ ከአንተ በተቃራኒ በመቆም ምንም ሳያዳምጥህ መልስ የሚሰጥህ ወይም ስትናገር የሚያዳምጥህ አንተን ለማጥቃት ወይም የአንተን ሃሳብ ለማኮላሸት ነው የሚሉት ዶክተር ደመቀ፣ ይህ ወደአሰብነው ግብ እንዳንደርስ እንደሚያደርገን ጠቁመዋል። እከሌ በዚህ ጎራ ተሰልፏል።

ስለዚህ ከሱ ጋር ላለመሰለፍ በማለት ሆን ተብሎ ከሱ ጋር ላለመሆን የሆነ ስንጥር እየሰነጠረ በተቃራኒህ ይቆማል። አንድ ከምሆን ሞቼ እገኛለሁ ይልሃል፤ ይህ የፖለቲካ ባህል የትም እንደማያደርሰን አመልክተዋል።

ይህ ዓይነት አካሄድ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ አሁን እየበዛ እንደመጣ ያመለከቱት ዶክተር ደመቀ፣ ከዚህ የተነሳም ግባችን ላይ እንዳንደርስ ፅንፍ የረገጡ ኃይሎች የአንዱን መብት፣ የመኖር ህልውና፣ ባህል፣ ወግ፣ ዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶችን ከግንዛቤ ሳያስገቡ እኔ ብቻ በሚል አስተሳሰብ ከምንጊዜውም በላይ ጎልተው መምጣታቸውን አስታውቀዋል።

“ይህን በዓለም ታሪክ ስንቃኝ የቡድን አስተሳሰብ (the we group, the they group) የእኛ ቡድን የእነሱ ቡድን፤ ከእኛ ለእኛ ወገን የእኛ ቡድን የሚጠቀመውን ነገር የእነሱ ቡድን እንዳይጠቀመው እናድርግ። የእኛ ቡድን የማያሳካውን ግብ የእነሱ ቡድን እንዳያሳካ እናድርግ የሚባል ሴራ በዓለማችን ላይ ከባባድ እልቂቶችን አስከትሏል” የሚሉት ዶክተር ደመቀ፣ የአንደኛውም ሆነ የሁለተኛው የዓለም ጦርነቶች የዚህ ዓይነት አስተሳሰብ ውጤቶች መሆናቸውን አስታውቀዋል።

“ለብዙ የአይሁድ ማህበረሰቦች በአውሮፓ እንዲታረዱ ምክንያት ሆኗል። ጭፍን በሆነ ጥላቻ መሰላል (ደረጃ) አስቀምጦ እነዚህ፣ እነዚህ ሰዎች መወገድ አለባቸው ብሎ ማሰብ በደቡብ አፍሪካ አንዳንድ ቦታዎች ላይ አይተናል። በኢትዮጵያም ውስጥ አንዳንድ ቦታዎች ላይ አልገባም ማለት አይቻልም። አንዳንድ ቦታዎች ላይ ሰዎች በእሳት ሲቃጠሉ አይተናል። ይህ በጣም አጸያፊ ተግባር ነው። ጭፍን ጥላቻ በጣም አስቸጋሪ ነገር ነው። ወደ እልቂት እንዳያመራን ዋልታ እረገጥ አመለካከቶችን ማስቀረት፣ መቁረጥ፣ መከራከርም ይኖርብናል ብለዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Interviews, Middle Column Tagged With: conspiracy theory, Ethiopia

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule