• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት “የመጨረሻ” ያለው ሤራ መክሸፉን መቀበል አቅቶታል

July 10, 2020 05:29 pm by Editor Leave a Comment

መንግሥት ህወሃትን ቀስ በቀስ ሥሩን እየቆራረጠ ቢቆይም አብዛኞች ባለመረዳትና በተገዙ ኃይሎች ውዥንብር ዕድሜው ሊራዘም እንደቻለ ለህወሃት ቅርበት ያላቸው እየገለጹ ነው። በተቀነባበረ ዕቅድ ሃጫሉ እንዲገደል ተደርጎ መንግሥትን ለመገልበጥ የታቀደውና የመጨረሻ የተባለው ሤራ መክሸፉ ህወሃት መንደር ግራ መጋባት መፍጠሩ ተስምቷል። የዐቢይ አስተዳደር እንደሚባለው ደካማ እንዳልሆነም አንዳንዶቹ በይፋ ሲናገሩ ተደምጧል።

ለውጡን ተክትሎ ከህወሃት አሰልቺ የስብሰባና የግምገማ (ምይይጥ) ባህል በተቃራኒው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በፍጥነት መጓዛቸውና ለህወሃቶች ከጅምሩ የማሰቢያ ጊዜ የከለከለ ነበር። የጎልጉል ታማኝ የመረጃ ምንጭ እንደሚሉት፤ የህወሃት ከፍተኛ አመራሮች ሲነጋ ልክ እንደማንኛውም ተራ ዜጋ ከፍተኛና አዳዲስ ውሳኔዎችን ይሰማሉ። በዚህም እነርሱ ለአንዱ ጉዳይ አንድ ወር ሲሰበሰቡና ለውሳኔ የያዙትን ጉዳይ ሳይጨርሱ አዳዲስ ጉዳይ ከመንግሥት በኩል በፍጥነት እየተነባበረባቸው፤ ራሳቸውን ከሂደቱ ጋር ማስማማት አቅቷቸው መቸገራቸውን ከከፍተኛ አመራሮች መስማታቸውን የመረጃ ምንጩ ያስረዳሉ።

ተቀማጭነታቸው በአሜሪካ የሆኑት እኚህ የህወሃት ወዳጅ በትላትናው ዕለት ከቅርብ ወዳጃቸው ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተረዱት አሁን የከሸፈው ሤራ በህወሃት ዘንድ የመጨረሻው ነበር። በነበረው ስሌት ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ወርደው በእስር ላይ ነበሩ። “ግን” አሉ ሲያስረዱ “ግን ነገሩ ሌላ ሆኖ በህወሃት አመራሮችና የቅርብ ደጋፊዎቻቸውና ተባባሪዎቻቸው ዘንድ የማይታመን ሆኗል”።

“ወዳጄ እንደነገረኝ” አሉ “የህወሃቱ ወዳጄ እንደነገረኝ የታሰበው ሳይሆን ቀርቶ መንግሥት ሁሉንም ጉዳይ መቆጣጠሩ የዐቢይ መንግሥት ለካስ ጠንካራ ነው፤ ከዚህስ በኋላ ምን ብናደርግ ይሻላል?” የሚል ውይይት አስነስቷል። ውይይቱ ንዴት የወለደው ነው።

ጎልጉል ከወራት በፊት ህወሃት በዲጂታል ወያኔ አማካይነት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ላይ የተካሄደው በሂሳብ የተሰራ የማጠልሸትና ከህዝብ የመነጠል ዘመቻ በውጤት የታጀበና ዓላማውን ያሳካ ሲል መገምገሙን ዘግበን ነበር። በዚሁ ዘገባ የመጀመሪያው የትግል ምዕራፍ ተጠናቋል ወደ ቀጣዩ የትግል ምዕራፍ በመሸጋገር መንግሥት የማስወገዱን ተግባር እናጣድፍ ማለቱ ተመልክቶ ነበር።

ህወሃት “እረኛውን ምታ በጎቹ ይበተናሉ” በሚለው መርህ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ላይ ያነጣጠረ ዘመቻ ከፍቶ የሚነዱትን ሲነዳ፣ የተገዙትን ሲጠቀምባቸው፣ የመሪያቸው አካሄድ ያልገባቸው ደግሞ ያለምክንያት ሲቃወሙ ህወሃት በመካከሉ አገግሞ እንዲነሳ ዕድል ሰጡት። የተከፈተውን የአፈና በር በወጉ መጠቀም ያቃታቸው፣ የተከፈተውን በር በመጠቀም በሤራ የተሳሰሩ መንግሥትን ፋታ ነሱት፤ በተለይ በሚዲያው መስክ። ሂደቱን በጽሞና የሚከታተሉ ደጋግመው ሲወተውቱ ይሰማ እንደነበረው የህወሃት ጥንካሬ ሳይሆን፣ የሌሎች ተባባሪ መሆን መንግሥትን ክፉኛ ጎድቶት ቆይቷል።

ቀደም ሲል የዘረጋውን የተተበተበ መስተጋብር (ኔትወርክ) በመጠቀም፣ እንዲሁም አሁን የከፋቸውንና ሥልጣን ባቋራጭ የሚመኙ ወገኖችን በማስተባበር መልኩን እየቀያየረ የሰነበተው ህወሃት ቀጣይ አካሄዱ የገባቸው ዐቢይ “ወደፊት ገና ከባዱ ፈተና ይጠብቀናል፤ ያንን ካለፍን በኋላ ነው ወዳሰብነው መንገድ የምንጓዘው፤ የሚቀረን የሞት ሽረት ትግል አለ” ሲሉ አስታውቀው ነበር።

ዛሬ የተቃጣውን የማተራመስና አገሪቱን የማፈራረስ ዕቅድ መሆኑ የተነገረለትን ሥራ ከአጋሮቻቸው፣ ከጸጥታ መዋቅራቸው፣ ከታማኙ የመከላከያ ሠራዊትና በስተመጨረሻ አካሄዱ ከገባው ሕዝብ ጋር ሆነው ካመከኑ በኋላ የወታደራዊ  መኮንን መለያቸውን ለብሰው “አይሳካላችሁም” ሲሉ በቴሌቪሽን መስኮት ብቅ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ የመንግሥት አስተማሪነትና ታጋሽነት ማክተሙን ይፋ ሲያደርጉ ይነበብባቸው የነበረው ስሜት እልህና ቁጭት ብቻ ነበር።

እንዳሉት ሆኖ ዛሬ አገሪቱ ወደ መረጋጋት ስታመራ በህወሃት ላይ በተጓዳኝ የሚወሰዱ እርምጃዎች እየከረሩ ሄደዋል። መረጃ አቀባያችን እንዳሉት መንግሥት የህወሃትን የብር ምንጮች ለማምከን በሥሡ ጀመሮት የነበረውን እርምጃ ያጠብቃል። የድንበር ላይ እንቅስቃሴዎችን ሙሉ በሙሉ ዘግቷል። እንደ አስፈላጊነቱ ህወሃትን የሚያልፈሰፍስ እርምጃዎችን ለመውሰድ በጫፍ ላይ ነው። ከዚያ በፊት ግን አሁን ህወሃት መካከል የተነሳውን መከፋፈልና የትኛው ወገን አሸንፎ እንደሚወጣ ትንሽ ጊዜ በመስጠት መጠበቅ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ነን ማለት ይችላል።

የጦርነት ጉሰማውን አስመልክቶ “ወዳጄ ማንን ነው የምንዋጋው? ትግራይ ያለው መከላከያ ሠራዊት ላይ የትግራይ ኃይል ሊተኩስ ነው? ወይስ አፋርን ሄዶ ይወርራል? አማራ ክልልን ይወጋል? ኤርትራ ላይ ሊዘምት ነው? እውነት እንነጋገር ከተባለ ህወሃት ከማን ጋር ይዋጋል?” ሲሉ የህወሃት የጦርነት አዋጅ ከፕሮፓጋንዳ ያላለፈ መሆኑንን ወዳጃቸው በተዘዋዋሪ እንደነገሯቸው የዜናው አቀባይ ለጎልጉል ነገረዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የትግራይ ተወላጅ የመከላከያ አባላት መቀሌ ሄደው “በፌደራል ሥርዓቱ ውስጥ እስካላችህ ድረስ ህግ ልታከበሩ ይገባል” በሚል በዝግ የህወሃትን አመራሮች ካነጋገሩ በኋላ ህወሃቶቹ “ጊዜ ስጡን” ማለታቸው ታውቋል። በዚሁ መነሻ ይሁን በሌላ ህወሃት ካለፈው ሳምንት ጀመሮ እስካሁን በስብሰባ (ምይይጥ) ላይ ናት።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics, Right Column Tagged With: abiy ahmed, Ethiopia, hachalu, reform, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule