• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዲጂታል “ወያኔ”፤ “እረኛውን ግደል፣ መንጋው ይበተናል”

July 26, 2019 08:17 am by Editor 2 Comments

አገራችን ከህወሓት አፋኝ የግፍ አገዛዝ ወጥታ በለውጥ ሒደት ውስጥ ትገኛለች። ሆኖም በአፋኙ ዘመነ ወያኔ እንኳን ሆኖ በማያውቅ መልኩ በአሁኑ ጊዜ አገራችንን እያፈረሰ የሚገኘው በማኅበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ ያለው የሃሰትና የፈጠራ ዜና ነው። ለዚህ ደግሞ በርካታ መዋዕለ ንዋይ እየፈሰሰ ቀንተሌት ተግተው የሚሠሩ “የሳይበር ወታደሮች” ተመድበዋል። እነዚህ በተለይ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በትጋት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ዓላማቸው መረጃ ማዛባት፤ የሃሰት መረጃ መበተን፤ የሚወጡ መረጃዎችን ማወዛገብ (ሕዝብ እውነቱንና ሐሰቱን እንዳይለይ ማድረግ)፤ ወዘተ ናቸው።

ይህ በዕዝና ቁጥጥር የሚመራ ኃይል ዋና ትኩረት የሚያደርገው በለውጡ ዙሪያ ያሉትን አመራሮች ማጠልሸት፤ የሕዝብ ድጋፋቸውን ማምከን፤ ከተቻለም ሕዝብ እንዲነሳባቸው ማድረግ ነው። ከዚህም በተጨማሪ በልዩ ልዩ ረቂቅ ስልት በሚበትኑት መረጃ ሕዝብ ከሕዝብ ጋር እንዲጋጭ፤ ደም እንዲቃባ፤ ሰላም እንዲደፈርስ፤ ሕዝብ እንዲፈናቀል፤ ሕዝብ በመሪዎቹ ላይ እምነት እንዲያጣ በማድረግ “በአመራር ላይ ያለው ኃይል አገር ማስተዳደር አቅቶታል” በሚል በአገር ውስጥና በውጪ ተዓማኒነቱን ማሳጣት ነው።

ከዚህ ዓይነቱ እኩይ ተግባር ጋር በተያያዘ ዛጎል ዜና “መንግሥትን ከህዝብ የመነጠሉ ዘመቻ የተሳካ መሆኑ ተገመገመ፤ መንግሥት በሚስጢር የያዘው ኩዴታ የዚሁ አካል ነው” በሚል አንድ ዜና አስነብቧል። ከዚህ በታች እንደሚከተለው የቀረበ ሲሆን ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከዚህ የዲጂታል ፀረ-ኢትዮጵያ ዘመቻ ጋር በተያያዘ ምን እየሆነ እንዳለ ሰሞኑን የሚያቀርበው ዘገባ ይኖራል፤ በቀጣይም አገር ለማፍረስ የተካሄደውን የግድያ ሤራ አስመልክቶ ከዚሁ የዲጂታል የፈጠራ ወሬ ወረርሽኝ ጋር ያለውን ተዛምዶ በተመለከተ የሚያቀርበው ዘገባ ይኖረዋል።

መንግሥት ለመግልበጥ ውስጥ ውስጡን የተዘረጋው መረብ መበጠሱን የዛጎል የመረጃ ምንጮች አመለከቱ። ዕቅዱ የቆየ ቢሆንም ተግባራዊ ለማድረግ የተፈለገው የለውጡን መሪዎች ተቀባይነት ካመናመኑ በኋላ ሲሆን፣ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ የሕዝቡን ንቃተ ህሊናና ባህል ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት በከፍተኛ በጀት፣ በባለሙያዎችና በማዕከላዊ ዕዝ ደረጃ የተደራጀ የማኅበራዊ ሚዲያ ሠራዊት (ዲጂታል “ወያኔ”) ትልቁን ሚና እንደተጫወተ ታውቋል።

የመረጃው ምንጮች እንዳሉት ከፌዴራል መንግሥት ቀጥሎ ከፍተኛ ሠራዊትና የትጥቅ አቅም ያደራጀው ቡድን፣ መንግሥት አመኔታ እንዳይኖረው ባሰማራው የማኅበራዊ ሚዲያ ሠራዊት አማካይነት ውጤታማ ሥራ መሥራቱን ግምግሟል። በግምገማውም ጠቅላይ ሚ/ር ዐቢይን ለይቶ መምታት የሚለው ስትራቴጂ ግቡን መትቷል። ለዚሁም በዋናነት የዜጎች መፈናቀል፣ በተለይም በሚፈለገው መልኩ የተጠለፈው የአዲስ አበባ የባለቤትነት አጀንዳ፣ የለገጣፎ ህገወጥ ግንባታ አፈራረስና “ኦሮሞ መምራት አይችልም” የሚለው ስልት ከሚፈለገው በላይ ሰርጿል። የለውጡ መሪዎች የገነቡት የሕዝብ ድጋፍ እንዲተን ተደርጓል።

ዳግም ወደ ሥልጣን ለመምጣት እየሠራ ያለው ቡድን ሃሳቡን እውን ለማድረግ ቢነሳ የሚገዳደረው ኃይል የመከላከያ ሠራዊት ብቻ እንደሆነ ገምግሞ የመከላከያው ሠራዊት ውስጥ ሰርጎ የመግባት ሰፊ ሥራ ሰርቷል። ወዳጅ አገራትና ታማኝ የሠራዊቱ አመራሮች ሤራውን እንዳከሸፉት የገለጹት የመረጃው ሰዎች “ውጥኑ ውስን የብሔር ድርጅቶችን እንዲያካትት ተደርጎ የተሠራ ነበር” ሲሉ ገልጸዋል። የብሄር ድርጅት ያሏቸውን ግን አልዘረዘሩም።

ከመከላከያ ሠራዊት ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ሰአረ ግድያ ጋር ጉዳይ ግንኙነት ይኖረው እንደሆነ ለተጠየቁት ዝምታን የመረጡት የዛጎል ምንጮች፣ ሰሞኑንን የመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ከፍተኛ መኮንኖች በውስጣቸው ምንም ዓይነት ችግር እንደሌለና ለሕገመንግስቱ ታማኝ ሆነው እንደሚሠሩ በተደጋጋሚ ያስታውቁት በምክንያት መሆኑንን ግን አልሸሸጉም።

የአሜሪካ የጦር መኮንኖች በሥልጠና ስም ወደ ኢትዮጵያ የገቡት ለዚሁ ዓላማ ይሁን አይሁን ምላሽ ያልሰጡት የዜናው ሰዎች፣ ሕዝብ “እረኛውን ግደል፣ መንጋው ይበተናል” የሚል መርህ ያዘለውን አገሪቱን የመበተን ሤራ በማስተዋል ቢመረምር እንደሚሻል ግን ጠቁመዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ባህር ዳር የተፈጠረውን ቀውስ ተከትሎ ድንገተኛ መግለጫ ሲሠጡ አዲስ አበባ ዙሪያ ሁሉንም ተቆጣጥረናል፤ ችግር የለም ማለታቸው ይታወሳል። እርሳቸው ዝርዝሩን ባይናገሩም የድሮው አውሮፕላን ማረፊያ በሚገኘው የደኅንነት ቢሮ አዲስ አበባ ላይ የታቀደውን ሤራ ሲያቀነባበር ተደርሶበት እጃቸውን እንዲሰጡ የተጠየቁ መታኮስ መርጠው መመታታቸውን ውስጥ አዋቂዎቹ እንደማሳያ ገልጸዋል።

ዛጎል በዚህ መልኩ ያቀረበውን ዘገባ በተለየም የጦር ኃይሎች አካባቢ ግድያና ተኩስ በተመለከተ በወቅቱ የአሶሼትድ ፕሬስ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ጦር ኃይሎች አካባቢ ሰኔ 15 ቀን ምን እንደተከሰተ በወቅቱ ያሰባሰበውን መረጃ እንደዚህ ዘግቦት ነበር።

ሰኔ 15 ቀን አመሻሽ ላይ በአማራ ክልል እንዲሁም በአዲስ አበባ ውስጥ ቦሌ አካባቢ የተከሰተው ግርግር እና ግድያ ብዙ ትኩረት ቢስብም ጦር ኃይሎች በተለምዶ ሲግናል (በድሮ አጠራሩ መኮ) የተከሰተው ሁነት ግን እስካሁን ይፋ አልሆነም።

ጋዜጠኛ ኤልያስ ቢያንስ ሶስት ምንጮች አረጋገጡልኝ እንዳለው ጦር ኃይሎች አካባቢ በነበረው ግጭት ሁለት ወይም ሶስት ሰዎች ህይወታቸው አልፏል። እስከ ሌሊቱ ስድስት ሰዓት ገደማም የጥይት ተኩስ ይሰማ ነበር። ይህ ክስተት በዕለቱ ከነበሩት ሌሎች ግድያዎች ጋር የሚያያዝ እንደሆነ ግልፅ አይደለም።

በቅርቡ ስለ ጉዳዩ ጋዜጠኛው የጠየቃቸው አንድ የመንግሥት የሥራ ኃላፊ “ስለ ጉዳዩ መረጃ የለኝም፤ አጣርቼ መልስ ልሰጥህ እሞክራለሁ” የሚል ምላሽ ሰጥተው ነበር።

በጉዳዩ ዙሪያ መረጃ አለኝ ያለ አንድ ግለሰብ ለጋዜጠኛው ተከታዩን መረጃ አቀብሎ ነበር፦ “ስለ ሰኔ 15ቱ (የጦር ኃይሎች አካባቢ ጉዳይ) የተወሰነ መረጃ አለኝ። መረጃውን ላገኝ የቻልኩት ደግሞ በዛ ምሽት ከሞቱት ሶስት የፌዴራል ኮማንዶዎች አንዱ የአክስቴ ልጅ ስለነበር ሬሳ ለመቀበል ከቤተሰብ ጋር በሄድንበት ጊዜ የአሟሟቱ ጉዳይ ስለተነገረን ነው። እናም ጉዳዩ ከጄኔራሎቹ ግድያ ጋር በተያያዘ የተጠረጠረ አንድ ኮሎኔል ለመያዝ በሄዱበት ጊዜ በተፈጠረው የተኩስ ልውውጥ ምክንያት ነው። ግን እስካሁን አንድ የመንግሥት አካል ስለ ጉዳዩ ምንም ነገር አለማለታቸው እጅግ በጣም አሳዝኖኛል” በማለት የዓይን እማኝነቱን መስጠቱን ኤልያስ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: digital woyane, Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. እውነቱ ይነገር says

    August 19, 2019 01:06 am at 1:06 am

    ራሳቸውን ለእለት እንጀራ ብለው በክፉ መንፈስ ተወርሰው ክፉ ሥራን በወገናቸው ላይ የሚፈጽሙ (ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ! ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም (ዮሐንስ 10፡10 እንደተባለው) ተጋላቢ ሰዎች እውነትን ለጊዜው ገለው ሊቀብሯት ይችሉ ይሆናል! አንድ ቀን ግን የሰው እጅ ሳይነካው የእውነት መቃብር ቃ! ቃ!! ቃ!!! ቁ! ቁ!! ቁ!!! ቃቁ! ቃቁ!! ቃቁ!!! በማለት የተቀበረው በድን ሳይሆን እውነት በራሷ ሕያው ሆና በመነሳት ራሷን በይፋ ትገልጣለች!!!

    ያኔ ውሸት በእውነት፣ ጥላቻ በፍቅር፣ ጦርነት በሰላም፣ ዘረኛነት በሰውነት፣ ጠባብነት በሰፊነት፣ መለያየት በአብሮነት፣ሞት በሕይወት ደህና አድርገው ይዋጣሉ!!! እስከ አሁን ድረስ የተባለውና የተሟረተው ክፉ ነገር ሁሉ በምድራችን/በሕዝባችን ላይ እንዳይሆን ሳናውቀው የከለከለልን የሰማይና የምድር ጌታ እግዚአብሔር ለዘላልም ይክበር!!! አሜን፡፡

    Reply
  2. እውነቱ ይነገር says

    August 19, 2019 05:48 am at 5:48 am

    ይድረስ ለነፍሰ ገዳዮች እና አስገዳዮች ወይም ሐገር በጥባጮች በሙሉ!!!
    (የነፈሰ ገዳዩ/የሰይጣን ምቹ ፈረሰኞችና ፈረሶች በሙሉ!)
    የማስጠንቀቂያ መልእክት አለኝ!!!

    ራሳቸሁን ለእለት እንጀራ ብላችሁ ለክፉ ሥራ/መንፈስ ተሰታችሁና ተወርሳችሁ ክፉ ሥራን በወገናችሁ ላይ የፈጸማችሁና (ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ! ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም የዮሐንስ ወንጌል 10፡10 እንደተባለው) እያስፈጸማችሁ ያላችሁ ተጋላቢና ጋላቢ ሰዎች እውነትን ለጊዜው ገላችሁ መቅበር ትችሉ ይሆናል! አንድ ቀን ግን የሰው እጅ ሳይነካው የእውነት መቃብር ቃ! ቃ!! ቃ!!! ቁ! ቁ!! ቁ!!! ቃቁ! ቃቁ!! ቃቁ!!! በማለት የተቀበረው በድን ሳይሆን እውነት በራሷ ሕያው ሆና በመነሳት ራሷን በይፋ ትገልጣለች!!! ከዚያም እናንተ ወይም ልጆቻችሁና የልጅ ልጆቻችሁ በሙሉ ትናንት በትቢትና በትምክህት ዛሬ ደግሞ በፍርሃት ከተደበቃችሁበት ዋሻ ብቅ እያላችሁ በጉልበት ከድሐው ጉሮሮ በማስለቀስ በሰበሰባችሁት የሐገር ሐብት/ገንዘብ ሆደ አምላካቸው የሆኑትን ምንደኞችን እየገዛችሁ እንደ ወረርሺኝ በምድሪቷ ላይ የዘራችሁትን ደህና አድርጋችሁ እንደምታጭዱ ቅንጣት ያህል አልጠራጠርም!!!

    ያኔ ውሸት በእውነት፣ ጥላቻ በፍቅር፣ ጦርነት በሰላም፣ ዘረኛነት በሰውነት፣ ጠባብነት በሰፊነት፣ መለያየት በአብሮነት፣ሞት በሕይወት ደህና አድርገው ይዋጣሉ!!! ብርቱ የሆነው ጨለማ ከእሱ በበራታ ብርሃን ይገለጣል! ሞትና ጮኸት፣ ዋይታና ለቅሶ አስለቃሽ በነበሩት ላይ ማንም ሳያዝዛቸው ለባለቤቱ ይመለሳሉ!!!

    እስከ አሁን ድረስ የተባለውና የተሟረተው ክፉ ነገር ሁሉ በምድራችን/በሕዝባችን ላይ እንዳይሆን ሳናውቀው የከለከለልን የሰማይና የምድር ጌታ እግዚአብሔር ለዘላልም ይክበር!!! አሜን፡፡
    እኔ እንደሆንሁ እመኑኝ ይሆናል ብለን ሳንገምት እግዚአብሔር በራሱ የጀመረውን ይህን የምድሪቷን አንድነት መንፈስ በራሱ ኃይልና ምህረት በመልካም እንደሚጨርሰው በቃሉ በኩል ተስፋ ይዤ በመታመን እጠብቀዋለሁ፡፡ ከእኔ ጋር የሚስማማ ሳይሆን በተስፋ ቃሉ የሚታመን ብቻ አሜን ይበል???

    ሰላም ሁኑልኝ
    እውነቱ ይነገር ነኝ
    እግዚአብሔር ፈቅዶ
    ከሚያኖረኝና ከምኖርበት
    ስፍራ/ሐገር በመሆን!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule