• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ውረሩ፣ ያገኛችሁትን ግደሉ እየተባልን ነው የምንመጣው” እጃቸውን የሠጡ የትህነግ ታጣቂዎች

September 8, 2022 02:46 am by Editor 1 Comment

በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን ላይ የተነሳው የሽብር ቡድን በሕዝብ ላይ አያሌ በደሎችን አድርሷል። ከእኩይ ቡድን አቅራቢያ የሚገኙ የአማራና የአፋር ክልል ነዋሪዎች ደግሞ የሽብር ቡድኑ ግፍና ወረራ ገፈት ቀማሾች ናቸው። ለሦስተኛ ጊዜ ጦርነት ያነሳው የትህነግ የሽብር ቡድን የትግራይ ተወላጆችን ከሕፃናት እስከ አዛውንት ድረስ እየመለመለ ለጦርነት እየላካቸው ነው።

የሽብር ቡድኑ በአማራና አፋር ክልል በወረራ በያዛቸው አካባቢዎች ንፁሐንን በጅምላ ረሽኗል፣ ሃብትና ንብፈታቸውን ዘረፏል አውድሟል። የሽብር ቡድኑ የሚልካቸው ታጣቂዎች ሀገሩን እየተከላከለ በሚገኘው ጥምር ጦር እየተመቱ ብዙዎች ይረግፋሉ። እድል የቀናቸው እጃቸውን ሰጥተው ሕይወታቸውን ያተርፋሉ።

የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች በወልቃት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ለሚገኘው ጀግናው የሀገር መከላከያ በርካቶች እጃቸውን እየሰጡ ነው። እጃቸውን ከሰጡት መካከከል የሽሬው ተወላጅ አብርሃም በሪሁ ይገኝበታል። የትህነግን የሽብር ቡድን ከመቀላቀሉ አስቀድሞ የፌዴራል ፖሊስ አባል የነበረው አብርሃም የሰሜን ዕዝ በተካደ ጊዜ በትግራይ ልዩ ኃይል በቁጥጥር ሥር ዋልኩ ይላል። ከዚያ በኋላ የሽብር ቡድኑን እንዲቀላቀል ይጠይቁታል። እርሱም እምቢ እንዳላቸው ይናገራል። ከዚያ በኋላ ግን በግዳጅ የሽብር ቡድኑን ተቀላቅያለሁ ነው የሚለው። አብርሃም አለቆቹ “የብልጽግናን ወታደር እንደመስሰዋለን፣ ደምስሰን እኛ እራሳችን እንመራቸዋለን” እንደሚሏቸው ተናግረዋል።

የብልጽግና ወታደር መከላከያ፣ ልዩ ኃይልና ፋኖ ሊወጋችሁ መጥቷል እንደሚባሉም ገልጿል። የመከላከያን ምት አልችል ሲል እጁን እንደሰጠ የሚናገረው አብርሃም ያን ሁሉ ግፍ ያሳለፈ መከላከያ እንደዚህ ይቀበለናል ብዬ አላሰብኩም ነበር ብሏል። ላደረጉልኝ ሁሉ ምስጋና ይገባቸዋል፣ በጣም ተንከባክበውናል ነው ያለው።

ከሰባት ዓመት በላይ ያለ ሰው እንዳይቀመጥ ከመጡ ያርዷችኋል ይሉናል። “ይገድሏችኋል፣ ያርዷችኋል፣ ቤት ውስጥ ቁጭ ብላችሁ ከምትሞቱ ገድላችሁ ብትሞቱ ይሻላችኋል፣ ከሰባት ዓመት በላይ ያለን ሰው ይገድላችኋል፣ ከሞት ላትተርፉ ነገር ዝም ብላችሁ ወደ ውጊያ ብትገቡ ይሻላችኋል” ይሉናልም ብሏል።

ለግዳጅ እምቢ ያለ ልጅ እናት አባቱ ይታሠራሉ፣ እናት አባት ሲታሠሩ የግድ ወደ ውጊያ እንገባለን ነው ያሉት። የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጥተው በታላቋ ኢትዮጵያ በሰላም እንዲኖሩም ጥሪ አቅርቧል።

በትግራይ ለእርዳታ የሚገባው እህል ለባለሀብቶች እና ለባለስልጣናቱ እንደሚከፋፈል የተናገረው አብርሃም የማመላለሻ ነዳጅ የለም በሚል ሰበብ ደሃው ማኅበረሰብ እርዳታ እንደማይደርሰውም ተናግሯል። የተራቡ ድሃዎች እያሉ የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች የእርዳታ ምግብ እየተመገቡ እንደሚዋጉም አረጋግጧል። “ስንቅ ከሕዝባችን፣ ትጥቅ ከጠላታችን” እየተባለ አብዛኛው ታጣቂ ማርከን እናስታጥቃችኋለን እየተባለ በባዶ እጁ ነው የሚገባው ነው ያለው።

“ውረሩ፣ ያገኛችሁትን ግደሉ” እየተባልን ነው የምንመጣውም ብሏል።

የ55 ዓመቱ ገብረ ሰንበት ገበረ ኪዳን ደግሞ ነባር ታጋዮች ተብለን አዲስ ክፍለ ጦር ተመስርቶልን ወደ አፋር ተላክን ነው ያሉት። ከአፋር በኋላ ወደ ትግራይ ተመልሰው በወልቃይት በኩል መምጣታቸውንም ገልፀዋል። በተደጋጋሚ እየከዳሁ በተደጋጋሚ በግዴታ ተመልሼያለሁ ነው ያሉት። ለመከላከያ ሠራዊት እጃቸውን ከሰጡ በኋላ በጥሩ እንክብካቤ ላይ እንዳሉም ተናግረዋል።

የአክሱም ተወላጇና የአክሱም ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዓመት ተማሪዋ ሮዛ ሙሉጌታ ከቤቱ እኔ ነኝ ታላቋ፣ ከቤት አንድ ሰው መውጣት ደግሞ ግዴታ ነው፣ ብዙ ጊዜ ተደበቅሁ፣ ነገር ግን ቤተሰብ ይታሠራሉ፣ ቤተሰብ ከሚታሰሩና ከሚንገላቱ እኔ ብሞት ይሻለኛል ብዬ መጣሁ ነው ያለችው። በሽብር ቡድኑ ውስጥ ለሁለት ወራት እንደቆየች የተናገረችው ሮዛ ያለ መሣሪያ ውጊያ እንዳስገቧትና እጇን መስጠቷን ነው የተናገረችው።

ትግራይን ታላቅ ማድረግ አለብን ይሉናልም ብላናለች። የትህነግ የሽብር ቡድን መሪዎች የሚፈልጉት እንዲፈፀምላቸው እንጂ ሕዝቡ የሚፈልገውን አንዳችም ነገር እንደማያዳምጡና እንደማይቀበሉም ገልፃለች። የትግራይ ሕዝብ የሕወሃት ጠብ አጫሪነት እና እንግልት እንደሰለቸውም ሮዛ ተናግራለች። የሕወሃት መሪዎች ለስልጣናቸው ሲሉ የማያደርጉት ነገር እንደሌለም አስታውቃለች።

እርዳታ ስጡን ስንል፣ የእርዳታ እህል አይገባም፣ እህል የለም ይሉናል፣ ነገር ግን ስልጠና ከገባሁ ጀምሮ የምመገበው የእርዳታውን ስንዴ ነው፣ የገባኝ አሁን ነው እርዳታውን ታጣቂው እንደሚበላው ነው ያለችው።

“የትግራይ ልጆች ለማይሆን ነገር ዋጋ አትክፈሉ፣ እጃችሁን ስጡ፤ እኔ እጅ የሰጠኹባቸው ሰብዓዊነት የሚሰማቸው እና እውነተኛ ኢትዮጵያውያን ናቸው፣ እናንተም እጃችሁን ስጡ፣ ኢትዮጵያን አንድ ለማድረግ እጃችሁን በመስጠት ተባበሩ” ነው ያለችው ሮዛ።

ውረሩ የሚባሉት ሕዝብ በሚናገራቸው ልክ ሳይሆን ደግና ከትግራይ ሕዝብ ጋር መቼም ቢሆን እንደማይለያይም ገልጸዋል ታጣቂዎቹ። (ታርቆ ክንዴ፤ አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: eprdf, Ethiopia, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfai Habte says

    September 9, 2022 03:12 am at 3:12 am

    የኢትዮጵያን መሪዎች ዛሬ ነቅተዋል እንጂ የ ወያኔ ልብ እንደፈለጉት ነው የሚዘውረው የነበረው። ሰላም እያለ፡ ስንቅና መድሃኒት መግብ ዚያገባ ጦርነት ይጀምራል። የኣብይን ርህራሄ እንደ ጅልነት ቆጥሮ ለሰወስተኛ ግዜ ጦርነት መክፈቱ ለጥፋቱ መሆኑ ወያነ ረስቶትስል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule