• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ውረሩ፣ ያገኛችሁትን ግደሉ እየተባልን ነው የምንመጣው” እጃቸውን የሠጡ የትህነግ ታጣቂዎች

September 8, 2022 02:46 am by Editor 1 Comment

በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን ላይ የተነሳው የሽብር ቡድን በሕዝብ ላይ አያሌ በደሎችን አድርሷል። ከእኩይ ቡድን አቅራቢያ የሚገኙ የአማራና የአፋር ክልል ነዋሪዎች ደግሞ የሽብር ቡድኑ ግፍና ወረራ ገፈት ቀማሾች ናቸው። ለሦስተኛ ጊዜ ጦርነት ያነሳው የትህነግ የሽብር ቡድን የትግራይ ተወላጆችን ከሕፃናት እስከ አዛውንት ድረስ እየመለመለ ለጦርነት እየላካቸው ነው።

የሽብር ቡድኑ በአማራና አፋር ክልል በወረራ በያዛቸው አካባቢዎች ንፁሐንን በጅምላ ረሽኗል፣ ሃብትና ንብፈታቸውን ዘረፏል አውድሟል። የሽብር ቡድኑ የሚልካቸው ታጣቂዎች ሀገሩን እየተከላከለ በሚገኘው ጥምር ጦር እየተመቱ ብዙዎች ይረግፋሉ። እድል የቀናቸው እጃቸውን ሰጥተው ሕይወታቸውን ያተርፋሉ።

የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች በወልቃት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ለሚገኘው ጀግናው የሀገር መከላከያ በርካቶች እጃቸውን እየሰጡ ነው። እጃቸውን ከሰጡት መካከከል የሽሬው ተወላጅ አብርሃም በሪሁ ይገኝበታል። የትህነግን የሽብር ቡድን ከመቀላቀሉ አስቀድሞ የፌዴራል ፖሊስ አባል የነበረው አብርሃም የሰሜን ዕዝ በተካደ ጊዜ በትግራይ ልዩ ኃይል በቁጥጥር ሥር ዋልኩ ይላል። ከዚያ በኋላ የሽብር ቡድኑን እንዲቀላቀል ይጠይቁታል። እርሱም እምቢ እንዳላቸው ይናገራል። ከዚያ በኋላ ግን በግዳጅ የሽብር ቡድኑን ተቀላቅያለሁ ነው የሚለው። አብርሃም አለቆቹ “የብልጽግናን ወታደር እንደመስሰዋለን፣ ደምስሰን እኛ እራሳችን እንመራቸዋለን” እንደሚሏቸው ተናግረዋል።

የብልጽግና ወታደር መከላከያ፣ ልዩ ኃይልና ፋኖ ሊወጋችሁ መጥቷል እንደሚባሉም ገልጿል። የመከላከያን ምት አልችል ሲል እጁን እንደሰጠ የሚናገረው አብርሃም ያን ሁሉ ግፍ ያሳለፈ መከላከያ እንደዚህ ይቀበለናል ብዬ አላሰብኩም ነበር ብሏል። ላደረጉልኝ ሁሉ ምስጋና ይገባቸዋል፣ በጣም ተንከባክበውናል ነው ያለው።

ከሰባት ዓመት በላይ ያለ ሰው እንዳይቀመጥ ከመጡ ያርዷችኋል ይሉናል። “ይገድሏችኋል፣ ያርዷችኋል፣ ቤት ውስጥ ቁጭ ብላችሁ ከምትሞቱ ገድላችሁ ብትሞቱ ይሻላችኋል፣ ከሰባት ዓመት በላይ ያለን ሰው ይገድላችኋል፣ ከሞት ላትተርፉ ነገር ዝም ብላችሁ ወደ ውጊያ ብትገቡ ይሻላችኋል” ይሉናልም ብሏል።

ለግዳጅ እምቢ ያለ ልጅ እናት አባቱ ይታሠራሉ፣ እናት አባት ሲታሠሩ የግድ ወደ ውጊያ እንገባለን ነው ያሉት። የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጥተው በታላቋ ኢትዮጵያ በሰላም እንዲኖሩም ጥሪ አቅርቧል።

በትግራይ ለእርዳታ የሚገባው እህል ለባለሀብቶች እና ለባለስልጣናቱ እንደሚከፋፈል የተናገረው አብርሃም የማመላለሻ ነዳጅ የለም በሚል ሰበብ ደሃው ማኅበረሰብ እርዳታ እንደማይደርሰውም ተናግሯል። የተራቡ ድሃዎች እያሉ የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች የእርዳታ ምግብ እየተመገቡ እንደሚዋጉም አረጋግጧል። “ስንቅ ከሕዝባችን፣ ትጥቅ ከጠላታችን” እየተባለ አብዛኛው ታጣቂ ማርከን እናስታጥቃችኋለን እየተባለ በባዶ እጁ ነው የሚገባው ነው ያለው።

“ውረሩ፣ ያገኛችሁትን ግደሉ” እየተባልን ነው የምንመጣውም ብሏል።

የ55 ዓመቱ ገብረ ሰንበት ገበረ ኪዳን ደግሞ ነባር ታጋዮች ተብለን አዲስ ክፍለ ጦር ተመስርቶልን ወደ አፋር ተላክን ነው ያሉት። ከአፋር በኋላ ወደ ትግራይ ተመልሰው በወልቃይት በኩል መምጣታቸውንም ገልፀዋል። በተደጋጋሚ እየከዳሁ በተደጋጋሚ በግዴታ ተመልሼያለሁ ነው ያሉት። ለመከላከያ ሠራዊት እጃቸውን ከሰጡ በኋላ በጥሩ እንክብካቤ ላይ እንዳሉም ተናግረዋል።

የአክሱም ተወላጇና የአክሱም ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዓመት ተማሪዋ ሮዛ ሙሉጌታ ከቤቱ እኔ ነኝ ታላቋ፣ ከቤት አንድ ሰው መውጣት ደግሞ ግዴታ ነው፣ ብዙ ጊዜ ተደበቅሁ፣ ነገር ግን ቤተሰብ ይታሠራሉ፣ ቤተሰብ ከሚታሰሩና ከሚንገላቱ እኔ ብሞት ይሻለኛል ብዬ መጣሁ ነው ያለችው። በሽብር ቡድኑ ውስጥ ለሁለት ወራት እንደቆየች የተናገረችው ሮዛ ያለ መሣሪያ ውጊያ እንዳስገቧትና እጇን መስጠቷን ነው የተናገረችው።

ትግራይን ታላቅ ማድረግ አለብን ይሉናልም ብላናለች። የትህነግ የሽብር ቡድን መሪዎች የሚፈልጉት እንዲፈፀምላቸው እንጂ ሕዝቡ የሚፈልገውን አንዳችም ነገር እንደማያዳምጡና እንደማይቀበሉም ገልፃለች። የትግራይ ሕዝብ የሕወሃት ጠብ አጫሪነት እና እንግልት እንደሰለቸውም ሮዛ ተናግራለች። የሕወሃት መሪዎች ለስልጣናቸው ሲሉ የማያደርጉት ነገር እንደሌለም አስታውቃለች።

እርዳታ ስጡን ስንል፣ የእርዳታ እህል አይገባም፣ እህል የለም ይሉናል፣ ነገር ግን ስልጠና ከገባሁ ጀምሮ የምመገበው የእርዳታውን ስንዴ ነው፣ የገባኝ አሁን ነው እርዳታውን ታጣቂው እንደሚበላው ነው ያለችው።

“የትግራይ ልጆች ለማይሆን ነገር ዋጋ አትክፈሉ፣ እጃችሁን ስጡ፤ እኔ እጅ የሰጠኹባቸው ሰብዓዊነት የሚሰማቸው እና እውነተኛ ኢትዮጵያውያን ናቸው፣ እናንተም እጃችሁን ስጡ፣ ኢትዮጵያን አንድ ለማድረግ እጃችሁን በመስጠት ተባበሩ” ነው ያለችው ሮዛ።

ውረሩ የሚባሉት ሕዝብ በሚናገራቸው ልክ ሳይሆን ደግና ከትግራይ ሕዝብ ጋር መቼም ቢሆን እንደማይለያይም ገልጸዋል ታጣቂዎቹ። (ታርቆ ክንዴ፤ አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: eprdf, Ethiopia, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfai Habte says

    September 9, 2022 03:12 am at 3:12 am

    የኢትዮጵያን መሪዎች ዛሬ ነቅተዋል እንጂ የ ወያኔ ልብ እንደፈለጉት ነው የሚዘውረው የነበረው። ሰላም እያለ፡ ስንቅና መድሃኒት መግብ ዚያገባ ጦርነት ይጀምራል። የኣብይን ርህራሄ እንደ ጅልነት ቆጥሮ ለሰወስተኛ ግዜ ጦርነት መክፈቱ ለጥፋቱ መሆኑ ወያነ ረስቶትስል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule