
“ባልደራስ የራሱን ሚሊሻ አዘጋጅቶ ትህነግን ይግጠም” አስተያየት ሰጪዎች
ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ፤ ማዕከላዊ መንግስት ህወሓትን “ያለበት ድረስ ሂዶ ማጥፋት አለበት” ሲል አስታወቀ። ፓርቲው የኢትዮጵያ መንግሥት የመከላከያ ሰራዊቱን ባለበት ጸንቶ እንዲቆይ ያስተላለፈውን ውሳኔንም ነቅፏል። የባልደራስን አቋም የተቃወሙ አስተያየት ሰጪዎች ባልደራስ ውጊያ ከፈለገ ራሱ ሄዶ ትህነግን ይግጠም ሲሉ መግለጫውን ነቅፈዋል
ፓርቲው “መንግሥት ‘ምዕራፍ አንድ’ ያለውን ዘመቻ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ሳያረጋግጥ ማቆሙ፤ ትልቅ አደጋ ያዘለ ነው” ሲል ስጋቱን ገልጿል። ህወሓት አሁንም የሀገሪቱን አንድነት ሊፈታተን በሚችል ወታደራዊ ቁመና ላይ ይገኛል” ያለው ባልደራስ፤ መንግሥት “ዘመቻውን ያቆመበትን ምክንያት በተመለከተ በቂ ምላሽ አልሰጠም” ሲል ተችቷል። የፌደራል መንግሥቱ ለኢትዮጵያ ህዝብ “ንቀት እያሳየ ነው” ሲልም ነቅፏል፡፡
ፓርቲው በመግለጫው እንዳስታወቀው አሸባሪው ህወሓት በጀመረው ጦርነት ምክንያት ሀገራችን ኢትዮጵያ የህልውና ትንቅንቅ ላይ እንደምትገኝ ጠቁሟል፡፡
በዚህም አገርን ለማስቀጠል በተደረገው መስዕዋትነት ፓርቲው ግንባር ድረስ በመሄድ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱንም አስታውቋል፡፡
የሰሜኑ ጦርነት መነሻ አሸባሪው ህወሓት በጀመረው የቅድመ-ማጥቃት እርምጃ መሆኑን እንረዳለን ያለው መግለጫው፣ የፌደራል መንግስት ጥቃቱን ለመከላከል ያደረገው ሀገር አቀፍ ዘመቻ ትክክለኛና ፍትሃዊ እንደነበርም ጠቁሟል፡፡
አሸባሪው ህወሓት አሁንም የአገሪቱን አንድነት ሊፈታተን በሚችል ወታደራዊ ቁመና ላይ ይገኛል ያለው መግለጫው፣ የዘመቻው ፍፃሜ የኢትዮጵያን አንድነት አደጋ ላይ የሚጥለውን የህወሓት ወታደራዊ አቅም በመስበር መቋጫት ይገባል ብሏል፡፡
ከምክክር ኮሚሽኑ ጋር በተያያዘ መንግስት እያካሄደ ያለው እንቅስቃሴ የአገራችንን ፖለቲካዊ ጥያቄዎች በውይይትና በምክክር ለመፍታት ትልቅ እድል እንደሚፈጥር የጠቆመው መግለጫው፣ የምክክር ሂደቱ አትዮጵያን አሸናፊ በሚያደርግ መልኩ እንዲጠናቀቅ እና ግልፀኝነት የተሞላበት ምክክር እንዲሆን ፓርቲው የበኩሉን አስታዋፅኦ እንደሚያደርግ አስታወቋል፡፡
የባልደራስን መግለጫ ተከትሎ አስተያየት የሰጡ መግለጫውን በመደገፍ የተናገሩ ሲሆን ሌሎች ግን ራሳቸው ሄደው የማይዋጉትን ጦርነት መከላከያው ይሂድ ብለው መወሰን አግባብ አይደለም በሚል ነቅፈዋል። በአማራና አፋር የመንደር ሚሊሻዎች ሳይቀሩ ትህነግን ሲዋጉ እንደነበር ባልደራስም እንዲሁ የራሱን ሚሊሻ አስተባብሮ ትህነግን መግጠም ይችላል በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
ኣሁንም ባልደራስ የጦርነትና የዕልቂት እንጂ የሰላምና የዕርቅ ወይም ሌላ ኣማራጭ የለውም። ትንሽ ተንፈስ ተብሎ ነበር ኣሁንም ሌላ የሽብርና የከፋፋይነት ዘመቻ በሕዝብ ስም ዕልቂት እንዲፈጠር መወትወት ኣያዛልቅም። በአንድ ክልል ውስጥ ያለ ክልሉ መንግስት ፈቃድ ገብቶ ጦርነት መግጠም ሕገመንግስታዊ ስለ መሆኑ ባልደራስ መረዳት ወይም መጠየቅም ኣልቻለም። የፌዴራል መንግስት የደርግ ዓይነት መንግስት ኣይደለም። እንደፈለገ በክልል መንግስት ውስጥ ጦር አዞ የፈለገውን ለማድረግ ሕገመንግስት ኣይፈቅድም። የትህነኣግ ጦር ከትግራይ ክልል ወጥቶ ሌላውን ክልል ቢወጋ የፌዴራል ጦር ኣስፈላጊውን እርምጃ ይወስዳል። በኣፋር በሃማራ ክልል ወይም ቤንሻጉል በኩል ትህነኣግ ሊዋጋ ቢሄድ መከላከያና የክልል ሚሊሺያ ሊዋጉ ይችላሉ። ትህነኣግ ከሁሉም ክልሎች ከወጣ ግን ያለበት ቦታ ሄዶ መዋጋት መንግስት ኣለበት ብሎ ባልደራስ የመጠየቅ ስልጣን ወይም መብት የለውም። ይህ የባልደራስ ኣካሄድ ከፌዴራሊዝም የራስ መስተዳድሩ መርዕ ጋር ሊጠረስ ስለሚችል ባልደራሶች የሕገመንግስት ሀሁ… ሊማሩ ይገባል።
BALDERAS is a legal opposition party fully committed to peaceful struggle only.The primary responsibility to defend the country when attacked by foreign or internal enemies is that of the government in power through the national army and through the mobilization of the entire Ethiopian people including members of BALDERAS.As such,BALDERAS does not have the popular mandate to replace the government in respect .
ከዚህ በላይ ባለው አጎልጉል ጽሁፍ መጨረሽ ላይ “….. ሌሎች ግን ራሳቸው ሄደው የማይዋጉትን ጦርነት መከላከያው ይሂድ ብለው መወሰን አግባብ አይደለም በሚል ነቅፈዋል።” የሚል ይገኛል። ጉድ እኮ ነው! መክላከያ ያልተላከ ማን ሊላክ ነው? የመከላከያ ሥራውስ ምንድን ነው? በርግጥ መክላከያ ከሌለ ሌላው ሰው መሄዱ የማይቀር ነው። በነገራችን ላይ ባልደራስ የመወሰን መብት የለውም። የማዘዝ/የመውሰን ሥልጣን ያለው ጠ/ሚንስትሩ ነው።