• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የፌደራል መንግሥቱ ለኢትዮጵያ ህዝብ ንቀት እያሳየ ነው፤ ህወሓትን ያለበት ድረስ ሂዶ ማጥፋት አለበት” – ባልደራስ

January 13, 2022 11:14 am by Editor 3 Comments

“ባልደራስ የራሱን ሚሊሻ አዘጋጅቶ ትህነግን ይግጠም” አስተያየት ሰጪዎች

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ፤ ማዕከላዊ መንግስት ህወሓትን “ያለበት ድረስ ሂዶ ማጥፋት አለበት” ሲል አስታወቀ። ፓርቲው የኢትዮጵያ መንግሥት የመከላከያ ሰራዊቱን ባለበት ጸንቶ እንዲቆይ ያስተላለፈውን ውሳኔንም ነቅፏል። የባልደራስን አቋም የተቃወሙ አስተያየት ሰጪዎች ባልደራስ ውጊያ ከፈለገ ራሱ ሄዶ ትህነግን ይግጠም ሲሉ መግለጫውን ነቅፈዋል

ፓርቲው “መንግሥት ‘ምዕራፍ አንድ’ ያለውን ዘመቻ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ሳያረጋግጥ ማቆሙ፤ ትልቅ አደጋ ያዘለ ነው” ሲል ስጋቱን ገልጿል። ህወሓት አሁንም የሀገሪቱን አንድነት ሊፈታተን በሚችል ወታደራዊ ቁመና ላይ ይገኛል” ያለው ባልደራስ፤ መንግሥት “ዘመቻውን ያቆመበትን ምክንያት በተመለከተ በቂ ምላሽ አልሰጠም” ሲል ተችቷል። የፌደራል መንግሥቱ ለኢትዮጵያ ህዝብ “ንቀት እያሳየ ነው” ሲልም ነቅፏል፡፡

ፓርቲው በመግለጫው እንዳስታወቀው አሸባሪው ህወሓት በጀመረው ጦርነት ምክንያት ሀገራችን ኢትዮጵያ የህልውና ትንቅንቅ ላይ እንደምትገኝ ጠቁሟል፡፡

በዚህም አገርን ለማስቀጠል በተደረገው መስዕዋትነት ፓርቲው ግንባር ድረስ በመሄድ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱንም አስታውቋል፡፡

የሰሜኑ ጦርነት መነሻ አሸባሪው ህወሓት በጀመረው የቅድመ-ማጥቃት እርምጃ መሆኑን እንረዳለን ያለው መግለጫው፣ የፌደራል መንግስት ጥቃቱን ለመከላከል ያደረገው ሀገር አቀፍ ዘመቻ ትክክለኛና ፍትሃዊ እንደነበርም ጠቁሟል፡፡

አሸባሪው ህወሓት አሁንም የአገሪቱን አንድነት ሊፈታተን በሚችል ወታደራዊ ቁመና ላይ ይገኛል ያለው መግለጫው፣ የዘመቻው ፍፃሜ የኢትዮጵያን አንድነት አደጋ ላይ የሚጥለውን የህወሓት ወታደራዊ አቅም በመስበር መቋጫት ይገባል ብሏል፡፡

ከምክክር ኮሚሽኑ ጋር በተያያዘ መንግስት እያካሄደ ያለው እንቅስቃሴ የአገራችንን ፖለቲካዊ ጥያቄዎች በውይይትና በምክክር ለመፍታት ትልቅ እድል እንደሚፈጥር የጠቆመው መግለጫው፣ የምክክር ሂደቱ አትዮጵያን አሸናፊ በሚያደርግ መልኩ እንዲጠናቀቅ እና ግልፀኝነት የተሞላበት ምክክር እንዲሆን ፓርቲው የበኩሉን አስታዋፅኦ እንደሚያደርግ አስታወቋል፡፡

የባልደራስን መግለጫ ተከትሎ አስተያየት የሰጡ መግለጫውን በመደገፍ የተናገሩ ሲሆን ሌሎች ግን ራሳቸው ሄደው የማይዋጉትን ጦርነት መከላከያው ይሂድ ብለው መወሰን አግባብ አይደለም በሚል ነቅፈዋል። በአማራና አፋር የመንደር ሚሊሻዎች ሳይቀሩ ትህነግን ሲዋጉ እንደነበር ባልደራስም እንዲሁ የራሱን ሚሊሻ አስተባብሮ ትህነግን መግጠም ይችላል በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: balderas

Reader Interactions

Comments

  1. gi says

    January 13, 2022 12:42 pm at 12:42 pm

    ኣሁንም ባልደራስ የጦርነትና የዕልቂት እንጂ የሰላምና የዕርቅ ወይም ሌላ ኣማራጭ የለውም። ትንሽ ተንፈስ ተብሎ ነበር ኣሁንም ሌላ የሽብርና የከፋፋይነት ዘመቻ በሕዝብ ስም ዕልቂት እንዲፈጠር መወትወት ኣያዛልቅም። በአንድ ክልል ውስጥ ያለ ክልሉ መንግስት ፈቃድ ገብቶ ጦርነት መግጠም ሕገመንግስታዊ ስለ መሆኑ ባልደራስ መረዳት ወይም መጠየቅም ኣልቻለም። የፌዴራል መንግስት የደርግ ዓይነት መንግስት ኣይደለም። እንደፈለገ በክልል መንግስት ውስጥ ጦር አዞ የፈለገውን ለማድረግ ሕገመንግስት ኣይፈቅድም። የትህነኣግ ጦር ከትግራይ ክልል ወጥቶ ሌላውን ክልል ቢወጋ የፌዴራል ጦር ኣስፈላጊውን እርምጃ ይወስዳል። በኣፋር በሃማራ ክልል ወይም ቤንሻጉል በኩል ትህነኣግ ሊዋጋ ቢሄድ መከላከያና የክልል ሚሊሺያ ሊዋጉ ይችላሉ። ትህነኣግ ከሁሉም ክልሎች ከወጣ ግን ያለበት ቦታ ሄዶ መዋጋት መንግስት ኣለበት ብሎ ባልደራስ የመጠየቅ ስልጣን ወይም መብት የለውም። ይህ የባልደራስ ኣካሄድ ከፌዴራሊዝም የራስ መስተዳድሩ መርዕ ጋር ሊጠረስ ስለሚችል ባልደራሶች የሕገመንግስት ሀሁ… ሊማሩ ይገባል።

    Reply
    • Teklebirhan says

      January 16, 2022 04:17 pm at 4:17 pm

      BALDERAS is a legal opposition party fully committed to peaceful struggle only.The primary responsibility to defend the country when attacked by foreign or internal enemies is that of the government in power through the national army and through the mobilization of the entire Ethiopian people including members of BALDERAS.As such,BALDERAS does not have the popular mandate to replace the government in respect .

      Reply
  2. Ashebir says

    January 13, 2022 02:31 pm at 2:31 pm

    ከዚህ በላይ ባለው አጎልጉል ጽሁፍ መጨረሽ ላይ “….. ሌሎች ግን ራሳቸው ሄደው የማይዋጉትን ጦርነት መከላከያው ይሂድ ብለው መወሰን አግባብ አይደለም በሚል ነቅፈዋል።” የሚል ይገኛል። ጉድ እኮ ነው! መክላከያ ያልተላከ ማን ሊላክ ነው? የመከላከያ ሥራውስ ምንድን ነው? በርግጥ መክላከያ ከሌለ ሌላው ሰው መሄዱ የማይቀር ነው። በነገራችን ላይ ባልደራስ የመወሰን መብት የለውም። የማዘዝ/የመውሰን ሥልጣን ያለው ጠ/ሚንስትሩ ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule