• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኬሪያና የጃዋር ድብቁ ግንኙነትና አዲሱ የቤት ውስጥ እስር

March 11, 2021 04:27 pm by Editor 2 Comments

የቀድሞ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የነበሩት ወ/ሮ ኬሪያ በዋስ መፈታታቸው ተሰምቷል። ፖሊስ ለችሎት እንዳስረዳው ወይዘሮዋ የተፈቱት ቀዳሚ ምርመራ እስኪሰማ ድረስ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀጽ 28 መሰረት ነው።  

ፋና ችሎቱን ጠቅሶ እንደዘገበው ወይዘሮ ኬሪያ ቀዳሚ ምርመራ እስከሚሰማ ድረስ የሚቆዩት በሰርቪስ ማረፊያ ነው። የህግ ማስከበሩ ሲጀመር ሌሎች ሲሸሹ መቀሌ ሆነው እጃቸውን የሰጡት የቀድሞ አፈ ጉባኤ፤ እጃቸውን ከሰጡ በኋላ ክስ ሳይመሰረትባቸው መቆየቱ ይታወሳል።

ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም እንዴት ወደ መቀሌ ሄዱ?   

አፈጉባዔዋ ወደ መቀሌ የሄዱት ከአዲስ አበባ ተገፍተው መሆኑንን ጉዳይን በወጉ ሲከታተሉ የነበሩ ይናገራሉ። ኬሪያ ሃላፊነታቸውን በገዛ ፈቃዳቸው መልቀቃቸውን ከማስታወቃቸው በፊት ከአቶ ጃዋር ጋር ጥብቅ ግንኙነት እንዲመሠርቱ ተደርጎ ነበር።  

ለጃዋር ሳሎን ቅርብ የሆኑ ኬሪያን በተደጋጋሚ እዚሁ ሳሎን እንዳዩዋቸው ምስክርነት ይሰጣሉ። የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ መረጃ የሚቀበላቸው የኦፌኮ ሰዎች እንዳሉት አፈጉባዔዋ ወደ መቀሌ ሊሄዱ ሰሞን በጃዋር ከፍተኛ ግፊት ይደረግባቸው እንደነበር አመራሮቹ ሲናገሩ መስማታቸውን አረጋግጠዋል።

ጃዋር መሀመድ ለምን ጫና ሊፈጥርባቸው እንደቻለ ሲያስረዱ “ወቅቱ የመንግሥት ፍጻሜ በመሆኑ ወ/ሮ ኬሪያ እጅግ ተፈላጊ ሚና መጫወት እንዳለባቸው በትህነግና በእነጃዋር ታምኖበት ነበር” ሲሉ ይጀምራሉ። አክለውም “ኬሪያ ወደ መቀሌ የመሄድ ብዙም ፍላጎት እንደሌላቸው ሲታወቅ ጃዋር መንግሥት እንደሚቀየር በማሳመን ከፓርቲያቸው መለየት እንደሌለባቸው በማስገንዘብ እንዲሄዱ ገፍቷቸዋል” ብለዋል።

“መንግሥት የመንግሥትነቱን ዕድሜ ጨርሷል” የሚለው ቅስቀሳ በትብብርና በቅንጅት ሲጀመር፣ ጎን ለጎን የትህነግ ሰዎችና አፈቀላጤዎች አጠር ባለ ጊዜ መንግሥትን በኃይል ለማስወገድ ማቀዳቸውን በቃል፤ ወታደራዊ ዝግጅቱን በተግባር እያሳዩና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ጦርነት ለማስነሳት ዕቅድ መኖሩን በአጋሮቻቸው አማካይነት ያስነግሩ እንደነበር ይታወሳል።

ምርጫ መደረግ እንደሌለበት ሲሰብኩ የነበሩት እነ ልደቱ አያሌው ሳይቀሩ በመናበብ “መንግሥት ከመስከረም 30 በኋላ የለም” የሚለውን ዘመቻ ሲያራግቡ ወ/ሮ ኬሪያ በእነ ጃዋር ግፊትና ትዕዛዝ አስፈጻሚነት ወደ ትግራይ አቅንተው መንግሥትን በገሃድ ተቃወሙ። የህገ መንግሥት ተርጓሚ አካል የሆነውን ትልቁን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሥልጣን መልቀቃቸውን ይፋ ሲያደርጉ ጃዋር የሚመራቸው ሚዲያዎች፣ የትህነግ ልሳኖችና በውጭ አገር ያሉ ተከፋይ ሚዲያና ወስዋሾች ዜናውን በስፋት አዳርሰውት ነበር።  

በወቅቱ ወ/ሮ ኬሪያ መቀሌ ተገደው እላፊ መናገራቸው ሲሰማ የትግራይ ቲቪ የመዝናኛ ክፍለጊዜ አዘጋጅቶ ኬሪያ ደስተኛ እንደሆኑ ለማስመለስ ተሞክሮ ነበር። በወቅቱ ጎልጉል በደረሰው መረጃ ግን ኬሪያ ተገደው ትግራይ ከሄዱ በኋላ ደስተኛ አልነበሩም።

በወቅቱ በትህነግ፣ እነጃዋርና ሌሎች ተባባሪዎች አማካይነት መንግሥት በኃይል ሲወገድ የውጭ ማኅበረሰብና መንግሥታትን ቅቡልነት ለማግኘት ወ/ሮ ኪሪያ አስፈላጊና ቁልፍ ሰው በመሆናቸው ነው ወደ ትግራይ እንዲሄዱና እንዲከዱ የተደረጉት የሚሉት የጎልጉል መረጃ ምንጭ፣ ትግራይ ከገቡ በኋላ ህገ መንግሥት እንደተጣሰ፣ በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት ህጋዊ እንዳልሆነ ጠቅስው መረጃ እንዲያሰራጩ ተደርጓል። ይህ ዓለምን የዞረ መግለጫና መረጃ ከተሰራጨ በኋላ መንግሥት በኃይል ሲቀየር የዓለም አቀፍ ተቋማትንና አገራትን ቅቡልነት ለማስገኘት የሕገመንግሥት ተርጓሚው ምክርቤት አፈጉባዔ የነበሩት ወ/ሮ ኬሪያ ተዘጋጅተው እንደነበር የመረጃው ምንጭ የኦፌኮን ከፍተኛ አመራሮች ጠቅሰው ተናግረዋል።

የታሰበው ሳይሆን ቀርቶ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ወዲያው ትህነግን ከድተው እጅ የሰጡት ኬሪያ እነ ስብሃት ነጋ ታስረው እስኪመጡ ድረስ ክስ ሳይመሰርትባቸው መቆየታቸው ይታወሳል። በዚሁ ቆይታቸው ምን መረጃ እንደሰጡና ለህግ ማስከበሩ ዘመቻ የሚጠቅም ግብዓት እንዳበረከቱ በግልጽ የተቀመጠ መረጃ የለም። ዛሬ በዋስ ከላይ በተቀመጠው መሰረት መፈታታቸውን ተከትሎ አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ተቃውሞ ሲያሰሙ እየታየ ነው።

ጎልጉል ያነጋገራቸው የመንግሥት ኃላፊ ከላይ በተዘረዘሩት ጉዳዮች ላይ መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ እንዳልሆኑ ጠሰው “ተቃውሞ በመረጃና በጭብጥ ላይ መከራከሪያ በማቅረብ ሲሆን አግባብ ነው፤ ከዚያ ውጭ አንድ ነገር ሲሆን በጥቅል መሳደብ፣ ማውገዝ፣ እኔን ስሙኝ ብሎ መወራጨት ህግን መጣስ ብቻ ሳይሆን ንግግር ከማብዛት የሚመጣ የልብ መደፈን ነው” ሲሉ በሰሙት ለጆሮ የሚቀፍ ስድብ ማዘናቸውን አስታውቀዋል። አግባብነት ያለውና መሰረታዊ መከራከሪያ የሚቀርብበት ትችት አስፈላጊ መሆኑንን ጠቅሰው “አሁን አሁን እላፊ መሳደብና እኔ እኔ … የሚል የትህነግ አይነት አመለካከት መግራት አስፈላጊ እየሆነ ነው” ብለዋል።

አንድ የህግ ባለሙያ “ወ/ሮ ኬሪያ አልተፈቱም። ወይዘሮ ኬሪያ ቀዳሚ ምርመራ እስከሚሰማ ድረስ የሚቆዩት በሰርቪስ ማረፊያ ነው። ውጭ ሆነው ክሳቸውን መከታተላቸው ሃጢያት የለውም። ነጻ አልተባሉም። የቤት ውስጥ እስር አይነት ወይም በረጅም ገመድ ማሰር እንደማለት ነው” የሚል አስተያየት ሰጥተዋል። አያይዘውም “በነጻ ቢለቀቁም መንግሥት ምን ያገባዋል? ጣልቃ ገብነት ይቁም እየተባለ እንደገና በፍርድ ቤት ሥራ መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ መጋበዝ አያስኬድም፣ ወይስ ጣልቃ ገብነቱን የምንቃወመው እኛ “ንጹህ ነው” ባልነው ሰው ላይ ሲፍጸም ብቻ ነው” ብለዋል።

በዛሬው ችሎት የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት ወይዘሮ ሕርቲ ምህረተአብ እና የክልሉ መንግሥት አማካሪ የነበሩት ወልደጊዮርጊስ ደስታ፣ እንዲሁም በእነ አባይ ወልዱ የክስ መዝገብ ላይ ከሚገኙ ተከሳሾች ውስጥ አምደማርያም ተፈራ በ30 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ መወሰኑ ተሰምቷል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: jawar, jawar massacre, keria, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. GI Haile says

    March 15, 2021 02:36 am at 2:36 am

    መልዕክቱ መልካም ነው ወ/ሮ ኬሪያ በአገርና በሕገመንግስቱ ላይ በስልጣናቸው ምክንያት ያደረጉት የውሸት ክስ የፌዴራል መንግስቱን በሕዝብና በመንግስት መካከል የነበረውን መልካም ግንኙነት ለማቃቃር መሞከራቸው እጅግ ከባድ ክህደትና ወንጀል ነው። ይህ ኣይነት የፓለቲካ ኣካሄድ በሌሎች አገር በሞትና በእስራት የሚያስቀጣ (Treasonous Act and. Sedition) ነው የፌዴራል መንጎስት ኣቃቤ ሕግ ጉዳዩን በምን አቅጣጫ ሊያቀርብ እንደሚችል ባይታወቅም ወ/ሮ ኬሪያ ከሶስት በላይ የፌዴራል ሕግ መጣሳቸው ግልፅ ነው። ከሕወኣት ጋር ሆነው ጦርነት ማወጃቸው ብቻ በሞት ቅጣት ሊያስቀጣ ወይም የዕድሜ ልክ ፍርድ ነው። ይህ ክስ የሲቪል ሳይሆን በሚሊቴሪ ትራይቡናል የሚቀርብ ክስ ነው።

    Reply
  2. Abebe sientayhu says

    April 24, 2021 10:03 am at 10:03 am

    ሰይጣኖች

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule